የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን - Addis Ababa Cooperative Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን - Addis Ababa Cooperative Commission

የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን - Addis Ababa Cooperative Commission Addis Ababa Cooperatives Commission manages, aids, controls, and organizes cooperatives. Addis Ababa Cooperative Agency organizes cooperatives in Addis Ababa.
(1)

‎የሰንበት ገበያዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል!!‎መስከረም 09/2019 ዓ.ም‎ማህበረሰቡ የዕለት ፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ በቅዳሜና እሁድ ገበያ አየተሰራ ይገኛል። ‎የኑሮ ውድነት...
19/09/2026

‎የሰንበት ገበያዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል!!

‎መስከረም 09/2019 ዓ.ም
‎ማህበረሰቡ የዕለት ፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ በቅዳሜና እሁድ ገበያ አየተሰራ ይገኛል።

የኑሮ ውድነትን ጫና ለመቀነስ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ እየቀረቡ ሲሆን፣ በተለይም የእሁድ ገበያው ለነዋሪዎች ተደራሽ በሆነ መልኩ በመዘጋጀቱ ብዙ ተጠቃሚዎችን እያስተናገዱ ይገኛሉ።

‎የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡም ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በማግኘት ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።
https://linktr.ee/addis_cooperative

በኮሪደር መሰረተ ልማት እርጅናዋ የተገፈፈ አዲስ አበባ:-
18/09/2026

በኮሪደር መሰረተ ልማት እርጅናዋ የተገፈፈ አዲስ አበባ:-

ለ2019 ዘመን መለወጫ በዓል በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በአቅርቦትና ገበያን በማረጋጋት የተሠሩ ስኬታማ ስራዎችን በቀጣይ በሚከበሩ በመስቀልና በእሬቻ በዓላትም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በማህ...
18/09/2026

ለ2019 ዘመን መለወጫ በዓል በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በአቅርቦትና ገበያን በማረጋጋት የተሠሩ ስኬታማ ስራዎችን በቀጣይ በሚከበሩ በመስቀልና በእሬቻ በዓላትም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በማህበራቱ በኩል ሰፊ ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደሚገኙ የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን አስታወቀ።

መስከረም 08/2018 ዓ ም
በዘመን መለወጫ በዓል በመዲናዋ በሚገኙ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት የተሠሩ የገበያ ማረጋጋት ስራዎች ለመጪዎቹ የመስቀልና የእሬቻ በዓላት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተገልጿል።

ኮሚሽኑ በማህበራቱ በኩል ለዘመን መለወጫ በአል የተከወኑ ስኬታማ የአቅርቦት ተግባራት በመስቀልና በእሬቻ በዓላትም በቂ የፍጆታ አቅርቦት እነዲኖር በመድረግ ገበያው ተረጋግቶ እንዲቀጥል ለማድረግ በመዲናዋ ከሚገኙ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ዩንየን ስራአስኪያጆችና የቦርድ አመራሮች እንዲሁም የክፍለ ከተማ የግብይት ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱም የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮምሽን ምክትል ኮሚሽነር ሀብተየስ ዲሮ እንደገለጹት በ2019 የዘመን መለወጫ በዓል በመዲናዋ በሚገኙ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል የተሠሩ የገበያ ማረጋጋት ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ለመጪዎች የመስቀልና የእሬቻ በዓላት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል።

ከመስቀልና ከእሬቻ በዓላት ጋር ተያይዞ በመዲናዋ የፍጆታ ምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ የአቅርቦት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልፀው፤ በቀጣይም ተጨማሪ ምርቶች ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፃዋል።

በዓላቱን በማስመልከት በሰንበት ገበያዎች እና በመደበኛ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ሱቆች አማካኝነት ህብረተሰቡ በቂ አቅርቦት እንዲያገኝ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።
https://linktr.ee/addis_cooperative

በትጋትና ጥረት የተወለደ አዲስ የማንሰራራት ንጋት!አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ጽዱ፣ ተወዳዳሪና ዘመናዊ እንድትሆን ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ አቅዶ በሰራው ሥራ ዘርፈ ብዙ ለውጦች ተመዝግበ...
18/09/2026

በትጋትና ጥረት የተወለደ አዲስ የማንሰራራት ንጋት!
አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ጽዱ፣ ተወዳዳሪና ዘመናዊ እንድትሆን ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ አቅዶ በሰራው ሥራ ዘርፈ ብዙ ለውጦች ተመዝግበዋል።

