18/06/2026
በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ዙሪያ አገልጋዩንና ተገልጋዩን ፊት ለፊት ያገናኘ የእንጠያየቅ መድረክ ተካሄደ::
********************
ሰኔ 11-2018 ዓ.ም
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባዘጋጀው የእንጠያየቅ መድረክ በቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት፣ በስራና ክህሎት ጽ/ቤት፣ በንግድ ጽ/ቤት፣ በመሬት ልማት ጽ/ቤት፣ በግንባታ ፈቃድ ጽ/ቤት፣ በህብረት ስራ ጽ/ቤት እንዲሁም በሌሎች ተቋማት በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ አገልግሎት ሰጭውንና ተገልጋዩን ፊት ለፊት ያገናኘ የእንጠያየቅ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው ዘመኑን የሚመጥን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው መድረክ መዘጋጀቱ አስተዳደሩ በበለጠ ክፍተቶችን ለይቶ ለማስተካከል የሚያግዝ ነው ሲሉ ገልፀዋል::
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበራ ግርማ በበኩላቸው በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች እና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የእንጠያየቅ መድረክ መካሄዱ ለሁለቱም ወገን ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው መንግስት ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል::
መፈታት አለባቸው ተብለው በነዋሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የሁሉም ጽ/ቤት አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተው መድረኩ ተጠናቋል::
መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication