የሰሜን ወሎ ዞን ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • የሰሜን ወሎ ዞን ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ

የሰሜን ወሎ ዞን ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ በዚህ ገጽ በሀገራችን፣ በክልላችን እንዲሁም በሰሜን ወሎ ዞን የሚሰሩ የከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን ስራዎችና ተያያዥ ጉዳዮች ይተነተኑበታል

11/09/2018የሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሰራተኞች በተለያዩ አርዕስቶች ስልጠና ወሰዱ።ከግንቦት 8/09/2018 ዓ.ም ጀምሮ1) በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ስርአትና መልሶ መ...
20/05/2026

11/09/2018
የሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሰራተኞች በተለያዩ አርዕስቶች ስልጠና ወሰዱ።
ከግንቦት 8/09/2018 ዓ.ም ጀምሮ
1) በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ስርአትና መልሶ መጠቀም ጋር በተያያዘ
2) ከአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂዎች አንፃር
3) የካይዘን አሰራር ስርአትና ጠቀሜታዎቹ ዙሪያ ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን ሰፊ ውይይትም ተካሂዶባቸዋል።
ሁሉም የመምሪያው ሰራተኞች ከስልጠናው በቂ ግንዛቤ እንዳገኙና ስልጠናዎቹ ስራዎችን ለመስራት ምቹ መዳላድል እንደሚፈጥሩላቸው የገለፁ ሲሆን፣ እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች በቀጣይነት ቢሰጡ መልካም መሆኑን ጭምር ገልፀዋል።

07/05/2026

29/08/2018
የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች ማረጋገጫ (Verification) መመሪያ

📌​​​​​​​​​​​​ይህ ሰነድ የማረጋገጫ ሂደቱ ስልታዊ እና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ እንዲከናወን የሚረዱ ሶስት ዋና ዋና ክፍሎችን ይዟል።

​ክፍል 1፡ የግድ መሟላት ያለባቸው ሰነዶች (11 ዓይነቶች)

​ለእያንዳንዱ ሰራተኛ ሊሟሉ የሚገባቸው መሰረታዊ የሰው ኃይል መረጃዎች፦

📌​​​​​​​​​​​​ብሄራዊ መታወቂያ፡ ከተመዘገበበት ስልክ ቁጥር ጋር።

📌​​​​​​​​​​​​የቢሮ መታወቂያ፡ ወቅታዊ የሆነ።

📌​​​​​​​​​​​​የቅጥር ደብዳቤ፡ የመጀመሪያ ቅጥር ሰነድ።

📌​​​​​​​​​​​​የዝውውር ሰነድ፡ ከሌላ መሥሪያ ቤት የመጡ ከሆነ።

📌​​​​​​​​​​​​የደረጃ እድገት፡ የተሰጡ የደረጃ እድገት ደብዳቤዎች።

📌​​​​​​​​​​​​የአገልግሎት ማራዘሚያ፡ ጡረታ ወጥተው ለሚሰሩ ብቻ።

📌​​​​​​​​​​​​የትምህርት ማስረጃዎች፡ ሁሉም የትምህርት ደረጃዎች።

📌​​​​​​​​​​​​የጡረታ ፎርም፡ የተሞላ የጡረታ መረጃ።

📌​​​​​​​​​​​​የስራ ልምድ፡ የቀድሞ የስራ ልምድ ማስረጃዎች።

📌​​​​​​​​​​​​የሹመት ደብዳቤ፡ ተሿሚ ለሆኑ አመራሮች።

📌​​​​​​​​​​​​የድልድል/ምደባ ደብዳቤ፡ አዲስ ድልድል ተደርጎ ከሆነ።

​ክፍል 2፡ ተጨማሪ የማህበራዊ ሁኔታ ሰነዶች

📌​​​​​​​​​​​​የጋብቻ ሰርተፍኬት

📌​​​​​​​​​​​​የልጆች የልደት ሰርተፍኬት (ልጆች ካሉ)

