Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ

Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ This is Addis Ketema Sub-city Communication Office's Offical page,Come and join us!
(2)

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ዙሪያ አገልጋዩንና ተገልጋዩን ፊት ለፊት ያገናኘ የእንጠያየቅ መድረክ ተካሄደ::********************ሰኔ 11-201...
18/06/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ዙሪያ አገልጋዩንና ተገልጋዩን ፊት ለፊት ያገናኘ የእንጠያየቅ መድረክ ተካሄደ::
********************
ሰኔ 11-2018 ዓ.ም

የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባዘጋጀው የእንጠያየቅ መድረክ በቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት፣ በስራና ክህሎት ጽ/ቤት፣ በንግድ ጽ/ቤት፣ በመሬት ልማት ጽ/ቤት፣ በግንባታ ፈቃድ ጽ/ቤት፣ በህብረት ስራ ጽ/ቤት እንዲሁም በሌሎች ተቋማት በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ አገልግሎት ሰጭውንና ተገልጋዩን ፊት ለፊት ያገናኘ የእንጠያየቅ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው ዘመኑን የሚመጥን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው መድረክ መዘጋጀቱ አስተዳደሩ በበለጠ ክፍተቶችን ለይቶ ለማስተካከል የሚያግዝ ነው ሲሉ ገልፀዋል::


የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበራ ግርማ በበኩላቸው በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች እና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የእንጠያየቅ መድረክ መካሄዱ ለሁለቱም ወገን ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው መንግስት ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል::



መፈታት አለባቸው ተብለው በነዋሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የሁሉም ጽ/ቤት አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተው መድረኩ ተጠናቋል::

መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።************************ሰኔ 11-2018ዓምበአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በሚገኘው ዳግማዊ ብርሃን ...
18/06/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።
************************
ሰኔ 11-2018ዓም

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በሚገኘው ዳግማዊ ብርሃን ቁጥር 1 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በተካሄደው የፈተና ማስጀመሪያ
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ፣ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወረቅነህ፣ የከፍለ ከተማው ት/ት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ብሩክ ተ/ማርያም ፈተናውን አስጀምረዋል፡፡

ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ፈተና ላይ፣ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ 201 የፈተና ጣቢያዎች ከ86 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወረቅነህ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ ተከታታይነት ያለው ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው ፈተናው እጅግ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ ሲሉ ተናግረዋል::

የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ብሩክ ተ/ማርያም በበኩላቸው በክፍለ ከተማ ደረጃ በ18 የመፈተኛ ጣቢያ ከ9ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ አስታውቀዋል::

17/06/2026

!!

በባለጉዳይ ቀን እየተሰጠ ያለው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ መምጣቱ ተገለፀ፡፡ *****************ሰኔ 10 -2018ዓ.ምበአዲስ ከተማ ክ/ከተማ  በባለጉዳይ ቀን...
17/06/2026

በባለጉዳይ ቀን እየተሰጠ ያለው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ መምጣቱ ተገለፀ፡፡
*****************
ሰኔ 10 -2018ዓ.ም

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በባለጉዳይ ቀን እየተሰጠ የአዲስ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው እለትም የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በተገኙበት ተገልጋዮች እየተስተናገዱ ይገኛሉ::

በአገልግሎቱ የረካ ማህበረሰብ ለመፍጠር በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ ሁሉም የስራ ሃላፊ አመራርና ሰራተኛ ህብረተሰቡን ዝቅ ብሎ በማገልገል ህዝብና መንግሥት የጣለበትን አደራ ለመወጣት መስራት ይኖርበታል ብለዋል::

ከጊዜ ወደ ጊዜ የአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ ፣ ግልፅና ከእንግልት የፀዳ እየሆነ መጥቷል ያሉት ተገልጋዮች በበኩላቸው ለዚህም አመራሩ በባለ ጉዳይ ቀን ተገኝቶ አገልግሎት መስጠት በመቻሉ እና አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ እየተሰራ መሆኑ አስደሳች ብለዋል::

መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

ለዓመታት ስንጠይቃቸው ለነበሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታችን ተደስተናል ሲሉ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ::*********************ሰኔ 10-2018ዓ....
17/06/2026

ለዓመታት ስንጠይቃቸው ለነበሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታችን ተደስተናል ሲሉ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ::
*********************
ሰኔ 10-2018ዓ.ም
የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በልዩ ትኩረት እየሰራ ሲሆን በዛሬው የአዲስ ቅኝት ፕሮግራማችን በወረዳ 5፣ በወረዳ 6 እና በወረዳ 11 የተፈቱ ጥያቄዎችን በመመልከት የነዋሪዎችን አስተያየት ጠይቀናል::

