19/08/2021
ሆያሆዬ ሆ!ሆያሆዬ ሆ!እንኳን ለቡሄ በዓል በሰላም አደረሳችሁ/ሰን።
አዲስ አበባ፣ለሚ ኩራ፣ወረዳ 13(ነሃሴ 13/2013ዓ.ም)በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 13 አስተዳድር ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት አዘጋጅነት የ2013ዓ.ም የቡሄን በዓል በአስተዳድሩ የወጣቶች ማዕከል አዳራሽ የአስተዳድሩ ሠራተኞችና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸዉ አካላት በተገኙበት ደማቅ ኘሮግራም የተካሄደ ሲሆን በዚህ ኘሮግራም የተለያዩ ባህላዊ ይዘት ያላቸዉ የቡሄ ጭፈራ ሆያ ሆዬ፤የስነጹፍና የሙዚቃ ድግስ ኘሮግራሙን ያደመቁና የበዓሉን በዓላዊ ይዘት የሚዘክሩ ዝግጅቶች ለታዳሚያን ቀርበዋል።እንዲሁም በዓሉን የሚገልጹ የተለያዩ በራሪ ወረቀቶችና ብሮሸሮች ለታዳሚያን ተሰራጭተዋል።