Tocha Communications

Tocha Communications This is an official page of Tocha Woreda Government Communication Affairs Office posting any social, economic, cultural and political events of this woreda.

ጤናማና አምራች ማህበረሰብን ለመገንባት አከባቢን ከአር ፁዱ በማድረግ ለነዋሪዎች ሚቹ አከባቢ መፈጠር ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ ።በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ መ/ዓለም እና ሹሹር ቀበሌዎች ከአር የፀዱ ...
02/09/2026

ጤናማና አምራች ማህበረሰብን ለመገንባት አከባቢን ከአር ፁዱ በማድረግ ለነዋሪዎች ሚቹ አከባቢ መፈጠር ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ ።

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ መ/ዓለም እና ሹሹር ቀበሌዎች ከአር የፀዱ በመሆናቸዉ በማብሰር የምረቃ ስነ-ሰርዓት ተካሄዷል ።

በመረሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቶጫ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንድነት ቡንጉዶ እንደጠቆሙት፦ ነዋርዎቹ አከባቢያቸዉን ፅዱና ንፁሁ በማድረጊ ለኑሮ ሚቹ ማድረጋቸዉ እንዳስደሰተቸዉ በመግለጽ አከባቢን ከብክለት ነፃ ማድረጊ የፓርቲያችን ኢኒሼቲቭ መሆኑን በማንሳት የተመዘገበው ስኬት የህዝብን አቅም አስተባብሮ በመስራት ረገድ የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸዋል።

አክለዉ አቶ አንድነት፦ቀበሌዎቹ ከአር የፀዱ መሆናቸዉ የነዋሪዎችን ጤናማነት ከማረጋገጥ ባለፈ ለልማት ስራዎች ሚቹ መደላደል ለመፍጠር ጽኑ መሰረት የጣለ ተግባር መሆኑንም አንስተዋል። የቀበሌው ህብረተሰብ ለውጤቱ መመዝገብ ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚበረታታ በመሆኑ፣ የተገኘውን ድል ለማስቀጠል እና ወደ ተሻለ የልማት ምዕራፍ ለመሸጋገር የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

የቶጫ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ተወካይና የበሽታ መከላከል ቡድን አስተባባሪ አቶ መላኩ መኩሪያ በበኩላቸው፦ ተቋሙ የህብረተሰቡን ጤና ከበሽታ ቀድሞ ለመከላከል በልዩ ትኩረት እየራ በሆኑ በዛሬዉ ዕለት የክልልና የዞን የጤና ቡድን በተለያዩት ጊዜያት ዞሬዉ በመመልከት በሰጡት ግብረ-መልስ መነሻ ሁለቱ ቀበሌዎች ከአር የፀዱ የሆናቸዉን አብስረዋል።

አክለዉ አቶ መላኩ፦አር/የሰገራ አጠቃቀም በህብረተሰቡ ላይ ያስከትል የነበረውን ከባድ የጤና ጫና በማስታወስ፣ አሁን የተደረሰው ስኬት በውሃ ወለድ እና ተላላፊ በሽታዎች የሚደርሰውን ጉዳት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰው አመላክተዋል።

በመረሃ-ግብሩ ላይ ጤናማና አምራች ማህበረሰብን ለመገንባት አከባቢን ከአር ፁዱ በማድረግ እንዲህ አይነት የመሰረታዊ ንጽህና ዘመቻዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ተጠቁሟል።

ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

የአፋልጉኝ ማስታወቂያተፈላጊዉ ህፃን ክብራለም ስንታየሁ፦የተባለ የ13 ዓመት ታዳጊ ከቤቱ ወጥቶ ባለመመለሱ ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ሁኔታ እየፈለጉት ይገኛሉ።ሙሉ ስም፦ክብራለም ስንታየሁ ወጁ ዕድሜ፦...
02/09/2026

የአፋልጉኝ ማስታወቂያ

ተፈላጊዉ ህፃን ክብራለም ስንታየሁ፦የተባለ የ13 ዓመት ታዳጊ ከቤቱ ወጥቶ ባለመመለሱ ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ሁኔታ እየፈለጉት ይገኛሉ።

