25/01/2022
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ንፋስ ስልክ ቅ/ጽ/ቤት በቀን 14/05/2014 የደንበኞች ፎረም ጠቅላላ አባላት የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡
የውይይቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች፡-
• የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም
• የአገልግሎት አሰጣጥ እና መልካም አስተዳደር ስራዎችን በተመለከተ እንዲሁም ከውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በአጠቃላይ በተነሱት አስተያየቶችና ጥቆማዎች ላይ የሚመለከታቸው የስራ ሀላፊዎች ማብራሪያና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የእለቱ የውይይት መድረክ በጥሩ ሁኔታ ተጠኗቋል፡፡