​ክፍል 3፡ የአሰራር ቅደም ተከተልና መመሪያዎች

✍​ሂደቱ ያለምንም መስተጓጎል እንዲሄድ ተቋማት የሚከተሉትን ተግባራት ማከናወን ይኖርባቸዋል፦

📌​​​​​​​​​​​​መርሃ-ግብር ማዘጋጀት፡ በቀን ለአንድ መረጃ ሰብሳቢ 7 ሰራተኞችን በማደራጀት ቀኑን አስቀድሞ ማሳወቅ።

📌​​​​​​​​​​​​የአካል መገኘት፡ በወሊድ፣ በህመም ወይም በአመት እረፍት ላይ ያሉ ሰራተኞች በአካል ቀርበው መመዝገብ አለባቸው።

📌​​​​​​​​​​​​የሰው ኃይል መመደብ፡ ስራውን የሚከታተል፣ ጥንቃቄ ያለውና የIT እውቀት ያለው ኃላፊ መመደብ።

📌​​​​ መረጃዎችን - በጊዜ፣ በጥራትና በማደራጀት የዲጅታል ሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ለማሳካት የድርሻቸውን እንወጣ። መልዕክታችን ነው።

የአብክመ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ

መጋቢት 30/2018 ዓምየሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ጠቅላላ ሰራተኞች የ3ተኛ ሩብ አመት የእቅድ አፈጻጸም ግመገማ አካሄዱ።። ዛሬ ማለትም መጋቢት 30/2018 ዓም ሁሉም የ...
08/04/2026

መጋቢት 30/2018 ዓም
የሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ጠቅላላ ሰራተኞች የ3ተኛ ሩብ አመት የእቅድ አፈጻጸም ግመገማ አካሄዱ።
። ዛሬ ማለትም መጋቢት 30/2018 ዓም ሁሉም የመምሪያው ሰራተኞችና የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት የመምሪያው የባለፉት ዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ተገምግሟል። በዚሁ መሰረት 100% በላይ አፈፃፀም የተያባቸው ተግባራት እንዳሉ ሁሉ በአመዛኙ በሚባል ሁኔታ ብዛት ያላቸው ተግባራት ከ50 እስከ 75 በመቶ አፈፃፀም ተገኝቶባቸዋል። በተለያዩ የስራ ተግዳሮቶች ምክኒያት አፈፃፀም የሌላቸውን ተግባራት በቀጣይ ሁነቶችን አመቻችቶ እንዲሰሩ ማድረግ የሁሉም የመምሪያው ሰራተኞች ኃላፊነት ነው።

 የሠሜን ወሎ ዞን አስተደዳር ለተለያዩ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ሹመት ተሰጥቷል።❶ አቶ ነጋ ጌታቸው ልሳነወርቅ ➛ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር እንስሳትና ዓሳ ሀብት መምሪያ ኃላፊ ❷ ወ/ሮ...
16/01/2026



የሠሜን ወሎ ዞን አስተደዳር ለተለያዩ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ሹመት ተሰጥቷል።
❶ አቶ ነጋ ጌታቸው ልሳነወርቅ ➛ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር እንስሳትና ዓሳ ሀብት መምሪያ ኃላፊ

❷ ወ/ሮ ደስታ አራጋው ሲሳይ ➛ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ኮንስትራክሽን ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ

❸ አቶ ደሳለ ባየ በላይ ➛ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ፕላን ልማት መምሪያ ኃላፊ

❹ አቶ ባንቴ ምስጋናው መሥፍን ➛ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር አከባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

መልካም የስራ ዘመን !

(ሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን)

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት (የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን እና የኮንስትራክሽን...
01/01/2026

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም

የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት (የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን እና የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት) በሁለተኛው ዙር (second wave) የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ተግባራዊ እንዲያደርጉ ከተመረጡ መ/ቤቶች በመመሆናቸው ከሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሪፎርሙን ወደ ትግበራ ለማስገባት የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡

የሪፎርሙ ቀዳሚ ግብ ዘመናዊ፣ ብቁ እና ገለልተኛ ተቋም በመገንባት በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እና በዘርፋችን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ፍሰታቸውን የጠበቁ፣ ከቢሮክራሲያዊ መጓተት የጸዱና በቴክኖሎጂ የተደገፉ በማድረግ የዜጎችን አመኔታ እና እርካታ ማሳደግ ነው። በተጨማሪም ሪፎርሙ ከፌዴራል እስከ ከተሞች ያለውን አደረጃጀት ተናባቢ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን በማድረግ ብቁ እና ትውልድን የሚሻገሩ ተቋማትን ለመገንባት ያስችላል። ይህም የተሟላ፣ የሚናበብ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ለመገንባት ያስችላል። አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ በመታገዛቸው የተገልጋይ እርካታ ይጨምራል፤ የሙስና እና ብልሹ አሰራር እድሎች ይዘጋሉ። ሁሉም ተልዕኮዎች በላቀ የታማኝነት መንፈስ፣ በ"ጊዜ የለንም" ስሜት (sense of urgency) እና በውጤታማነት የሚከናወኑ ይሆናል። ይህም የመንግስትን ወጪና ጊዜ በመቆጠብ የዜጎችን እርካታ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ "ለትክክለኛው ቦታ ትክክለኛውን ባለሙያ እና አመራር" በብቃት ላይ ተመስርቶ በመመደብ፣ ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ዘመናዊ እና ውጤታማ ተቋም መገንባት ዋነኛው ግባችን ነው። ይህም ዜጎችን በላቀ ብቃት ማገልገል የሚችል እና ለሚነሱ ቅሬታዎች ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል። በተለይ ከመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የፖሊሲ አምዶች ስር ከተቀመጡት ተግባራት መካከል አምድ 3 የመንግሥት ሠራተኞች የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት መገንባትና የማስፈጸም አቅምን ማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጡት ተግባራት ዋነኛው ሲሆን፤ በዚህ አምድ ውስጥ ከተካተቱት ዋና ዋና ሥራዎች ማለትም ሥርዓተ ስልጠናዎች (Curriculum) መቅረፅ፤ የስልጠና ሞጁል ዝግጅትና አቅም ግንባታ ሥራዎች፤ የብቃት ምዘና ብሉ ፕሪንት እና የፈተና ጥያቄ ዝግጅት፤ ሠራተኞችን መመዘንና ውጤት የማሳወቅ ሥራዎች በሚቀጥሉት አራት ወራት ለማጠናቀቅ እና በምዘና ውጤት መሠረት ተከታታይ የአቅም ግንባታና የሥልጠና መርሀ ግብሮችን በጋራ መተግበር የግድ ይለናል፡፡

እነዚህን ተግባራት በተቀመጠላቸው ጊዜ እና የጥራት ደረጃ ለማዘጋጀት ከውስጥ አቅም ባሻገር ከከፍተኛ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እና በትብብር መስራት አስፈላጊ ነው። በዚህም መሰረት ሚኒስቴር መ/ቤቱ ከተለያዩ አራት ከፍተኛ የት/ርት እና ስልጠና ተቋማት (የአዲስ አበባ ዩኒቨሪሲቲ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና የብቃት እና ሥራ አመራር ኢኒስቲትዩት) ጋር ዛሬ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

በቀጣይ ከፌደራል የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ኢኒስቲትዩት ጋር በተመሳሳይ ይፈራረማል።

ዛሬ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት አጠቃላይ ማዕቀፍ ሲሆን በቀጣይ የሚኒስቴር መ/ቤታችን እና ተጠሪ ተቋማት እንደየባህሪያቸው እና እንደየሥራ ስፋታቸው ከእነዚህ ተቋማት ጋር ውል የሚፈርሙ ይሆናል።

መረጃው Ministry of Urban and Infrastructure/Ethiopia ነው።

በኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ አስደናቂ ሥራን እየሠራች ካለችው ከሰሜን ወሎዋ መናገሻ ከወልዲያ ከተማ አስተዳደር የዞናችን ከተሞች ብዙ ተሞክሮዎችንና ትምርህቶችን ሊወስዱ ይገባል።
17/12/2025

በኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ አስደናቂ ሥራን እየሠራች ካለችው ከሰሜን ወሎዋ መናገሻ ከወልዲያ ከተማ አስተዳደር የዞናችን ከተሞች ብዙ ተሞክሮዎችንና ትምርህቶችን ሊወስዱ ይገባል።

ዘላቂ የቤት ልማት ፕሮግራምን ዕውን ለማድረግ በተዘጋጀ ረቂቅ የፖሊሲ ሠነድ ላይ ምክክር ተደረገበከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር አማካኝነት በተዘጋጀ ረቂቅ የቤት ልማት ፖሊሲ ሠነድ ላይ አነስ...
17/12/2025

