05/06/2026
በሊዝ ጨረታ ለመኖሪያ ፣ለንግድ እና ለልማት የተላለፉ ቦታዎችን የወሰዱ ተጠቃሚዎች በውሉ መሠረት በፍጥነት ወደ ልማት ስራ እንዲገቡ የወልቂጤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አሳሰበ።
ግንቦት 28/2018ዓ.ም [ወልቂጤ ]
በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ለ5ኛ ዙር ያወጣውን የመኖሪያ ቦታ የሊዝ ጨረታ በይፋ ተከፈተ።
ለ5ኛ ዙር የወጣው ግልፅ የሊዝ ጨረታ ለመኖሪያ ቤት 54 ፕሎቶች ለከተማው ነዋሪው የማቅረብ ስራ መሰራቱን ማዘጋጃ ቤቱ ገልጿል ።
የወልቂጤ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶፊቅ ሱልጣ እንደተናገሩት በ2018 በጀት አመት የከተማ መሬት ጨረታ ስራ በህግ፣በግልፅነትና በተወዳዳሪነት ለተጠቃሚዎች በሊዝ ለማስተላለፍ ከምንም ጊዜ በተሻለ በትኩረት መሠራቱን ገልጸዋል ።
ለ5ኛ ዙር የወጣውን ግልፅ የመኖሪያ ቦታ የሊዝ ጨረታ ኮሚቴዎችና ስነምግባሮች በተገኙበት ጨረታው መከፈቱንም አስረድተዋል ።
በዚህ ዙር ለመኖሪያ ቤት 54 ፕሎቶች ለከተማው ነዋሪው የማቅረብ ስራ መሰራቱን ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
ለማህበረሰቡ በፍትሀዊነት የመኖሪያ እና የንግድ ቦታ በሊዝ ጨረታ በማስተላለፍና ፋላጎቶችን በሟሟላት የከተማዋን ገቢ በማሳደግ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትን ላይ መሠረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
ቀጣይ ጨረታውን ያሸኑፉ የህብረተሰብ ክፍሎች ተለይተው የሊዝ ውል ማስፈፀምና የመሬት ርክክብ ስራ እንደሚሰራ ገልፀው ከዚህ በፊት በሊዝ ቦታ አግኝተው የተረከቡ አካላትም ፈጥነው ወደ ልማት መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
እንዲሁም ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤቱ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት በማድረግና የተላለፉ ቦታዎች የመሠረተ ልማት ምቹ በማድረግና ህዝቡን በማሳተፍ በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የከተማችን ማህበረሰብ ለልማት ለእድገት እያደረገው ያለውን ንቁ ተሳትፎ በማጠናገር ከተማዋ ውብ ማራኪ እና ለዜጎቿ ምቹ እንድትሆን በጋራ እንስራ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።