በከተማዋ የተገነቡት ሜጋ ፕሮጀክቶችና የልማት ኢኒሼቲቮች የህዝቡን የልማትና የተጠቃሚነት ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር ከተማዋ እንድታንሰራራ እና ለሌሎች ከተሞች የብልጽግና ፋና ወጊ እንድትሆን አስችሏታል።

ባለፉት አምስት ዓመታት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ከ60 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት የገቡ ሲሆን በ2018 ዓ.ም ብቻ ከ20ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ችለዋል። ይህ በ24/7 የሥራ ባህል የተተገበረው የፕሮጀክት አፈጻጸም ለከተማዋ ማንሰራራት ጉልህ ድርሻ ተጫውቷል።

በከተማዋ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ለከተማዋ ዘመናዊነትን ከማላበስ በዘለለ ነዋሪው ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲንቀሳቀስ ምቹ መደላድል ፈጥረዋል። የመንገድ ኔትዎርክ ሽፋንና ጥራትን በማሳደግ የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዲሳለጥ አድርጓል።

በከተማዋ ምንም ያልነበሩ የትራንስፖርት ቴርሚናሎችና መኪና ማቆሚያዎች በበርካታ ቦታዎች ተገንብተው ህብረተሰቡን ከእንግልትና ከአደጋ መታደግ ችለዋል።

የነዋሪዎችን አስከፊ አኗኗር ለማሻሻል ታቅዶ የተተገበረው የከተማ ማደስ ሥራም አዲስ አበባ ፈጥና እንድታንሰራራና ባለፉት ጊዜያት “አይቻልም” ተብሎ የተዘጋውን አዲስ አበባን የመለወጥ ውጥን ወደ ተግባር እንዲቀየር አስችሏል። ከተማዋ ለኑሮ ምቹ፣ ለጤና ተስማሚ እንድትሆን ብክለትን ለመቀነስ በተሰራው የአረንጓዴ ልማት ሥራ የከተማዋ የአረንጓዴ ሽፋን ከ2.8 በመቶ ወደ 24 በመቶ አድጓል።

በተጨማሪ ለከተማዋ ጽዳት በተሰጠው ትኩረት አዲስ አበባ ከ10 ጽዱ የአፍሪካ ከተሞች አንዷ መሆን ችላለች።

በአዲስ አበባ የተመዘገቡ የመሰረተ ልማት ስኬቶች ለነዋሪዎቿ ዘመናዊ አገልግሎት ከመስጠታቸው በተጨማሪ ከተማዋን ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ ቱሪስት መዳረሻነት እንድትሸጋገር አስችሏታል።

በኮንፍረንስ ቱሪዝም በ2018 ዓ.ም. ብቻ ከ220 በላይ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ስብሰባዎችን በማስተናገድ አዲስ አበባ ማንሰራራቷን አስመስክራለች።

ኮሚሽኑ በሰራቸው የአስቸኳይ ጊዜ ሙስና መከላከል የህብረት ስራ ማህበራትን ሀብት ማዳን ተችሏል፡- ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድመስከረም 5/2018 ዓ.ምየአዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን ሙስናን ለ...
17/09/2026

ኮሚሽኑ በሰራቸው የአስቸኳይ ጊዜ ሙስና መከላከል የህብረት ስራ ማህበራትን ሀብት ማዳን ተችሏል፡- ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድ

መስከረም 5/2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን ሙስናን ለመከላከልና ብልሹ አሠራሮችን ለማስወገድ ባከናወናቸው የአስቸኳይና ተከታታይ የመከላከል ሥራዎች የህብረት ስራ ማህበራትን ሀብት ከኪሳራና ከምዝበራ መታደግ መቻሉን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድ ገልጸዋል።

እንደ ኮሚሽነሯ ገለጻ በተለይም ኮሚሽኑ የህብረት ስራ ማህበራት ወደ ሪፎርም በማስገባት አገልግሎት አሰጣጣቸውን ከከተማዋ ሁሉን አቀፍ የለውጥ ጎዳና ጋር የሚመጋገቡ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርቷል ያሉ ሲሆን፤ ይህንን ለውጥ ሊያመክን የሚችሉ ሙሰናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።

በተጨማሪም ኮሚሽኑ በተቋም ግንባታ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በተጠያቂነት እና በሞራል እሴቶች ግንባታ ዙሪያ ውጤታማ ሥራዎችን ማከናወኑን አንስተዋል።

