Jekow Woreda Gov't Communication Affairs Office

Jekow Woreda Gov't Communication Affairs Office Jekow Woreda Government Communication Affairs Office

‎በኑዌር ብሔረሰብ ዞን የጅካዎ ወረዳ ም/ቤት 3ኛ ምርጫ ጊዜ 14ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤውን አጠናቋል።በጂካዎ ወረዳ ባለፉት 12 ወራት የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያ...
29/08/2026

‎በኑዌር ብሔረሰብ ዞን የጅካዎ ወረዳ ም/ቤት 3ኛ ምርጫ ጊዜ 14ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤውን አጠናቋል።

በጂካዎ ወረዳ ባለፉት 12 ወራት የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት የጂካዎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ቱት ገለጹ።

የወረደ ዋና አስተዳዳሪ የአስፈጻሚ አካላትን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የ12ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለጉባኤ አባላቱ አቅርበዉ በጉባኤ አባላት ዉይይት ተደርጓል።

ባለፉት 12ወራት በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ዙሪያ አበረታች ዉጤቶች መሰራታቸዉን የጉባኤ አባላት ገልጸዋል።

ተጀምረው እስካሁን ያልተጠናቀቁ የመንገድና የመብራት መሰረተ ልማት አገልግሎት ችግር የተለያዩ ስራዎችን በተቀላጠፈ መንገድ ለማከናወን አስቸጋሪ መሆኑን አንስተዋል።

በትምህርት፣በግብርና በጤና ዘርፉ ላይም የግብዓት ችግሮች መኖራቸዉን ጠቁመዋል።

የጂካዎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ቱት ጂንግ ከጉባኤ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ የተቋረጡ መሰረተ ልማቶችን ለሟሟላት ከክልሉ መንግስት ጋር ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በግብርናዉ ዘርፍ የጂካዎ ወረዳ ህዝብ ከተረጅነት ለማላቀቅ በዉሃ ሸሽ፣በመስኖ በመኸር እርሻ ኋላ ቀር አሰራርን በማዘመን በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የጉባኤውን የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የጂካዎ ወረዳ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ኩዮች ኛክ በቋሚ ኮሚቴዎች አማካኝነት የሚደረገው የክትትልና ቁጥጥር ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ምክር ቤቱ ያከናወናቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት በማጎልበት ሊሻሻሉ የሚገባቸውም በማስተካከል የራሱን ድርሻ እንደሚወጣም አስረድተዋል።

አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ የእርሻ ስራውን በማዘመን ውጤታማ እንዲሆን በዘርፉ የተሰማሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል።

በጂካዎ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀምና ሀብቱን ወደ ልማት በመቀየር የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል እንደሚገባም ገልፀዋል።

የጅካዎ ወረዳ የክረምት ሊግ(Summer league )የእግር ኳስ ውድድር በጅካዎ አካዳሚ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።ከጅካዎ ወረዳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም...
26/08/2026

የጅካዎ ወረዳ የክረምት ሊግ(Summer league )የእግር ኳስ ውድድር በጅካዎ አካዳሚ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።

ከጅካዎ ወረዳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

በመዝግያ ጨዋታው ተገኝተው የመዝግያ ንግግር ያደረጉት የጅካዎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ቱት ጂንግ እንዳሉት ስፖርት በወጣቶች ዘንድ ማህበራዊ ግንኙነትን ፣ጓደኝነትን ፣መጋራትንና መተሳሰብን የሚፈጥር መድረክ እንደሆነ ገልፀዋል ::

የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የበጋ ሊግ ውድድር በኳችቲንግ ከተማ አዘጋጅነት ለተከታታይ 15 ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ በእግር ኳስ ጨዋታ ጅካዎ አካዳሚ የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን ሁለተኛ አጃክ ተሸላሚ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

የጅካዎ ወረዳ ምክር ቤት  መደበኛ ጉባኤ ከነሐሴ 22-23/2018 ዓ/ም እንደሚካሄድ ተገለጸ።የጅካዎ ወረዳ ምክር ቤት 3ኛ የምርጫ ጊዜ 14ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ከነሐሴ እስከ ...
25/08/2026

የጅካዎ ወረዳ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ከነሐሴ 22-23/2018 ዓ/ም እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የጅካዎ ወረዳ ምክር ቤት 3ኛ የምርጫ ጊዜ 14ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ከነሐሴ እስከ 4 /2018 ዓ/ም የሚካሄድ መሆኑን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኩዮች ኛክ ገለፁ ።


