የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት

የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር  ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት ይህ ገጽ በዓለም ከተማ ከተማ አስ/ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ገፅ ነው
(1)

🌧️ በመሬ አለም ከተማ በረዶ በሽንኩርትና የተለያዩ የጓሮ አትክልት ላይ ጉዳት አደረሰ።መስከረም 6/2019 ዓ.ምበመሬ አለም ከተማ በመስከረም 6/2019 ዓ.ም በጣለው ዝናብ ተከትሎ የተከሰተ...
17/09/2026

🌧️ በመሬ አለም ከተማ በረዶ በሽንኩርትና የተለያዩ የጓሮ አትክልት ላይ ጉዳት አደረሰ።

መስከረም 6/2019 ዓ.ም

በመሬ አለም ከተማ በመስከረም 6/2019 ዓ.ም በጣለው ዝናብ ተከትሎ የተከሰተው በረዶ በከተማዋ 03 ቀበሌ ኪዳነምህረት አካባቢ በሚገኙ የሽንኩርትና የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ።

በተለይም በአካባቢው የሚገኙ የሽንኩርት አዝመራዎች በበረዶው መጎዳታቸውና የአርሶ አደሩን የምርት ተስፋ መቀነሱ ታውቋል።

🌱 በረዶው በአዝመራው ላይ ያደረሰውን ጉዳት በመለየት በቀጣይ የሚወሰዱ የጉዳት ምርመራና የድጋፍ ርምጃዎች እንደሚኖሩ ይጠበቃል።

ተማሪ ደሞዜ ፈቃዱን ለመደገፍ በከንቲባ ተወካይ አስተባባሪነት  ማህበረሰቡ እና የመንግስት ሰራተኞች ድጋፍ አደረጉ።‎‎መስከረም 06/2019 ዓ/ም‎‎  የመማር አቅሟ ለሌላት የመሀል ሜዳ ሁለተ...
16/09/2026

ተማሪ ደሞዜ ፈቃዱን ለመደገፍ በከንቲባ ተወካይ አስተባባሪነት ማህበረሰቡ እና የመንግስት ሰራተኞች ድጋፍ አደረጉ።

‎መስከረም 06/2019 ዓ/ም

‎ የመማር አቅሟ ለሌላት የመሀል ሜዳ ሁለተኛ ዓመት ተማሪ የሆነች ደሞዜ ፈቃዱ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላትና የመንግስት ሰራተኞች በእናቷ አማካኝነት ድጋፍ ተደረገላት።

‎ ድጋፉ ከአለም ከተማ ማህበረሰብና ከመንግስት ሰራተኞች ሰውን መርዳት ሰው መሆን በቂነው በማለት በማሰባሰብ ሰባት ሺህ አራት መቶ ብር (7,400 ብር)፣ አንድ የደስታ ወረቀት እና አስር እስክሪብቶ ለተማሪዋ እናት አልማዝ ሀብታሙ ድጋፉን አበርክተዋል።

‎ በተጨማሪም የአለም ከተማ ትራንስፖርት ጽ/ቤት ተማሪዋ ከአለም ከተማ እስከ ደብረ ብርሃን በነፃ ትራንስፖርት እንድትጓዝ ድጋፍ አድርጓል።

‎ ይህ ድጋፍ ተማሪዋ ትምህርቷን እንድትቀጥል ከማህበረሰቡ የተደረገ የትብብርና የመረዳዳት ተግባር መሆኑ ተገልጿል።

‎ የተማሪዋ ትምህርት ቀጣይነት እንዲኖረው እና በትምህርት ጉዞዋ የሚያጋጥሟትን ችግሮች ለማቃለል እንድትችል ተማሪ ደሞዜ ፈቃዱን መርዳት የምትፈልጉ የማህበረሰብ ክፍሎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000397847342 በማስገባት መደገፍ ትችላላችሁ ።

‎ "ሰውን መረዳት ሰው መሆን በቂ ነው "