ዘላቂ የቤት ልማት ፕሮግራምን ዕውን ለማድረግ በተዘጋጀ ረቂቅ የፖሊሲ ሠነድ ላይ ምክክር ተደረገ

በከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር አማካኝነት በተዘጋጀ ረቂቅ የቤት ልማት ፖሊሲ ሠነድ ላይ አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት በተካተተ የቤት ልማት ፕሮግራም ከሪል እስቴት አልሚዎች ጋር የሚመክር የግብዓት ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ተካሄደ፡፡

መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ታላቁን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ባስመረቁበት ወቅት በይፋ እንደተናገሩት የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታን በቀጣዮቹ 5 ዓመታት ዕውን ለማድረግ የተያዘውን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ የተዘጋጀ ረቂቅ ፖሊሲ እንደሆነ ገልጸው ከአሁን በፊት የቤት ልማት ፖሊሲ እንዳልነበረና የቤት ልማቱ እንደ አንድ ፕሮግራም የተያዘ እንደነበር ገልጸው መድረኩ ግብኣት ለማሰባሰብና ረቂቅ ፖሊሲውን ለማዳበር ያለመ እንደሆነ በማስታወስ ለዕቅዱ ዕውን መሆን የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ የማይተካ ሜና ስላለው ተሳታፊዎች ያልተገደበ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ጋብዘዋል፡፡

የመክፈቻ ንግግሩን ተከትሎ የተዘጋጀውን ረቂቅ ሠነድ ያቀረቡት በከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚው አቶ ፀጋዬ ሞሼ የፖሊሲውን ዝርዝር ጉዳይ ሲያቀርቡ እንደተናገሩት ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች የመኖሪያ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ 8 የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለይቶ ያስቀመጠ እንደሆነና የቤት ልማት ፋይናንስን፣ የመሬት አቅርቦትን፣ አቅም ያገናዘበ ቤት መገንባትን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ መጠቀምን፣ የገጠር ቀበሌዎችንና ሁለተኛ ከተሞችን ታሳቢ ያደረገ መሆንን፣የመሠረተ-ልማት መሟላትን፣ የቤት ፈላጊዎችን የተጠናከረ መረጃ መያዝን እና ጠንካራ የቤት አቅርቦት ግብይት ስርዓትን ያካተተ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም የፖሊሲው ዓላማ ተገማችና ብቁ የቤት አቅርቦትን 91 በመቶ ለሚሆነው ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ላለው የህብረተሰብ ክፍላችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ እንደሆነና የሚገነቡት ቤቶችም በ5 የቤት ልማት አማራጮች እንደሚገነቡና የተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን ተጠቅሞ በተዘጋጀው ዲዛይን መሠረት ግንባታው የሚከናወን እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በተደረገው የጋራ ውይይት በርካታ ግብዓቶች የተገኙ ሲሆን የፖሊሲው በአጠረ-ጊዜ እንዲህ በተደራጀ መልኩ ተዘጋጅቶ መቅረቡና የግል ባለሀብቱን ሚና ያጎላ መሆኑ፣ የፋይናንስ ምንጮችም ተለይቶ የሚቀርብበት ዕድል መፈጠሩ እና የግል ባለሀብቱ አቅሙን አቀናጅቶ እንዲጠቀም ዕድል መስጠቱ የሚበረታታና አስደሳች መሆኑን አድንቀው የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መሆቸውን ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም መድረኩን የመሩት ክቡራን ሚኒስትር ዴኤታዎች በሰጡት የማጠቃለያ አስተያየት መርሃ-ግብሩ የተጠናቀቀ ሲሆን ክቡር የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) የተነሱ ነጥቦች ሁሉ ጠቃሚዎችና ፖሊሲውን ለማዳበር የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸው በግንባታው ሂደት የምንፈጥረው አቅም በጣም ከፍተኛና ከቤት ግንባታ ባለፈ ለሀገር ግንባታው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችል እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ክብርት ወ/ሮ ሔለንም በበኩላቸው የፕሮጀክቱ ሌጋሲ ከሀገርና ከህዝብ ዕድገት ጋር የሚቀጥል እንደሆነ ገልጸው የቴክኖሎጂውን ችግር በመፍታት የህብረተሰቡን ችግር መፍታት እንደሚቻል ተናግረው ሀገርን በዘላቂነት መገንባት ለግል ሴክተሩ የተሰጠ ኃላፊነት ነውም ብለዋል፡፡