ከጅካዎ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም

ጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወራት የወረዳውን የልማት ና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የሚቀርቡበት፣ እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የሚያስችለውን መደበኛ ጉባኤ በመጪው ነሔሴ 22 እስከ 23/2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የጅካዎ ወረዳ ምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኩዮች ኛክ ጓንዶንግ ተናግረዋል።

ዋና አፈ ጉባኤው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ በእነዚህ ሁለት የጉባኤ ቀናት ውስጥ በርካታ ሀገራዊ ፣ ክልላዊ እና ወረዳዊ ጠቀሜታ ያላቸው አጀንዳዎች ላይ ውይይት ይደረጋል ብለዋል።

22/08/2026
በጅካዎ ወረዳ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለሴክተር መ/ቤቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ ።የጅካዎ ወረዳ ምክትል አስተዳደሪ አቶ ቴኛንግ ጋትሉዋክ እንደገለፁት መ...
18/08/2026

በጅካዎ ወረዳ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለሴክተር መ/ቤቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ ።

የጅካዎ ወረዳ ምክትል አስተዳደሪ አቶ ቴኛንግ ጋትሉዋክ እንደገለፁት መንግስት የህብረተሰቡን ጤና አገልግሎት አስተማማኝ ለማድረግና ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን በማከናወን ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልፀዋል::

የወረዳ ኤች አይቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ኘዶር ሉዋል እንዳሉት በወረዳ የኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ ባለድርሻ አካላትን ያጣመረ ትግበራ ያስፈልጋል ብለዋል።

ከጅካዎ ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት(ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም)
ኳችቲያንግ

‎የጅካዎ ወረዳ  የ2018 በጀት ዓመት አስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የ12 ወራት የስራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ  ተካሄደ።‎‎ከጅ...
16/08/2026

‎የጅካዎ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት አስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የ12 ወራት የስራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

‎ከጅካዎ ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ነሀሴ 09/2018 ዓ/ም)

የ2018 ዓ.ም የአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጅካዎ ወረዳ እየተካሄደ ነው።በመርሃ ግብሩ የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች፣ የተለያዩ የማኅበረሰብ ...
03/08/2026

የ2018 ዓ.ም የአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጅካዎ ወረዳ እየተካሄደ ነው።

በመርሃ ግብሩ የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች፣ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ የፀጥታ አካላት፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኞች በንቃት በመሳተፍ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን በተግባር አስጀምረዋል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጅካዎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ቱት ፣ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በየዓመቱ በሕዝብ ሰፊ ተሳትፎ የሚከናወን ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።

መርሃ ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን በመቀነስ፣ በረሃማነትን በመከላከል፣ የተፈጥሮ ሀብትን በማልማት እንዲሁም ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴና ጤናማ አካባቢ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ስኬት በመትከል ብቻ ሳይሆን በችግኞች እንክብካቤና ጥበቃ እንደሚወሰንም አሳስበዋል።

የጅካዎ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ትኛንግ ጋትሏዋክ በበኩላቸው፣ በወረዳው የተዘጋጁ ችግኞች በተገቢው ቦታ እና በታቀደው ዕቅድ መሰረት እየተተከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ የአካባቢውን የደን ሽፋን ማሳደግ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።

እንዲሁም ሕብረተሰቡ የሚተክላቸውን ችግኞች በአግባቡ በመንከባከብ የፕሮግራሙን ዘላቂ ስኬት እንዲያረጋግጥ ጥሪ አቅርበዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመጠበቅ፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የተፈጥሮ ሀብትን ለማጠናከር የሚተገበር ሀገራዊ እንቅስቃሴ ሲሆን፣ በጅካዎ ወረዳም ዘንድሮ በሕዝቡ ተሳትፎ እየተካሄደ ይገኛል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመጠበቅ፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የተፈጥሮ ሀብትን ለማጠናከር የሚተገበር ሀገራዊ እንቅስቃሴ ሲሆን፣ በበጅካዎ ወረዳም ዘንድሮ በሕዝቡ ሰፊ ተሳትፎ በይፋ መጀመሩ ለፕሮግራሙ ስኬት አበረታች ጅምር መሆኑ ተገልጿል።

