Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi

Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in Abu Dhabi.
(3)

ማስታወቂያ!ስማችሁ ከታች የተዘረዘረው ዜጎቻችን ፓስፖርታችሁ ታድሶ የመጣ ስለሆነ በመደበኛ የስራ ሰዓት (8:30 AM-3:30 PM) የቀድሞውን ፓስፖርትና የክፍያ ደረሰኝ በመያዝ (የፓስፖርት ...
31/05/2026

ማስታወቂያ!

ስማችሁ ከታች የተዘረዘረው ዜጎቻችን ፓስፖርታችሁ ታድሶ የመጣ ስለሆነ በመደበኛ የስራ ሰዓት (8:30 AM-3:30 PM) የቀድሞውን ፓስፖርትና የክፍያ ደረሰኝ በመያዝ (የፓስፖርት ባለቤቱ ብቻ) በኤምባሲያችን ቀርባችሁ የታደሰውን ፓስፖርት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናስታውቃለን።

Beeksisa!

Lammiilee keenya Maqaan keessan kan armaan gaditti ibsame/tarraa'e Paaspoortin keessan waan isinii dhufee jiruuf guyyaalee hojiin itti kennamu Wiixataa hamma Jimaataatti sa'aatii (8:30 AM (waaree Dura)-3:30 PM (Waaree Booda) tti Imbaassitti argamuun nagahee paaspoort keessan ittiin haaromfattan harkatti qabachuun paaspoorti keessan isinii dhufee jiru fudhachuu akka dandeessan kabajaaan isin beeksifna.

በዮርዳኖስ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቆንስላ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ፣--------ከአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ ዮርዳኖስ አማን የተጓዙ ባልደረቦች በአማን ከተማ እና አካባቢው ለሚኖሩ ኢት...
31/05/2026

በዮርዳኖስ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቆንስላ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ፣
--------
ከአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ ዮርዳኖስ አማን የተጓዙ ባልደረቦች በአማን ከተማ እና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎች የፓስፖርት እድሳት እንዲሁም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉ ዜጎች የጉዞ ሰነድ (Laissez Passer) አገልግሎት ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል፡፡

አገልግሎቱ ከዛሬ ሜይ 31 ጀምሮ ለሚቀጥሉት አራት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከእነዚህ አገልግሎቶች በተጨማሪ ባልደረቦቹ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን እንደሚጎበኙ እና በአማን ከተማ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን የማህበረሰብ ክፍሎች ጋርም ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡

በዮርዳኖስ ቁጥራቸው ከ45 እስከ 50 ሺ የሚገመት ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ፡፡

በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በየሦስት ወሩ ዲፕሎማቶችን ወደ አማን ከተማ በማሰማራት ለእነዚህ ዜጎች ቋሚ የአገልግሎት መስጫ ሥርዓት በመዘርጋት ለዜጎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

የመደመር መንግስት መጽሐፍ የአረብኛ ትርጉምን የተመለከተ ጥንቅር  በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
30/05/2026

የመደመር መንግስት መጽሐፍ የአረብኛ ትርጉምን የተመለከተ ጥንቅር በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የፃፉት የመደመር መንግስት መፅሐፍ ዓርብኛ ትርጉም ከአፍሪካ እስከ መካከለኛው ምስራቅ እንዴት ይነበባል? ...

ክቡር አምባሳደር ዶክተር ጀማል ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (FBC) ጋር ያደረጉትን ቆይታ እንዲከታተሉ ተጋብዘዋል።
28/05/2026

ክቡር አምባሳደር ዶክተር ጀማል ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (FBC) ጋር ያደረጉትን ቆይታ እንዲከታተሉ ተጋብዘዋል።

#ፋና #ኢትዮጵያ

Eid Mubarak!
27/05/2026

Eid Mubarak!