የመልካም አስተዳደር ችግር የሆኑ በወረዳ 5 የመፀዳጃ እጥረትን ለመቅረፍና የመንገድ ዳር ክፍት ቱቦን ከደራሽ ጎርፍ ስጋት እንዲሁም ከሚጣሉ የተለያዩ ተረፈ ምርቶችን ለመከላከልና ጤናማ ከባቢ ለመፍጠር በተሠራው ሥራ እጅግ መርካታቸው ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል።

በወረዳ 6 ለረጅም አመት የመልካም አስተዳደር ችግር የሆነው ወንዝ ከፍተኛ ጎርፍ በነዋሪዎች ህይወት ላይ ደቅኖት የነበረው ስጋት የድጋፍ ግንብ በመገንባቱ ምክንያት ከስጋት ማላቀቅ መቻላቸውን የገለጹ ሲሆን በተመሳሳይ በወረዳ 11 ለረጅም ዓመት የመልካም አስተዳደር ችግር የነበረው የተማሪዎች የክፍል ጥምርታን ለማሳደግ የቦር አምባ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ መጀመሩን ነዋሪዎች በከፍተኛ ሁኔታ መደሰታቻው ገልጸዋል።

የአዲሰ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ትምህርት ጽ/አቤት ኃላፊ አቶ አብረሃም ጎሳ በበኩላቸው የቦር አምባ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ግንባታ እንዲደረግ በርካታ የአከባቢው ነዋሪዎች በተለያዩ መድረኮችና በመደበኛ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ በተደጋጋሚ ሲነሳ በመቆየቱ ምክንያት አሁን በጥሩ የግንባታ አፈጻጸም ሂደት ላይ እየተፋጠነ የሚገኝ መሆኑንና ለዚህም ሥራ መጀመር ስኬት የክፍለ ከተማና የወረዳ ካቢኔና አጠቃላይ አመራር ምስጋና ይገባቸዋል ሲሉ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የመልካም አስተዳደር፣ ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጓዱ ጥጋቡ በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማና በወረዳ 74 የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየትና ከነዋሪዎች የቀርቡ ቅሬታና አቤቱታዎች በሥርዓት ተይዘው እንዲመሩና አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ አሰራሮችን መሠረት በማድረግ በፍጥነት በመፍታት የህዝብ እርካታን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

አቶ ጓዱ ጥጋቡ አክለውም በክፍለ ከተማና በሁሉም ወረዳ ውስጥ የነበሩ የህዝብ አንገብጋቢ መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት መቻሉንና ለአብነት በወረዳ11 የትምህር ቤት ማስፋፊያ ግንባታን እንዲሁም በወረዳ5 እና 6 የመፀዳጃ እጥረትና ከፍተኛ የጎርፍ ስጋትን ለመቅረፍ የከተማና ክፍለ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ እንዲሁም የአከባቢውን ነዋሪዎች በማስተባበር በራስ አቅም ችግሩን ከመሠረቱ በመቅረፍ ለዘላቂነት መፍታት መቻሉን ገልጸዋል።

# # # # # # # # # # # # # #
መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

የ“FAME by Sheeraz” መስራች ሚስተር ሺራዝ ሐሰን እና ልዑካን ቡድናቸው የአዲስ አበባን የቱሪዝም መዳረሻዎች ጎበኙሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ. ም (ቱሪዝም ኮሚሽን)የ“FAME by Shee...
16/06/2026

የ“FAME by Sheeraz” መስራች ሚስተር ሺራዝ ሐሰን እና ልዑካን ቡድናቸው የአዲስ አበባን የቱሪዝም መዳረሻዎች ጎበኙ

ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ. ም (ቱሪዝም ኮሚሽን)

የ“FAME by Sheeraz” መስራች ሚስተር ሺራዝ ሐሰን እና ልዑካን ቡድናቸው በአዲስ አበባ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎችን እና የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱም የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችን የጎበኙ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች እንዲሁም የቱሪዝም መሠረተ ልማቶች ከተማዋ ተመራጭ የቱሪዝም ማዕከል እየሆነች ስለመምጣቷ ማረጋገጫ ነው ሲሉ ልዑካኑ ተናግረዋል::

“FAME by Sheeraz” ስመጥር የዲጂታል ሚዲያ እና የብራንዲንግ ድርጅት ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ ግለሰቦችን እና ተቋማት ጋር በቅርበት የሚሰራ ተቋም ነው::

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችን  የ90 ቀናት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ ላይ ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ተወያይተን ወደ ተግባር አስገብተናል። በድህረ ምርጫ በፍጥነት ፈታችንን ወ...
16/06/2026