ሙሉ ስም፦ክብራለም ስንታየሁ ወጁ ዕድሜ፦13 ዓመት የመኖሪያ አድራሻ፦ዳውሮ ዞን፣ ቶጫ ወረዳ፣ ሻንዳ ሀውሻ ቀበሌ የጠፋበት ቀን ነሀሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጥዋቱ 2:00 ሰዓት ከቤት ወጥቶ አልተመለሰም ።

ይህንን ልጅ ያያችሁ ወይም ያለበትን ቦታ የምታውቁና ማንኛውንም ፍንጭ መረጃ መስጠት የምትችሉ የትኛውም ዜጋ ከታች በተዘረዘሩት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ለአባቱ ማሳወቅ ትችላላችሁ ።

ለምታደርጉልን ትብብር ከልብ እያመሰገንኩኝ ወሮታ ከፋይ ነኝ ይላል ወላጅ አባቱ ።

የፈላጊ ወላጅ አባት አቶ ስንታየሁ ወጁ !!

ለጥቆማ 0911418197/0950419026 ይደዉልልን

በጎነት ለአብሮነት !!!

ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

የዳውሮ ዞን አመራሮች ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂዱት የቆዩት የግምገማ እና ምዘና መድረክ ዛሬ ተጠናቋል።‎‎በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስ...
01/09/2026

የዳውሮ ዞን አመራሮች ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂዱት የቆዩት የግምገማ እና ምዘና መድረክ ዛሬ ተጠናቋል።

‎በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ መኩሪያ አመራሩ በመንግስትና በፓርቲ የተጣለበትን ኃላፊነቱን በብቃት በመወጣት፣ መልካም ስነ-ምግባርን መላበስ፣ የአመለካከት ጥራትን ማጎልበት እና የፓርቲና የመንግስት ስራዎችን በብቃት መፈፀም የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዳለበት ገልጸዋል።

‎የአመራር ምዘናውን በተመለከተም የአመራሩ ቁርጠኝነት፣ ተነሳሽነት፣ የተግባር አፈጻጸም እና የተጣለበትን ተልዕኮ የመወጣት ሚና መነሻ በማድረግ አካላዊና ሂስ ግለ-ሂስ ግምገማ እና ምዘና ተካሂዷል።

‎በግምገማው ወቅት በ2018 በጀት ዓመት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸው የተጠቀሰ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ አሁንም ተገቢውን ምላሽ ያላገኙ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች፣ የአመራር ውጤታማነት ችግር፣ አገልግሎት አሰጣጥ፣ፈጣን ምላሽ እና ብልሹ አሰራር ችግሮች በዝርዝር ተገምግመዋል።

ፓርቲው ከዚህ ግምገማ መነሻ በማድረግ ጉድለቶችን በጥልቀት በመገምገም በተለዩ ጉዳዮች ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድም አስታውቋል።

‎አቶ መንግስቱ አክለውም እያንዳንዱ አመራር በተመደበበት የሥራ ኃላፊነት ላይ የህዝቡን ተጠቃሚነትና ለማረጋገጥ ከምን ጊዜም በላይ በላቀ ቁርጠኝነት መሰራት እንዳለበት በማጠቃለያው በዝርዝር ያነሱ ሲሆን በሌብነትና ብልሹ አሠራር ላይ ተጠያቂነት የሚያሰፍን አሰራር መዘርጋት እንዳለበት አሳስበዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የአመራር አንድነትን የሚሸረሽሩ፣ የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎችን የሚያደናቅፉ እንዲሁም ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ አፍራሽ አስተሳሰቦችን በንቃት መመከት እንደሚገባ ተገልጿል።

‎በዚህ መድረክ የተለዩ ችግሮችን መነሻ በማድረግ ሁሉም መዋቅር ላይ ያሉ ጉዳዮች በዝርዝር የመገምገም ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ቀጣዩ የግምገማ ምዕራፍ በወረዳና በከተማ አስተዳደር እርኬን እንደሚካሄድም ተጠቁሟል።

‎የመድረኩ ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው የፓርቲና የመንግሥት ተግባራትን በላቀ ውጤት ለመፈጸም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን በቆራጥነት ለመፍታትና የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በቅንጅት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