🏗️ የአለም ከተማ መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የአገልግሎት አሰጣጥና ወቅታዊ ሥራዎች ግምገማ አካሄደ።መስከረም 5/2019 ዓ/ም  በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የአገ...
15/09/2026

🏗️ የአለም ከተማ መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የአገልግሎት አሰጣጥና ወቅታዊ ሥራዎች ግምገማ አካሄደ።

መስከረም 5/2019 ዓ/ም

በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የአገልግሎት አሰጣጡንና ወቅታዊ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ከጠቅላላ ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር የግምገማና ውይይት መድረክ አካሄደ።

በግምገማው መድረክ የጽ/ቤቱ አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም፣ ለሕብረተሰቡ የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ በወቅቱ እየተከናወኑ ያሉ የሚጠገኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች እና በሥራ አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ ጎኖችና ተግዳሮቶች በስፋት ተገምግመዋል።

የዓለም ከተማ ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የጽ/ቤቱ ተወካይ አቶ አረሳውም አጥላባቸው መድረኩን የመሩ ሲሆን፣ ከጽ/ቤቱ አጠቃላይ ሠራተኞች ጋር በወቅታዊ የሥራ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

@ በውይይቱም በተለይ አገልግሎቶችን በቀልጣፋ፣ በጥራትና በተጠያቂነት ለሕብረተሰቡ ማቅረብ፣ የሥራ ቅንጅትን ማጠናከርና በወቅቱ የተያዙ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በተገቢው አፈጻጸም ማጠናቀቅ ላይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

💡 የመሠረተ ልማት ሥራዎች የከተማዋን የልማት ጉዞ ለማፋጠንና የነዋሪዎችን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግ ወሳኝ በመሆናቸው፣ ሥራዎችን በቅንጅትና በተጠያቂነት ማከናወን እንደሚገባ ተገልጿል።

በዉይይቱም ተሳታፊወች ሀሳብ አስተያየት አንስተዉ የመድረክ መሪዉ በቂመልስ ሰጥተዉበት የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጦ ዉይይት ተጠናቋል።

‎በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸው ተገለፀ‎‎የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ...
15/09/2026

‎በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸው ተገለፀ

‎የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ኦረንቴሽን ውይይት በደብረብርሃን ከተማ እያካሔዱ ነው።

‎ሁለተኛ ቀኑን በያዘው ውይይት የ2018 በጀት ዓመት የዘርፎች የተግባራት አፈፃፀም ግምገማ እየተካሔደ ነው።

‎የመንግስት ተግባራት ሪፖርትን ያቀረቡት የዞኑ ፕላንና ልማት ኃላፊ አቶ ኃይሌ የሺጥላ እንደገለፁት በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት በርካታ ተግባራት በስኬት መፈፀማቸውን ገልፀዋል።

‎በከተማና በገጠር ለስራ ዕድል ፈጠራ በተሰጠው ትኩረት ከ124 ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በቋሚና በጊዜያዊነት የስራ እድል መፈጠሩን ገልፀዋል።

‎በዞኑ የሚገኙ ማዕድናትን ወደ ጥቅም በማዋልና ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በግብዓትነት በማቅረብ እንዲሁም የማዕድን ሀብት የሚገኙበትን ቦታዎች ጥናት አድርጎ በመለየት ረገድ በበጀት አመቱ አበረታች ስራ መፈፀሙ ተመላክቷል።

‎በዘመናዊ ግብርና በመካናይዜሽን፣ በመስኖ እና በአትክልት ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም የምርት አሰባሰብን በማዘመን ረገድ አዳጊ ውጤት ተመዝግቧል ተብሏል።

‎በቱሪዝም ዘርፉ መሻሻል የታየበት ተግባር ያለ ቢሆንም የሠላም ሁኔታውን ይበልጥ አስተማማኝ ማድረግ፣ የመዳረሻዎችን ምቹነት ማሳደግና የመሠረተ ልማት ተደራሽነት ስራ የሚጠይቅ መሆኑ በሪፖርቱ ተገልጿል።