በተቋሙ በድኀረ ሪፎርም ውስጥ ከፍተኛ እንቅፋት ሆነው ከቆዩት ችግሮች መካከል ሌብነትና ብልሹ አሠራር ዋነኛዎቹ ሲሆኑ፣ በተወሰዱ የሪፎርም፣ የመከላከል እርምጃዎችና የቁጥጥር ሥርዓቶች ምክንያት ተቋሙ ያጋጥሙት የነበሩ ስጋቶች እየቀነሱ መምጣታቸው ተስፋ ሰጪ ውጤት መሆኑን ጠቁመዋል።

ኮሚሽነሯ በንግግራቸው በተቋሙ ውስጥ በሥነ ምግባር እና በተገቢ የሥራ አፈፃፀም አርአያ ለሆኑ ባለሙያዎች እውቅና መሰጠቱ የተቋሙን የተጠያቂነትና የታማኝነት ባህል ለማጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል።

በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመትም ሙስናን የመከላከል ሥራ የአንድ ክፍል ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም አመራርና ሠራተኛ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን በማሳሰብ፣ ሁሉም በየደረጃው የድርሻውን በመወጣት ሙስና ለተቋሙ ስጋት እንዳይሆን በትጋት መሥራት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በተቋሙ ውስጥ ግልፅነትን፣ ተጠያቂነትን እና መልካም አስተዳደርን የሚያጠናክሩ ተጨማሪ የሪፎርም እና የመከላከል ሥራዎች በትኩረት እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
https://linktr.ee/addis_cooperative

ለዓለም ከተሞች ምሳሌ የሆነች ከተማ - አዲስ አበባ አዲስ አበባ  ዝቅተኛ የአደጋ ተጋላጭ የሆነች፥ ደህንነቷ የተጠበቀና የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም ከተማ በሚል  ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለ...
17/09/2026

ለዓለም ከተሞች ምሳሌ የሆነች ከተማ - አዲስ አበባ

አዲስ አበባ ዝቅተኛ የአደጋ ተጋላጭ የሆነች፥ ደህንነቷ የተጠበቀና የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም ከተማ በሚል ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም ሁለተኛ ከተማ ሆና ተቀምጣለች።

የጂኦስፓሻል ኩባንያ አልፋ ጂኦ በዋነኝነት በሶስት መመዘኛዎች የአዲስ አበባ ከተማን የመዘነ ሲሆን አካላዊ የአየር ንብረት ለውጥ፥ አደጋ ተጋላጭነት፤ሊገጥሙ ለሚችሉ አደጋዎች አስተዳደር እና ፖሊሲ ምላሽ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ የማላመድ እርምጃዎች ላይ በማተኮር ነው ምዘናው የተካሄደው።

በእነዚህ መመዘኛዎች አዲስ አበባ ከተማ ከ72 ከተሞች ጋር ተወዳድራ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ለዓለም ከተሞች ምሳሌ ሆናለች፡፡

በዓለም የስልጣኔ ቁንጮ የተባሉትን እንደነ ፓሪስ እና ለንደን የመሳሰሉት ከተሞች አስከትላ በዓለም ላይ የአየር ንብረት ተጋላጭነት የምትቋቋም ከተማ በሚል ከአሜሪካዋ ቺካጎ ቀጥሎ በቁንጮ ላይ የተቀመጠችው አዲስ አበባ በኮሪደር እና የመንዝ ዳርቻ ልማት ያከናወነችው ስራዎች እና የዘረጋቻቸው ዘመናዊ መሰረተ ልማቶች በዚህ ደረጃ እንድትቀመጥ አስችሏታል፡፡

አዲስ አበባ የዓለም ቀልብ የምትስብ ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ ብቻ አይደለችም ከምቹነት ባለፈ የአደጋ ተጋላጭነቷ ዝቅተኛ የሆነች፥ ደህንነቷ የተጠበቀ የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም ከተማ ናት ፡፡

በዓለምአቀፉ ጂኦስፓሻል ኩባንያ አልፋ ጂኦ (Alpha Geo) ለአዲስ አበባ የተሰጠው ማረጋገጫ ለፖሊሲ አውጪዎች፤ ኢንቬስተሮች እና የመሰረተ ልማት ባለቤቶች አዲስ አበባ ከተማ በተመለከተ የውሳኔ ሀሳቦች ለመስጠት እጅጉን ጠቃሚ ነው፡፡