በግምገማው መድረክ የተገኙ የዞኑ አጠቃላይ አመራሮች በተያዘው በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የሕዝቡን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ለማረጋገጥ የሚያስችል የጋራ መግባባት ላይ በመደረስ ተጠናቋል። ስል የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

የዳዉሮ ብሄር የዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል ማህበራዊ ትስስርን ከማስጠበቅ ባለፈ አብሮነትን እና ሰላምን ከሚሰብኩ ታላቁ የባህል እሴት ዉስጥ አንዱ መሆኑ ተገለጸ።የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለ...
01/09/2026

የዳዉሮ ብሄር የዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል ማህበራዊ ትስስርን ከማስጠበቅ ባለፈ አብሮነትን እና ሰላምን ከሚሰብኩ ታላቁ የባህል እሴት ዉስጥ አንዱ መሆኑ ተገለጸ።

የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዉሏል ።

በመረሃ-ግብሩ ላይ የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሰ እንደጠቆሙት፦የአብሮነት እና የሰላም እሴቶች ማጠናከሪያ የሆነዉ የዳዉሮ ብሄር የዘመን መለወጫ"ቶኪ-በዓ" በዓል ማህበራዊ ትስስርን ከማስጠበቅ ባለፈ አብሮነትን እና ሰላምን ከሚሰብኩ ታላቁ የባህል እሴት ዉስጥ አንዱ መሆኑን አብራርተዋል።

አክለዉ ዋና አስተዳዳሪዉ፦ የብሔሩን ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክ መገለጫ የሆኑ ዕሴቶች ተጠብቀዉ ለትውልድ ማሻገር እንደሚገባ በማንሳት እንደ ቶጫ ወረዳ ያሉት የባህልና ቅርስ ማንከባከብና ማስተዋወቅ ስራዎችን በልዩ ትኩረት እንደምሰሩ አረጋግጠዉ በዓሉ ሲከበር ማህበረሰቡ ለወረዳው እና ለሀገሩ ሁለንተናዊ ልማት እና ዕድገት በአንድነት ተባብሮ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የቶጫ ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ም/ኢን/ር አስረስ ከበደ በበኩላቸዉ የ"ቶኪ በዓ" በዓል የዳውሮ ህዝብ የማንነት መገለጫና ይቅርታ፣ዕርቅ የሚነግስበት ጥላቻና መቃቃር ተጥሎ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ታላቅ የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል መሆኑን አብራርተዋል።

አክለዉ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወረዳዉ እጅግ በርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶችና እሴቶች ባለቤት መሆኑን ጠቅሰው፤ እነዚህን ሃብቶች ማልማትና ለህዝብ ማስተዋወቅ ረገድ ጽ/ቤታቸው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ በማንሳት
ወጣቱ ትውልድ የራሱን ባህል አውቆ እንዲያኮራና የሀገር በቀል እውቀቶችን እንዲያዳብር በዓሉ ትልቅ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

በበዓሉ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ አባላት እና የወረዳው የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት የተለያዩ አዉደሪዕ በማቅረብና በዳዉሮ ባህላዊ ክዋንዎች ታጅቦ ተከብሮ ዉሏል።

ዘገባዉ የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ "ቶኪ-በዓ"በዓል አከባበር በፎቶ!!!ቶጫ ወረዳ ኮሙኒኬሽን !
01/09/2026

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ "ቶኪ-በዓ"በዓል አከባበር በፎቶ!!!

ቶጫ ወረዳ ኮሙኒኬሽን !

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ "ቶኪ-በዓ"በዓል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል።በበዓሉ ላይ የወረዳዉ አመራሮች የሀገር ሽማግለዎች የሀይማኖት አባቶችና ጥሪ የተደረገላ...
01/09/2026

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ የዳዉሮ ብሄር ዘመን መለወጫ "ቶኪ-በዓ"በዓል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በበዓሉ ላይ የወረዳዉ አመራሮች የሀገር ሽማግለዎች የሀይማኖት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸዉ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ቶጫ ወረዳ ኮሙኒኬሽን !