‎በትምህርት በኩል የገጠመውን ችግር ለመፍታት የተደረገው ጥረት አበረታች ቢሆንም ይሔ ዘርፍ በጣም የተጎዳ ስለሆነ ከተማሪ ምዝገባ፣ ከወንበር ማገናኘትና ትምህርት ማስጀመር ላይ ተገቢው ትኩረት ከአሁኑ ሊሰጠው ይገባል።

‎በቀጣይ የገቢ አሰባሰብ ስራ ላይ ትኩረት በመስጠት የህዝብን የመልማት ጥያቄዎች መመለስ የሚያስችል ትኩረት እንደሚያስፈልግ ሪፖርቱን ያቀረቡት አቶ ኃይሌ የሺጥላ በሪፖርታቸው አፅዕኖት ሰጥተዋል።

📌 በዓለም ከተማ የሳምንታዊ የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች ግምገማ ተካሄደ።📅 መስከረም 5/2018 ዓ.ምበዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የሳምንቱን የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም ለመገምገ...
15/09/2026

📌 በዓለም ከተማ የሳምንታዊ የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች ግምገማ ተካሄደ።

📅 መስከረም 5/2018 ዓ.ም

በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የሳምንቱን የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም ለመገምገም፣ የተገኙ ውጤቶችን ለማጠናከርና ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የሥራ ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

በግምገማ መድረኩ የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና የሦስቱም ቀበሌዎች አመራሮች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የሰላም፣ ሕዝብ ደህንነት ጽ/ቤት ኃላፊና የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ ከንቲባ አቶ ጉርምስ ጫነያሌው እና የከተማ ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊና የከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ተወካይ ዋና ሳጅን ዘመድኩን አይፎክር የሳምንቱን የሥራ አፈጻጸም ገምግመዋል።

በዚህም የሳምንቱ የሥራ አፈጻጸም በመገምገም፤ የተከናወኑ ሥራዎች፣ የታዩ ጥንካሬዎች፣ ክፍተቶችና በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገባቸዉን ተግባራት በስፋት ተነስተዋል።

💡 በተለይም የተገኙ ውጤቶችን ማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በአፋጣኝ ማስተካከል፣ የቀጣይ ሳምንት ተግባራትን በግልጽ አቅጣጫና በተሻለ አፈጻጸም ለመፈጸም ተገቢው አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በተቀናጀ አሠራርና በተጠናከረ አፈጻጸም የቀጣይ ሥራዎችን ለማሳካት በሚያስችል መልኩ ውይይቱ ተጠናቋል።

📚🎓  የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  በአለም ከተማ በሚገኙ አጠቃላይ የትምህርት ቤቶች የትምህርት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ።መስከረም 5/2019 ዓ.ም‎  በአለም ከተማ ከተማ አስተዳ...
15/09/2026

📚🎓 የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአለም ከተማ በሚገኙ አጠቃላይ የትምህርት ቤቶች የትምህርት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ።

መስከረም 5/2019 ዓ.ም

‎ በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባሉ አጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የአዲሱን የትምህርት ዘመን በይፋ ለማስጀመር የችቦ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

‎በመርሀ ግብሩ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር፣ ምክትል ኃላፊዎችና ሁሉም መምህራን በመገኘት የአዲሱን የትምህርት ዘመን በተስፋ፣ በትጋትና በተማሪዎች ላይ የተመሠረተ አገልግሎት ለማስጀመር ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

‎ ችቦ ማብራቱ የአዲሱን የትምህርት ዘመን በተስፋና በብሩህ እይታ ለመጀመር የሚያመለክት ሲሆን፣ ችቦው እውቀትን፣ ብርሃንን፣ ተስፋን እና የትውልድ ለውጥን የሚወክል መልዕክት ተላልፏል። መምህራንም የተማሪዎችን እውቀት፣ ክህሎት፣ ሥነ-ምግባርና የተሟላ ችሎታ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