26/05/2026

የመደመር መንግስት አረብኛ ዕትም ይፋዊ የምርቃት ስርዓት ወቅት ክቡር አምባሳደር ዶ/ር ጀማል ካስተላለፉት መልዕክት መካከል

Jemal Beker
Ethiopian Broadcasting Corporation
Ethiopian News Agency
The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia

23/05/2026

በኢትዮጵያና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች (ዱባይ) መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ የ“Dubai-Ethiopia Business Connect” መድረክ ትናንት ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በይፋ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ጀማል በከር በሁለቱ አገራት መካከል እየተጠናከረ የመጣው ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ለግል ዘርፉ ሰፊ የገበያና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን እየፈጠረ መሆኑን ገልጸው የኤምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ምቹ በሆኑ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ሙሉው የክቡር አምባሳደር መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል።

Jemal Beker
Ethiopian News AgencyThe Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Ethiopian Broadcasting Corporation

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛው የዒድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል እንኳን አደረሳችሁ እያልን በበዓሉ ምክንያት በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከሜይ 25/2026 እስከ ሜይ ...
22/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛው የዒድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል እንኳን አደረሳችሁ እያልን በበዓሉ ምክንያት በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከሜይ 25/2026 እስከ ሜይ 29/2026 ድረስ ስራ ዝግ መሆኑን የተገለፀ በመሆኑ ኤምባሲውም በነዚህ ቀናት ዝግ መሆኑን እየገለጽን፣ መደበኛው ሥራ ጁን 01/2026 የሚጀምር መሆኑን እንገልጻለን።

በመሆኑም ኤምባሲው ዝግ በሚሆንበት ወቅት ለሚገጥማችሁ አስቸኳይ ነገሮች በኤምባሲው ስልክ ቁጥር +971500001522 በቀጥታ በመደወል ወይንም በዋትሳፕ ድምጽ ሪከርድ በማድረግ /በጽሁፍ/ መረጃ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

የዱባይ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ትስስር ፎረም በአዲስ አበባ በይፋ ተጀመረ ————- በኢትዮጵያና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች (ዱባይ) መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ትብብር ይ...
22/05/2026

የዱባይ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ትስስር ፎረም በአዲስ አበባ በይፋ ተጀመረ
————-
በኢትዮጵያና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች (ዱባይ) መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ የ“Dubai-Ethiopia Business Connect” መድረክ ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በይፋ ተካሂዷል።

ይህንን መድረክ ለመካፈል የዱባይ የንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር መሐመድ አሊ ረሺድ ሉታ የመሩት የ36 አባላት የንግድ ልዑክ አዲስ አበባ የተገኘ ሲሆን በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ከ250 በላይ የንግድ ማኅበረሰብ አባላትና ከፍተኛ የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች በፕሮግራሙ ላይ ታድመዋል።

በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ጀማል በከር በሁለቱ አገራት መካከል እየተጠናከረ የመጣው ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ለግል ዘርፉ ሰፊ የገበያና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን እየፈጠረ መሆኑን ገልጸው የኤምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ምቹ በሆኑ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የዱባይ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር መሐመድ አሊ ረሺድ ሉታ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ያላትን ስትራቴጂካዊ የንግድ ተመራጭነት ጠቅሰው የዱባይ ኩባንያዎች አጋርነታቸውን ለማስፋትና አዳዲስ የንግድ ዕድሎችን ለመፍጠር ጽኑ ፍላጎት እንዳላቸው አስታውቀዋል።

በመድረኩ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የሚመለከታቸው አካላት አማካኝነት በኢትዮጵያ ስላሉት ወቅታዊና ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ ማበረታቻዎችና የሪፎርም ሥራዎች በተለይም በግብርና፣ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በቱሪዝም፣ በሎጅስቲክስ እና በታዳሽ ኃይል ዘርፎች ዙሪያ ለዱባይ የንግድ ልዑክ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።

ዱባይ ቻምበርስ ከ300,000 በላይ አባላት ያሉት ሲሆን፣ በቀጠናው ካሉ ትልልቅ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ የንግድ ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን ይህ የቢዝነስ ትስስር መድረክ በሁለቱ አገራት የግል ዘርፎች መካከል ቀጥተኛ ግንኙነትን (B2B) ለመፍጠርና የጋራ የንግድ ልውውጥን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ መሠረት የጣለ መሆኑ ተገልጿል።

Jemal Beker
Ethiopian News AgencyThe Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Ethiopian Broadcasting Corporation

የጋብቻ ማስታወቂያ
22/05/2026

የጋብቻ ማስታወቂያ

Address

Villa19 Ahl Alma'rifa St/Al Nahyan/Abu Dhabi
Abu Dhabi

Opening Hours

Monday 08:30 - 15:30
Tuesday 08:30 - 15:30
Wednesday 08:30 - 15:30
Thursday 08:30 - 15:30
Friday 08:30 - 12:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi:

Share