መረጃው Ministry of Urban and Infrastructure/Ethiopia ነው።

የሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ የአምስት ወራት የተግባር አፈጻጸም ገመገመ! በከተማና በመሠረተ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶች ተለይተውም የቀጣይ የአፈጻጸም አቅጣጫዎች ተሰጥተውባ...
13/12/2025

የሰሜን ወሎ ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ የአምስት ወራት የተግባር አፈጻጸም ገመገመ!

በከተማና በመሠረተ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶች ተለይተውም የቀጣይ የአፈጻጸም አቅጣጫዎች ተሰጥተውባቸዋል!

(ሰሜን ወሎ ከ.መ.ል - ታኅሣሥ 4/2018 ዓም - ወልድያ)

የሰሜን ወሎ ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የአምስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን ከከተማና ወረዳ አስተዳደሮች የከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤቶች፣ ከመሪና ንዑስ ማ/ቤቶች እንዲሁም ከታዳጊ ከተሞች ኃላፊዎችና ከመምሪያው የማኔጅመንት አባላት ጋር በጋራ ገምግሟል።

በግምገማው ወቅት ከተሰብሳቢዎች በተሰጡ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ላይ የመምሪያው ኃላፊ አቶ መኮንን የሱፍ ምላሽ እና ግልጽ የቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

አቶ መኮንን በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች በአስቸኳይ መፈታት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ሊሆኑ ይገባል ያሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በሰፊው አብራርተዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎችን እርካታ በመጨመር አገልግሎቱን ፈጣን፣ ግልፅና ፍታሃዊ ማድረግና ማሳደግ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም፣ ከኮሪደር ልማት አጀማመርና አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ያለውን ሂደት ማጠናከር፣ ገቢን ሙሉ በሙሉ የገቢ አቅምን አሟጦ መሰብሰብና የማዘጋጃ ቤታዊ ኦዲትን በወቅቱ ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በመሠረተ ልማት ዘርፍም የህብረተሰብ ተሳትፎን ማጠናከር እና የመሠረተ ልማት ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ እንዲሁም የጥራት ደረጃቸውን ጠብቀው በማሠራት ህዝብን ተጠቃሚ ማድረግ፣ የሚገነቡ ግንባታዎችን በዲዛይናቸውና ከፕላን ምድቡ ጋር ተስማሚ ሆነው እንዲገነቡ ከማድረግ በተጨማሪ ከተሞች ጽዱ ውብና ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ ቀጣይ ተቀዳሚ ሥራ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

አያይዘውም የተጀመሩ የመሬት መረጃን በዲጂታል መንገድ የማደራጀት ሥራ በሁሉም ከተሞች እንዲተገበር ማድረግና የቤቶችን መረጃ ዲጂታላይዝ አድርጎ መያዝን በተመለከተ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተው እነዚህም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን ሊሆኑ ይገባል በማለት አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የመምሪያ ኃላፊው የከተማ አስተዳደሮች፣ ወረዳዎችና የመምሪያው አካላት የተቀናጀ ሥራ በመሥራት ሁሉንም በተዋረድ ያለ ሠራተኛ የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠናን እንዲወስዱ በማድረግ እና ፋይዳ (የዲጂታል) መታወቂያ እንዲይዙ በማድረግ ወቅቱን ጠብቆ ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የነጭ ሪቫንን ሳምንትን ምክንያት በማድረግ ከሰሜን ወሎ ዞን 3ኛ ዙር መካከለኛ አመራር ሰልጣኞች 130 ሺህ ብር ተሰበሰበ።ወልድያ:- ታህሳስ 03/2018 ዓ/ም (ሰሜን ወሎ ኮሙኒኬሽን) ከሰሜ...
12/12/2025