‎በዕለቱ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ባደረጉት ንግግር፣ የአዲሱ የትምህርት ዘመን ዋና ትኩረት ተማሪዎች ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ፣ መምህራንም ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ ማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል።

‎ ትምህርት ቤቱ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ለማሻሻልና ተማሪዎች በእውቀትና በሥነ-ምግባር የበቁ ዜጎች እንዲሆኑ ለማድረግ በትብብር እንደሚሠራም ጠቁመዋል።

‎መምህራን በበኩላቸው የትምህርት ዘመኑን በአዲስ የሥራ መንፈስ ለመጀመር ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው፣
ተማሪዎችን በትምህርት ብቻ ሳይሆን በሥነ-ምግባር፣ በፈጠራ ችሎታና በማህበራዊ ኃላፊነት ለማብቃት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

‎ትምህርት ቤቱ በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን የመማር ፍላጎት በማሳደግ፣ የመምህራንን የሙያ አቅም በማጠናከር እና የትምህርት ሂደቱን በተሻለ መልኩ በመምራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተያዘውን ዕቅድ በተግባር ለማዋል የመማር ማስተማር በመርሀ ግብሩ ተጀምሯል።

ሰሜን ሸዋ ዞን በ2019 በጀት ዓመት 9.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብና 20 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ለማስገባት ማቀዱን አስታወቀ!!​ደብረ ብርሃን፦መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም...
14/09/2026

ሰሜን ሸዋ ዞን በ2019 በጀት ዓመት 9.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብና 20 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ለማስገባት ማቀዱን አስታወቀ!!

​ደብረ ብርሃን፦መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን ገቢ ወደ 9.7 ቢሊዮን ብር ከፍ ለማድረግና 20 አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ሙሉ ምርት ለማስገባት ማቀዱን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ አስታውቀዋል።

​ዋና አስተዳዳሪው ይህንን የገለጹት "አርቆ ማየት አልቆ መሥራት" በሚል መሪ ቃል እየተካሔደ የሚገኘውን የዞኑን የ2018 በጀት ዓመት የልማትና ሰላም አፈጻጸም ግምገማ እንዲሁም የ2019 እቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ነው።

​አቶ መካሻ በንግግራቸው፤ ዞኑ ባለፉት ሦስት ዓመታት የነበረበትን የጸጥታና የልማት ተደራራቢ ፈተናዎች ተጋፍጦ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

«የዛሬ ሦስት ዓመት የነበረው ድቅድቅ ጨለማ እየተገፈፈ መጥቷል፤ ዛሬ ከትላንትናው የተሻለ ሲሆን፣ ነገ ደግሞ ከዛሬ ይበልጥ ብሩህ እንደሚሆን እርግጠኞች ነን» ሲሉ የአመራሩንና የሕዝቡን ቁርጠኝነት አብራርተዋል።

​በኢንዱስትሪ፣ ግብርና እና ገቢ አሰባሰብ የተመዘገቡ ስኬቶችን ያብራሩት አቶ መካሻ ዞኑ ከሦስት ዓመት በፊት ይሰበስብ የነበረው 1.9 ቢሊዮን ብር ገቢ በ2018 በጀት ዓመት ወደ 5 ቢሊዮን ብር ማደጉንና በ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ወደ 9.7 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ግብ መያዙን አስታውቀዋል።

በ2018 በጀት ዓመት 20 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን፤ በ2019 ደግሞ ተጨማሪ 20 እና ከዚያ በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት ይገባሉ ብለዋል።