በኑዌር ዞን በተከሰተው የዝናብ እጥረት  ምክንያት የሰብል ዕድገት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱ ተገለፀ። ችግሩ የአርሶ አደሮችን የምርት ዕድል በመቀነስ በቀጣይ ወራት የምግብ እጥረት ሊፈጠር ይችላ...
02/08/2026

በኑዌር ዞን በተከሰተው የዝናብ እጥረት ምክንያት የሰብል ዕድገት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱ ተገለፀ።

ችግሩ የአርሶ አደሮችን የምርት ዕድል በመቀነስ በቀጣይ ወራት የምግብ እጥረት ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት እንዲነሳም አድርጓል።

የሰብል ምርት መቀነስ ለምግብ እጥረት ስጋት እየፈጠረ ሲሆን፣ በመጪዎቹ የክረምት ወራት ደግሞ ከፍተኛ ዝናብና ጎርፍ ሊከሰት እንደሚችል ስጋት መኖሩንም ተመልክቷል።

በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮች የዝናብ ሁኔታውን ተከትሎ በተለያዩ ጊዜያት ሰብል ለመዝራት ጥረት ቢያደርጉም፣ የዝናብ እጥረቱ በመቀጠሉ የተዘሩት ሰብሎች በተፈለገው መጠን እንዳያድጉ እንቅፋት ሆኗል። በዚህም የሰብል ምርት ከተጠበቀው ደረጃ ዝቅ ሊል እንደሚችል ግምት ተሰጥቷል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጃክ ጆሴፍ እንደገለፁት የዝናብ እጥረቱ በሰብል ምርት ላይ ብቻ ሳይወሰን፣ በአርሶ አደሮች የኑሮ ሁኔታና በአካባቢው የምግብ አቅርቦት ላይም ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ገልፀዋል።

በተለይም የምርት መቀነስ ከቀጠለ በቀጣይ ወራት የምግብ እጥረት እና የርሀብ ስጋት ሊጨምር እንደሚችልም አስታውቋል። ።
በአንጻሩ ግን በመጪዎቹ የክረምት ወራት የዝናብ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር እንደሚችልም የተጠቆመ ሲሆን በዚህ ሁኔታ የአካባቢው ወንዞች በውሃ ሊሞሉ እና የውሃ ሙላት ሊከሰት ይችላል ብለዋል።

ይህም በአንድ በኩል የዝናብ እጥረትን በመቋቋም ሰብሎችን ለማዳን ዕድል ቢፈጥርም፣ በሌላ በኩል የጎርፍ አደጋን በመጨመር የተዘሩ ሰብሎችን እንደገና ሊጎዳ እንደሚችልም ተናግረዋል።

በዞኑ ዋንቱዋ፣ ማኩዌይ፣ ጅካዎ እና ላሬ ወረዳዎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት በተዘሩ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የተለመደው የዝናብ መጠን ባለመገኘቱ በእርሻ ላይ የተዘሩ ሰብሎች መድረቅና መመንመን እንደተከሰተ ሲገለጽ፣ ይህም የአካባቢውን የምግብ ዋስትና በእጅጉ ሊያዳክም እንደሚችል ተጠቁሟል።

በተለይም በእነዚህ ወረዳዎች በዝናብ ላይ ተመስርተው የሚያርሱ አርሶ አደሮች በከፍተኛ ችግር ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ የተከሰተው ሁኔታ ፈጣን ድጋፍ ካልተደረገለት የረሀብ አደጋን ሊያስከትል እንደሚችል ስጋት ተገልጿል።

በመሆኑም የሚመለከታቸው መንግሥታዊ ተቋማትና አጋር ድርጅቶች የተጎዱ ማህበረሰቦችን በፍጥነት በመገምገም አስፈላጊውን የሰብአዊ ድጋፍና የግብርና መልሶ ማቋቋም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

በዛሬው እለት በጅካዎ ወረዳ ከተረጂነት ለመላቀቅ መኸር እርሻ በምስል።ከጅካዎ ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም)
29/07/2026

በዛሬው እለት በጅካዎ ወረዳ ከተረጂነት ለመላቀቅ መኸር እርሻ በምስል።

ከጅካዎ ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም)

Adresse

Democratic Republic Of The

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Jekow Woreda Gov't Communication Affairs Office publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Raccourcis

Partager