06/05/2024
እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን!
የትንሳኤ በዓል እየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች መከራ የተቀበለበት በመጨረሻም ሞትን ድል አድርጎ በመነሳት ሰላምን ያበሰረበት በመሆኑ በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በሃይማኖታዊ ስነስርዓቶች ታጅቦ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው፡፡
የመከራዉ ግዝፈት ትንሳኤውን እንዳላስቀረዉ ሁሉ የሀገራችንን ብልፅግናም ወቅታዊ ችግሮች እንደማያስቀሩት እዉን እንደሆነ ግልፅ ነዉና እንደተለመደው በዓሉን በኢትዮጵያዊ ጨዋነታችን በወንድማማችነትና እህትማማችነት እሳቤ ተደጋግፈን፣ የተቸገሩ ወገኖችን በመጠየቅ ያለንን እየተጋራን ማሳለፍ ይኖርብናል፡፡
በዓሉ የደስታ፣ የፍሰሃና የፍቅር እንዲሆንልን እመኛለሁ፤ መልካም የትንሳኤ በዓል!!
አቶ ሙስጠፋ ትኩ
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