በተለይም በቡልጋ ከተማ አስተዳደርና እንሳሮ ወረዳ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ያሉ ትላልቅ ፋብሪካዎችና ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለአካባቢውና ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ፣ ትራክተሮች፣ የመውቂያና ማጨጃ ማሽነሪዎችና የመስኖ አሰራሮችን በመጠቀም በአሁኑ ወቅት በሄክታር የሚገኘውን 34 ኩንታል አማካይ ምርት በ2019 ወደ 37 ኩንታል ከፍ ማድረግ አለብን ብለዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ለ124 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል መፈጠሩን ያሱሱት አቶ መካሻ፤ ዘንድሮ የሚፈጠሩት የሥራ እድሎች ከቁጥር ባለፈ ዘላቂና የዜጎችን ህይወት በእውነት የሚለውጡ «ጥራት ያላቸው» መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

​በትምህርቱ ዘርፍ የታየውን ተጽዕኖ ለመቀነስ በተደረገው ጥረት በ2019 በጀት ዓመት 612 ሺህ ተማሪዎችን ለማስተማር እቅድ ተይዟል።

በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው አዳሪ የሞዴል ትምህርት ቤት ተማሪዎች በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ500 በላይ ከፍተኛ ውጤት እንዲያመጡ ማስቻሉን እንደ ጥሩ ተሞክሮ ጠቅሰዋል።

ይህ አሰራር በታችኛ ደረጃ (ከቅድመ-መደበኛና 1ኛ ደረጃ) ጀምሮ ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

​ዋና አስተዳዳሪው አመራሩ የደረሰበትን የጸጥታና የመልካም አስተዳደር ፈተናዎች ንቆና መስዋዕትነት ከፍሎ ዞኑ በክልል ደረጃ 2ኛ ደረጃ እንዲይዝ ማድረጉን አድንቀዋል።

በ2019 በጀት ዓመትም የዞኑን ሕዝብ ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ክፍተቶችን አርሞ ለአንደኝነት ደረጃ ለመወዳደር አመራሩ በቁጭትና በአዲስ ሞራል መሥራት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 አዲስ ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክን እንደገለጹት የተገኘው ውጤት በዞኑ በተከሰቱ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ሆነን ነዉ ብለዋል።

🎒 የመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ለተቸገሩ ህፃናት የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።📅 መስከረም 4/2019 ዓ.ምበሰሜን ሸዋ ዞን ዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር፣ “በጎነትና አብሮነት ለኢ...
14/09/2026

🎒 የመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ለተቸገሩ ህፃናት የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

📅 መስከረም 4/2019 ዓ.ም

በሰሜን ሸዋ ዞን ዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር፣ “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወኑ የበጎ ተግባራትን በማጠናከር፣ የመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ለዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የመማሪያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።

📚 የተደረገው ድጋፍ 128 ደርዘን ደብተሮች፣ 6 ፓኮ እስክሪብቶች እንዲሁም የተለያዩ አጋዥ መፃሕፍትን ለሁምቦልድ ቤተ-መጽሐፍ ያካተተ ሲሆን፣ ድጋፉ በተለይ በቋሚነት ችግር ላይ ላሉ 200 ህፃናት ተማሪዎች የሚደርስ ነው።

🤝የመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት አባል አቶ አድሱ አረጋሀኝ እንደገለፁት ይህ ድጋፍ ለ6ኛ ተከታታይ ዓመት የተደረገ ሲሆን፣ ችግር ላይ ያሉ ህፃናት በትምህርታቸው እንዲቆዩ፣ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት እንዳያስተጓጉላቸው እና የተሻለ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ የሚያግዝ በጎ ተግባር ነው ሲሉ ገልፀዋል።

📖 አክለዉም የዚህ ዓመቱ ድጋፍ ምንጭ “ከማምሻ ወግ እድሜ” መፅሐፍ ሽያጭ የተገኘ ገቢ ሲሆን፣ ይህም የንባብ ባህልን፣ የበጎ ፈቃድ ተሳትፎንና የማህበራዊ ኃላፊነትን በማጣመር ለህፃናት የተሻለ የትምህርት ዕድል ለመፍጠር የተደረገ አበረታች ተግባር ነው ብለዋል።

🌱 የመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ያደረገው ድጋፍ በችግር ላይ ያሉ ህፃናትን በትምህርት እንዲቆዩ ከማገዝ ባሻገር፣ ሌሎች ተቋማት፣ ማህበራትና ግለሰቦችም ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ለተቸገሩ ህፃናት የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያጠናክሩ የሚያበረታታ ነው።

በመጨረሻም የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ለመርሀቤቴ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት እዉቅና እና ሽልማት አበርክተዋል።

❤️ አንድ ደብተር የአንድን ህፃን የትምህርት ጉዞ ሊያሻሽል ይችላል፤ አንድ በጎ ተግባር ደግሞ የብዙ ህፃናትን ተስፋ ሊያድስ ይችላል!