በዓለም ላይ የሚገኙ ከተሞች ፈጣን የህዝብ ቁጥር ጭማሪን እያስተናገዱ ሲሆን ይህ የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት ማደግ አዳዲስ ፍላጎቶችን ይዞ የሚመጣ ሲሆን በዚያው መጠን ደግሞ ከተሞች ለሚፈጠሩ አዳዲስ ፍላጎቶች ፈጣን ምላሽ መስጠት ይገባቸዋል፡፡

በዚህ መርህ የተቃኘው የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ እና የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ በዓለማቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት እያደረገ ሲሆን በ8 ወንዞች 59 ኪሎ ሚትር ርዝመት ያለው የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ለበርካታ ችግሮች ሁሉን አቀፍ ምላሽ የሰጠ ነው፡፡

ወንዞችን ማልማት ከመዋብ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት፤ የወንዞችን መበከል ይከላከላል፣ የጎርፍ አደጋን ይቀንሳል፣ የከተማዋን የሙቀት መጠን ይቀንሳል፥ ነዋሪዎች ንጹህ አየር የሚያገኙበትን፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን እና አዕምሮአቸውን የሚያድሱበትን ዕድል ይፈጥራል።

ለ2019 አዲስ ዓመት የኑሮ ውድነትንና ገበያን ለማረጋጋት የተሠራው ሥራ ስኬታማ ነው፡- ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድመስከረም 5/2019 ዓ.ምየአዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን ለ2019 ዓ.ም. የ...
16/09/2026

ለ2019 አዲስ ዓመት የኑሮ ውድነትንና ገበያን ለማረጋጋት የተሠራው ሥራ ስኬታማ ነው፡- ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድ

መስከረም 5/2019 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን ለ2019 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ዝግጅት የኑሮ ውድነትን ለመቀነስና ገበያን ለማረጋጋት ከሸማች ኀብረት ሥራ ማህበራት፣ አምራቾች፣ አቅራቢዎችና አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ያከናወነው ሥራ ስኬታማ መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ሽታዬ መሀመድ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሯ እንደገለጹት ለበዓሉ የምርት አቅርቦት በቂና ተደራሽ እንዲሆን የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች፣ የምግብ ዘይትና ሌሎች መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች በሸማች ኀብረት ሥራ ማህበራት አማካኝነት በቂ መጠን ለከተማዋ ነዋሪዎች ቀርበዋል።

በተለይም የልኳንዳ ሥጋ ቤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ሥጋ በማቅረብ ለገበያ መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ አንድ ኪሎ ግራም ሥጋ በ1200 ብር በመሸጥ ነዋሪዎች የበዓል ፍላጎታቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያሟሉ አስችለዋል ብለዋል።

በዚህ ሂደት ሸማች ኀብረት ሥራ ማህበራት ከአምራቾች እና ከአቅራቢዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር በመፍጠር የንግድ ሰንሰለቱን በማሳጠር ምርቶች ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲደርሱ ማድረጋቸው ተገልጿል። ይህም ሰው ሠራሽ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከልና የገበያ መረጋጋትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና ተጫውቷል።

ኮሚሽነር ሽታዬ መሀመድ በመጨረሻ እንዳሉት፣ ኀብረት ሥራ ማህበራት በበዓላት ወቅት ብቻ ሳይሆን ዓመቱን ሙሉ የምርት አቅርቦትን በማሳደግ፣ የኑሮ ውድነትን በመቀነስና ገበያን በማረጋጋት ያላቸውን ሚና የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እየሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን በ2019 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ወቅት በተለያዩ የሽያጭ ማዕከላት፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ባዛሮችና የሠንበት ገበያዎች አማካኝነት የፍጆታ ምርቶችን ለነዋሪዎች በቂና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የገበያ መረጋጋት እንዲፈጠር አስተዋጽኦ አድርጓል።

በቀጣይ በሚከበሩ የመሰቀልና የኢሬቻ በአላትም በአቅርቦቱ ረገድ ከወዲሁ በእቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝም ኮሚሽነሯ ጠቁመዋለ።
https://linktr.ee/addis_cooperative

በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎቻችን አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን እንመኛለን! ‎‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ በመሆኑ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጅማሮን ተከትሎ፤...
16/09/2026

በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎቻችን አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን እንመኛለን!

‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ በመሆኑ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጅማሮን ተከትሎ፤ እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን እንዲከታተል፣ ለጥሩ ውጤት በጽናት እንዲተጋ፣ እንዲሁም የሀገራችንን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባ አበረታታለሁ።

‎ ዛሬ እየተገበርነው ያለው በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው፣ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ እንደመሆናችሁ መጠን፣ የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የእናንተ ቁርጠኝነት መሠረት እንደሆነ ሙሉ እምነቴ ነው።

‎ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖቻችን ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ ነው። ተማሪዎቻችንን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን ቀጥሉበት ስል በትህትና አሳስባለው።

‎በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ለምትገኙ ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን በመጪው ቀናት የሚከበሩ የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት አከባበርን በተመለከተ ከሰራተኞቹ ጋር ውይይት አካሄደ።መስከረም 04/2019 ዓ.ምኮሚሽኑ የጳጉሜን ...
15/09/2026

የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን በመጪው ቀናት የሚከበሩ የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት አከባበርን በተመለከተ ከሰራተኞቹ ጋር ውይይት አካሄደ።

መስከረም 04/2019 ዓ.ም
ኮሚሽኑ የጳጉሜን ቀናትን አከባበር አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የሚከበሩት የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት መነሻ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።

በውይይት መድረኩ እንደተገለጸው የመስቀልና የኢሬቻ በአላት የሀገራችን ብዝሀ ማንነት የሚያንፀባርቁ ሲሆኑ፤ እነዚህ በአላት ትውፊታቸውና እሴታቸው በመጠበቅ ለአለም ማስተዋወቅ ይገባል የተባለ ሲሆን፤በአላቱ ለከተማዋ ቱሪዝም ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸውም ተመላክቷል።

በዓላቶቹ ሰፊ ህዝብ ወጥቶ የሚያከብራቸው በመሆኑ አንድነታችንን ፣ ህብረብሄራዊ እሴቶቻችን ለማጎልበትም ትልቅ እድል የሚፈጥሩ መሆናቸውም ተመልክቷል።

በአላቶቹ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበር የሁሉም ባለድርሻ አካል ሚና ከፍተኛ መሆን እንደሚገባው ተገልጿል።

የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት መንፈሳዊና ባህላዊ እሴቶቻቸውን በጠበቀ መልኩ በማክበር ለህዝባችን ህብረ ብሔራዊ አብሮነት መጠናከር እና ለሀገር ግንባታ ሚና እንዳለው በመገንዘብ ሰራተኛው የራሱን አበርክቶ ሊያደርግ እንደሚገባም በመድረኩ ተገልጿል።

በዓላቱ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ሁሉ ሀብትና ቅርስ እንደሆኑ እና የበዓላቶቹን እሴቶች በጠበቀ መልኩ በደመቀና ባሸበረቀ መንገድ ማክበር እንደሚገባም ተገልጿል።

በመጨረሻም የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን ፣የወንድማማችነት/እህትማማችነት እሴቶች ባጎለበተ መልኩ መከበሩ የተገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይ የሚከበሩ የመስቀልና የኢሬቻ በአላት ትውፊታቸው ተጠብቆ እንዲከበሩ ሁሉም ሚናውን መወጣት እንዳለበትም በውይይቱ ተመላክቷል።
https://linktr.ee/addis_cooperative

የዛሬን ኑሮ እያሻሻሉ የነገን ትውልድ የመገንባት ስትራቴጂ በአዲስ አበባየኢትዮጵያ የልብ ምት የሆነችው አዲስ አበባ ባለፉት አምስት ዓመታት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባሻገር፣ የነዋሪዎችን የ...
15/09/2026

የዛሬን ኑሮ እያሻሻሉ የነገን ትውልድ የመገንባት ስትራቴጂ በአዲስ አበባ

የኢትዮጵያ የልብ ምት የሆነችው አዲስ አበባ ባለፉት አምስት ዓመታት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባሻገር፣ የነዋሪዎችን የኑሮ ጥራት እና አስተሳሰብ በማሻሻል ወደ አዲስ የብልጽግና ምዕራፍ እየተሸጋገረች ትገኛለች።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተደጋጋሚ እንደሚያነሱት ከተማዋ የምትከተለው የልማት ስትራቴጂ ትውልድ ግንባታን ማጠንጠኛ ያደረገ "ሰው-ተኮር" ተግባር ነው።