31/08/2026
በዳውሮ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በመካሄድ ላይ ነው‎‎በዳውሮ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በታርጫ ከተማ...
29/08/2026

በዳውሮ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

‎በዳውሮ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

‎መድረኩ በየደረጃው የሚገኘውን አመራር የአመለካከትና የተግባር አንድነት ለመመዘን የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም እንዲሁም አመራሩ በቀጣይ የሕዝብ ተጠቃሚነትን በተሟላ ሁኔታ እንዲያረጋግጥ ለተልዕኮ ለማዘጋጀት ያለመ ነው።

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ በንግግራቸው ተልዕኮዎችን በተሻለ መልኩ በመፈጸም የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መጠነ ሰፊ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

‎ከአፈጻጸም አኳያም ከጊዜ ወደ ጊዜ አዎንታዊ መሻሻሎች መታየታቸውን ያብራሩ ሲሆን በአስፈፃሚ ተቋማት መካከል የሚታየውን የተግባር አፈጻጸም ልዩነት መስተካከል እንደሚገባም አሳስበዋል።

‎የአመራር ቁመና በብልፅግና ፓርቲ መሠረታዊ መርሆችና ዕሴቶች ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበትም አቶ አንድነት አክለዋል።

‎የመድረኩ ዋና ዓላማም አስፈጻሚዎች የመንግሥትና የፓርቲ ተግባራትን በጥራት፣ በእውቀትና በውጤታማነት እንዲያከናውኑ ማብቃት መሆኑም ተገልጿል።

‎ በተጨማሪም መድረኩ ድክመቶችን በማረም ለቀጣይ ተልዕኮ ከማዘጋጀት ባሻገር፣ የውስጠ-ፓርቲ አንድነትን፣ ጤንነትንና የዴሞክራሲያዊ መርህን በማረጋገጥ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳካት የጎላ ሚና እንደሚኖረውም ተመላክቷል።

አመራሩ የአገልጋይነት እሳቤ በመላበሰ  የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ ተግባር ነው፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)​በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲካ...
28/08/2026

አመራሩ የአገልጋይነት እሳቤ በመላበሰ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ ተግባር ነው፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

​በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የከፍተኛ አመራር የግምገማና ምዘና መድረክ በስኬት ተጠናቋል።

​የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ መድረኩ ውስጣዊ የእይታ አድማስን ያሰፋ፣ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶችን ያጎለበተ ውጤታማ የትግል ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

መድረኩ በአመራሩ ዘንድ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅምን በማሳደግ፣ የፓርቲና የመንግስት ተልዕኮዎችን በብቃት ለመፈጸምና ለማስፈጸም አቅም እንደሚፈጥር አንስተዋል።

አመራሩ የአገልጋይነት እሳቤን በመላበስ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንዲሁም የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በማሳለጥ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።

ብልሹ አሰራሮችን ማስወገድ፣ ጤናማ የአሰራር ስርዓት መትከልና ተቋማዊ ጤንነትን ማስጠበቅ ለነገ የማይባል አበይት ተግባር መሆኑንም በአፅንኦት አንስተዋል።

​በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፤ መድረኩ ግልጽ፣ አሳታፊ፣ መገነባባትንና መተራረምን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ለቀጣይ ስራዎች ጠንካራ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።

​አቶ ፍቅሬ አክለውም ህብረ-ብሔራዊ አንድነትንና ወንድማማችነትን በማጎልበት ክልሉን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የግምገማ ሂደት እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በዚህም ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት የህዝብን አዳጊ ጥያቄዎችን ለመመለስ ብርቱ ትግል መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

መድረኩ የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን በተጠያቂነት ለማረም ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ በመርሃ ግብር በሁሉ እርከን እንዲፈጸም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ተቀምጠዋል። መረጃው የክልሉ ፓርቲ ኮምኒኬሽን ነው።

"ቶኪ-በዓ" በዓል የዳውሮ ብሔር የማይዳሰስ ቅርስ በመሆኑ በቀጣይ በዩኔስኮ (UNESCO) ለመመዝገብ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል እጩ ዶ/ር ታማኝ ኃይለ የዳዉሮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላ...
28/08/2026

"ቶኪ-በዓ" በዓል የዳውሮ ብሔር የማይዳሰስ ቅርስ በመሆኑ በቀጣይ በዩኔስኮ (UNESCO) ለመመዝገብ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል እጩ ዶ/ር ታማኝ ኃይለ የዳዉሮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ!!

በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ መጪው የዳውሮ ብሔር ዘመን መለወጫ "ቶኪ-በዓ" በዓል በልዩ ድምቀት ለማክበር ያለመ የጋራ ዉይይት መድረክ ተካሄዴ ።

የዉይይት መድረኩን የመሩት የዳውሮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ እጩ ዶ/ር ታማኝ ኃይለ እንደገለጹት፣ የዳውሮ ብሔር የራሱን ባህል፣ ቋንቋ እና አኗኗር ታሪካዊ ስርዓቶች ጠብቆ ማቆየት የሚችለው ህዝቡ የራሱን ቅርስና መገለጫዎቹን በአግባቡ ሲንከባከብ ለትዉልድ በማስተላለፍ እንደሆነ አብራርተዋል።

አክለዉ እጩ ዶ/ር ታማኝ "ቶኪ-በዓ" በዓል የዳውሮ ብሔር የማይዳሰስ ቅርስ በመሆኑ በቀጣይ በዩኔስኮ (UNESCO) ለመመዝገብ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ዓላማ ከግብ ለማድረስም ሁሉም ዜጋ የበዓሉን ታሪካዊና ባህላዊ እሴት ተረድቶ በንቃት ሊሳተፍና ሊያከብር እንደሚገባና በዓሉ ከማንኛውም ሃይማኖታዊ ስርዓት ጋር ፍጹም የማገናኝ በመሆኑ ማህበረሰቡ ባህሉን ከሃይማኖት ጋር ሳይቀላቀል በባህላዊ ይዘቱ ብቻ አጠናክሮ ማክበር እንደሚገባ አሳስበዋል።

የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሰ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የ"ቶኪ-በዓ" በዓል ከወትሮው የተለየ መልክና ድምቀት ይኖረው ዘንድ የወረዳው አስተዳደር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለዉ፦የብሔሩ ህዝብ የቆየ አኗኗር ታሪካዊ ስርዓቶችና እሴቶች በትውልድ መካከል እንዲተላለፉ በዓሉን በባለቤትነት ስሜት ማክበር እንደሚገባና የ"ቶኪ-በዓ" በዓል የዳውሮ ህዝብ ማህበራዊ ትስስርና መገለጫ በመሆኑ፣ በዩኔስኮ የምዝገባ ሂደት ውስጥ የወረዳው ህዝብና አመራር የድርሻቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለባቸው በመጦቆም በዓሉ በዳዉሮ ባህላዊ እሴቶች ላይ ብቻ የተመሰረተ በመሆኑ፣ ማንኛውም ዜጋ ያለምንም ልዩነት በደስታና በጋራ መንፈስ ሊያከብረው እንደሚገባ አሳስበዋል።

የቶጫ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንድነት ቡንጉዶ እንዳብራሩት፦የ"ቶኪ-በዓ" በዓል ከማንኛውም ሃይማኖታዊ ጣልቃገብነት ወይም ግንኙነት ነጻ የሆነ፣ የዳውሮ ብሔር ንጹህ ባህላዊ መገለጫ በመሆኑ ፓርቲው አባላትና አመራሮችም የብሔሩን የማይዳሰስ ቅርስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በሚደረገው ጥረት ከህዝቡ ጎን በመቆም የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የማስተባበር ስራዎችን አጠናክረው እንድቀጥሉ አሳስበዋል።

በመድረኩ፦ህዝቡም ባህሉን በመጠበቅና አንድነቱን በማጠናከር በዓሉን በታላቅ ድምቀት ማክበር እንዳለበት ጥሪ ቀርቦል።

ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

Address

Tocha
Toamasina

Telephone

+251911418197

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tocha Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Tocha Communications:

Shortcuts

Share