የነጭ ሪቫንን ሳምንትን ምክንያት በማድረግ ከሰሜን ወሎ ዞን 3ኛ ዙር መካከለኛ አመራር ሰልጣኞች 130 ሺህ ብር ተሰበሰበ።

ወልድያ:- ታህሳስ 03/2018 ዓ/ም (ሰሜን ወሎ ኮሙኒኬሽን) ከሰሜን ወሎ ዞን 3ኛ ዙር የመካከለኛ አመራር ሰልጣኞች "እኔም ለእህቴ የድርሻየን እወጣለሁ በሚል" እሳቤ 130 ሺህ ብር ተሰብስቦ ለጉባለፍቶ ወረዳ ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሪያ እንድውል ድጋፍ ተደረገ።

ድጋፉን የጉባለፍቶ ወረዳ አስተዳዳር ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ተረክበዋል።

የተሰበሰበው ገንዘብም "በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ "በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ሶስተኛ ዙር ስልጠና በወልድያ ከተማ ሲከታተሉ ከነበሩ በሰሜን ወሎ ዞን ከሚገኙ የከተማ እና የወረዳ አመራሮች በየቡድን ውይይታቸው የተሰበሰበ ነው።

በድጋፍ ርክክቡ ወቅት መልዕክት ያስተላለፉት የሰሜን ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሙስጦፋ ፓርቲያችን ሰው ተኮር በመሆኑ ይኸ ድጋፍ ለታለመለት ዓላማ እንድውል አሳስበዋል።

"ተቋሙ ከጥቃቅን ሥራ በመላቀቅ ወደ ስትራቴጂክ ጉዳዮች በመግባት የከተማና መሠረተ ልማት ዘርፎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል"ዶ/ር ሞላ መልካሙየአማራ ክልል ከተማና...
10/12/2025

"ተቋሙ ከጥቃቅን ሥራ በመላቀቅ ወደ ስትራቴጂክ ጉዳዮች በመግባት የከተማና መሠረተ ልማት ዘርፎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል"
ዶ/ር ሞላ መልካሙ
የአማራ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ

የአማራ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ4ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ከቢሮው ሠራተኞች ጋር አካሂዷል። ተቋሙ ከጥቃቅን ሥራ በመላቀቅ ወደ ስትራቴጂክ ጉዳዮች በመግባት የከተማና መሠረተ ልማት ዘርፎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሞላ ዞኖችንና ከተሞችን የመስክ ድጋፍና ክትትል በማድረግ አዳጊ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግሥት ከተሞችን የሚያይበት ሁኔታ ተቀይሯል፤ ከተሞች በደንብ ከተመሩ የዕድገት ማዕከላት ይሆናሉ ያሉት ዶ/ር ሞላ ይህ ካልሆነ ግን ከተሞች ችግሮች የሚባባሱባቸዉ እንደሚሆኑ አሳስበዋል።

የተቋሙ የርብርብ ማዕከላት የመኖሪያ ቤት ልማትና የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት እንዲሁም ከተሞች አረንጓዴና ፅዱ ለነዋሪዎች ምቹ ማድረግ ነዉ ያሉት ቢሮ ኅላፊዉ መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
ከተሞች ከማንዋል አሰራር በመዉጣት ወደ ዘመናዊ አሰራር በመግባት የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠትና ህገ ወጥነትን መከላከል አለባቸው ያሉት ዶ/ር ሞላ የገጠር ከተማ ትስስር ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መስረት ለተለያዩ ልማቶች በማዋል ጥቅም እንዲሰጡ ማድረግ ይገባል ሲሉ አጽንኦት ሰጠው አሳስበዋል።
በመጨረሻም ዶ/ር ሞላ አክለዉ እንዳሉት የቢሮውን የፀደቁ የሕግ ማዕቀፎች ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግና በሂደት ላይ ያሉ ትን በማኔጅመንት እየተገመገሙ የህግ አካል ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል።

አቶ እያሱ አድማሱ የዕቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የቢሮዉን የ2018 በጀት ዓመት የ4 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።

ዘጋቢ፡ ሙሉጌታ ስመኝ

Address

Woldia

Telephone

+251333310324

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሰሜን ወሎ ዞን ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የሰሜን ወሎ ዞን ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ:

Share