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችን የ90 ቀናት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ ላይ ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ተወያይተን ወደ ተግባር አስገብተናል።

በድህረ ምርጫ በፍጥነት ፈታችንን ወደ ሥራ በመመለስ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገብ፣ ተከታታይና አዳዲስ ነገሮችን መተግበር፣ ህብረተሰባችን ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በላቀ ትጋትና ያለ እረፍት መፈጸም የሚያስችል እቅድ ይዘን በልዩ ትኩረት የምንፈፅም ይሆናል።

ከሰኔ 9 እስከ ጳጉሜ 5 በሚቆየው 90 ቀናት ውስጥ የምንፈፅማቸው ዋና ዋና ግቦች፤ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት፣ አገልግሎት የማሻሻል ስራን በማጠናከር የመሶብ አንድ ማእከል ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋት፣ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት ፣ የንግድ ስርዓቱን መግራት፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ መስራት፣ በአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት፣ የሰላም ግንባታ ስራዎች፣ የገቢ አሰባሰብ፣ ልመናንና ተረጂነትን መቀነስ፣ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብርን በተቀናጀ የህብረተሰብ ተሳትፎ መተግበር፣ የኢትዮዽያ ታምርት ንቅናቄን በአዲስ ቅኝት መምራት፣ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ፣ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችን በጥራት እና በተያዘላቸው የጊዜና በጀት ገደብ ማጠናቀቅ፣ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን ማጠናከር … ወዘተ ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈፀም ተዘጋጅተናል።

የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ በትኩረት በመስራት አዲሱ በጀት ዓመት ህዝባችንን ይበልጥ የምናገለግልበት፣ አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዟችንን የምናረጋግጥበት እንዲሆን ከእቅድ ዝግጅት እስከ ተግባር አፈፃፀም በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የምንፈፅም ይሆናል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። ‎ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል...
15/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። ‎ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጥሪ አቅርበዋል።

Prime Minister Abiy Ahmed and senior government officials today officially launched the 2026 Green Legacy Initiative planting cycle, calling on all Ethiopians, across every sector of society, to join the nationwide effort to plant this year’s target of 8 billion seedlings.

የዚህን ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማ...
15/06/2026

የዚህን ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን።

‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ!

Today, we officially launched this year’s Green Legacy Initiative. With a target of planting 8 billion seedlings this year, we are steadily advancing toward our larger set goal of 65 billion trees.

Join the movement and leave your green legacy for future generations!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡት የገበያ ማዕከላት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና ምርትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከቱ ይገኛሉ -   ምክትል ከንቲባ   አቶ ጃንጥራር አ...
15/06/2026

በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡት የገበያ ማዕከላት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና ምርትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከቱ ይገኛሉ - ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገበያ ማረጋጋት፣ የሕገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር እና የኢትዮጵያ ታምርት ግብረ-ኃይል ያለፉት ወራት አፈፃፀም እና የቀጣይ የክረምት ወራት የሥራ አካሄድን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ባለፉት ወራት ከምርት አቅርቦት፣ ከግብይት ሰንሰለት፣ ከዋጋ ቁጥጥር እና ከተያያዙ የግብይት ሂደቶች አንጻር የተከናወኑ ተግባራትን የሚያሳይ ዝርዝር የሥራ ሪፖርት ቀርቧል።

በቀረበው ሪፖርት ላይ በተለይም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እና ከዓለም አቀፍ ገበያ አንጻር የሀገር ውስጥ ገበያን ለመቆጣጠር በግብረ-ኃይሉ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸው ተመልክቷል።

በዚህም በከተማዋ ከተገነቡት ሰባቱም ሁለገብ የገበያ ማዕከላት በተጨማሪ፣ በ256 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ከግብርና እስከ ኢንዱስትሪ ምርቶች በጥራትና በስፋት ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ በሪፖርቱ ተገልጿል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ፤ የገበያ ማዕከላቱ በከተማ አስተዳደሩ በስፋት የለሙት ገበያን በዘላቂነት ለማረጋጋትና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማስተካከል ስለመሆኑ አንስተዋል።

የምርት አቅርቦትን ማሻሻልና ተደራሽነትን ማረጋገጥ ላይ ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ምክትል ከንቲባው፤ የግብይት ስርዓቱን ጤናማ ለማድረግ ሕገ-ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ሕጋዊ መስመር ለማምጣት በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በቀጣይ የክረምት ወራትም የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል፣ በአቅርቦትና በስርጭት ሂደት ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተመላክቷል።

AMN

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ:

Share