‎የአዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ ለመከላከያ ሰራዊትና ለደጀን ሀይል የእርድ ሰንጋ ድጋፍ ተደረገ።‎‎መስከረም 1/2019ዓ/ም‎‎   የአለም ከተማ  ከተማ አስተዳደር እና የመርሐቤቴ ወረዳ አ...
11/09/2026

‎የአዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ ለመከላከያ ሰራዊትና ለደጀን ሀይል የእርድ ሰንጋ ድጋፍ ተደረገ።

‎መስከረም 1/2019ዓ/ም

‎ የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር እና የመርሐቤቴ ወረዳ አስተዳደር በጋራ በመሆን የአዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ ለመከላከያ ሰራዊት እና ለደጀን ሀይል የእርድ ሰንጋ ድጋፍ አድርገዋል ።

‎ በድጋፍ እርክብክቡ የአለም ከተማና የመርሐቤቴ ወረዳ አስተዳደር አመራሮች የተገኙ ሲሆን ሰባት የእርድ ሰንጋ፣ሁለት ፍየል እና 45000 (አርባ አምስት ሺ ብር ) በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል።

‎ ድጋፉ የመከላከያ ሰራዊቱን እና ደጀን ሀይሉን በበዓሉ ወቅት ለመደገፍና ከሰራዊቱ ጎን መቆማቸውን ለመግለጽ መሆኑ ተገልጿል።

‎ የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር እና የመርሐቤቴ ወረዳ አስተዳደር አመራሮች እንደገለጹት፣ ድጋፉ ለሀገር ሰላምና ደህንነት የሚሰራውን የመከላከያ ሰራዊትና ደጀን ሀይሉን ለማበረታታትና የአጋርነት መንፈስን ለማጠናከር የተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

አዲስ ተስፋ፣  አዲስ ዓመት ጉልበት እና አዲስ የስኬት ጉዞ!📅 ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ምየሰሜን ሸዋ ዞን አለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገለታዉ መኮ...
10/09/2026

አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ዓመት ጉልበት እና አዲስ የስኬት ጉዞ!

📅 ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም

የሰሜን ሸዋ ዞን አለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገለታዉ መኮንን የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
ኃላፊው በመልዕክታቸው፤ አዲሱ ዓመት ያለፈውን ዓመት ተሞክሮ በመውሰድ የተሻለ የሥራ አፈጻጸምና ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችል አዲስ የሥራ ዘመን መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም የከተማዋን ሰላም፣ ልማትና የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የመንግሥት፣ የፓርቲና የሕዝብ ትብብር ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፤ የከተማው ነዋሪዎች በልማትና በሰላም ጉዳዮች ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ገለታዉ መኮንን አዲሱ ዓመት የጋራ ዓላማዎችን በማሳካት፣ አብሮነትን በማጠናከርና ለከተማዋ ተጨማሪ ውጤት በመፍጠር የሚታወስ ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
🎉 ለመላው የአለም ከተማ ነዋሪዎች፣ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን 2019 ዓ.ም የሰላም፣ የአንድነት፣ የልማትና የብልፅግና ዓመት እንዲሆን ተመኝተዋል።
🌿 እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!
#አዲስዓመት #እንኳንአደረሳችሁ #አለምከተማ #አንድነት #አብሮነት #ልማት #ብልፅግና

Address

`Alem Ketema

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share