የዚህ የለውጥ ጉዞ መሠረት አስተሳሰብን መለወጥ በመሆኑ ይህንኑ መርህ ከትምህርት ቤቶች ጀምሮ በተግባር እየተረጎሙት ይገኛሉ።

"ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ስንገነባ ልጆቻችን የሚረሱባት ከተማ ልትሆን አይገባም" በሚል ጽኑ አንድ ሚሊዮን ገደማ ለሚሆኑ ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ የምገባ መርሐ ግብር መተግበሩ የዚሁ ስኬት ማሳያ ነው።

ከዚህ ቀደም በከተማዋ የመንግሥት የሕጻናት መዋያ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ያልነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸውን ከ1 ሺህ 100 በላይ ማድረስ ተችሏል።

በተጨማሪም የሕጻናት መጫወቻ ስፍራዎች ከ20 ወደ 5 ሺህ 500 ከፍ መደረጋቸው አስተዳደሩ ለትውልድ ግንባታ የሰጠውን ልዩ ትኩረት በጉልህ ያሳያል።

ይህ ሰው-ተኮር የልማት አቅጣጫ በትምህርት ዘርፍ ብቻ የተገደበ አይደለም። አቅመ ደካሞችን ታሳቢ ያደረጉ የቤት እድሳት እና ግንባታ ፕሮጀክቶች፣ ለነዋሪው ምቹ የሆኑ ዘመናዊ መዝናኛ ስፍራዎች እና ፓርኮች ግንባታ፣ እንዲሁም የጤና ተቋማት ማስፋፊያ ስራዎች የዚሁ ትውልድን የመቅረጽ እና የዜጎችን ክብር ከፍ የማድረግ የተቀናጀ ራዕይ አካል ናቸው።

አስተዳደሩ በቀጣይ ዓመታት የትምህርት ዘርፉን ይበልጥ ለማዘመን ተደራሽነትን፣ ጥራትን እና ፍትሃዊነትን በዋና ምሰሶነት ነድፎ እየሠራ ነው።

ከንቲባዋ እንደገለጹት የስኬት መለኪያው በፈተና የሚያልፉ ተማሪዎች ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ የተማሪዎችን እውነተኛ "ልቀት" ማረጋገጥ ነው።

ዘንድሮ በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የተመዘገበው የ96 በመቶ የማለፍ ምጣኔ እጅግ አበረታች ቢሆንም፣ የከተማ አስተዳደሩ ዋነኛ ግብ ከዚህ የዘለለ መሠረታዊ እና ዘላቂ የጥራት ለውጥ ማምጣት ነው።

ትምህርት ቤቶችን ከአዋኪ ድርጊቶች ሙሉ ለሙሉ ነጻ በማድረግ ጤናማ የመማር ማስተማር አካባቢን በመፍጠር ረገድ የተከናወነው ተግባር ሌላው ስኬት ነው።

ተማሪዎች በስጋት ሳይሆን በተረጋጋ መንፈስ እንዲማሩ የትምህርት ቁሳቁስና የደንብ ልብስ አቅርቦትን በነጻ ማሟላት ተችሏል።

በተጨማሪም ተማሪዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚያሳልፉትን ጊዜ በመገደብ ትኩረታቸውን በትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያደርጉ ከወላጆች ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው።

ከዚህ ጎን ለጎንም ያለ መምህራን ብቃት የታለመውን ልቀት ማምጣት ስለማይቻል የመምህራንን አቅም መገንባት እና ጥቅማጥቅሞችን ማሻሻል ቀዳሚ ተግባር ሆኖ በመተግበር ላይ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያካሄደ ያለው የለውጥ ጉዞ በመንግስትና በሕዝብ መካከል በተፈጠረ ጠንካራ የጋራ መተማመን ላይ የተመሠረተ ነው።

ከተማዋ በትምህርት፣ በጤና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና መሰረተ ልማት ዝርጋታ እያስመዘገበች ያለው ስኬት በቀጣይ ዓመታት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥርና በአፍሪካ ደረጃም የከተማነት ተምሳሌት ሆኖ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

Address

5 Kilo Near Kidiste Mariam Church
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:30
Friday 08:30 - 11:30
13:30 - 17:30

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን - Addis Ababa Cooperative Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን - Addis Ababa Cooperative Commission:

Shortcuts

Share