Bayra Koysha Woreda Government Communication/የባይራ ኮይሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Bayra Koysha Woreda Government Communication/የባይራ ኮይሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

Bayra Koysha Woreda Government Communication/የባይራ ኮይሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bayra Koysha Woreda Government Communication/የባይራ ኮይሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን, Government Organization, Bayra koysha woreda, Sodo.

ማሰታወቂያ********************ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት ለወላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ርከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኛ ለመሆን ተወዳድረው በጽሑፍ እና በቃል ፈተና የተሻለ ውጤት በማምጣታቸ...
29/05/2026

ማሰታወቂያ
********************

ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት ለወላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ርከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኛ ለመሆን ተወዳድረው በጽሑፍ እና በቃል ፈተና የተሻለ ውጤት በማምጣታቸው ለህዝብ አስተያየት የቀረቡ ዕጩዎች ናቸው፡፡

የዳኝነት ሥራ ከፍተኛ ኃላፊነት የሚጣልበት ከመሆኑ አንጻርየተሻለ ሥነ-ምግባር ያለውን ሰው የሚፈልግ መሆኑ እሙን ነው፡፡

ስለሆነም ከዛሬ ማለትም 21/09/18 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ቀን 25/09/18 ዓ.ም ድረስ በዕጩ ዳኞች ላይ የሥነ-ምግባር ግድፈት፣ ችግር ወይም ጥሰት ስለመኖሩ ማስረጃ ካላችሁ ለከፍተኛ ፍ/ቤት ንዑስ ዳኝነት አስ/ርጉባኤ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ አስተያየት እንድትሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

በተጨማሪ ሌላ ጥቆማ ወይም አስተያየት ካላችሁ ከዚህ በታች በተዘረዘሩ ስልክ ቁጥሮች እንዲሁም በተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ጥቆማ/አስተያየት እንድትሰጡ በከፍተኛ ፍ/ቤት ስም በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል - ቦርዱወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 21፣ 2018 (ወዞመኮአ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...
29/05/2026

ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል - ቦርዱ

ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 21፣ 2018 (ወዞመኮአ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ።

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት፤ ለምርጫው 54 ሚሊየን 571 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል።

የምርጫውን ሂደት የአፍሪካ ህብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ልዑካን እንደሚታዘቡ ገልጸዋል።

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።

የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች ሥራቸውን ጀምረዋል - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ************************ከቦርዱ ፈቃድ ያገኙ የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች ምርጫውን ለመታዘብ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው ሥራ...
29/05/2026

የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች ሥራቸውን ጀምረዋል - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
************************

ከቦርዱ ፈቃድ ያገኙ የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች ምርጫውን ለመታዘብ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው ሥራ መጀመራቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ የአፍሪካ ሕብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካዮቻቸውን ልከው ሥራ ጀምረዋል።

ሁለቱ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በተጨማሪ በሀገር ውስጥ የተደራጁ 55 ሲቪክ ማኅበራትም ፈቃድ ወስደው ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል።

55ቱ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ 1 ሺህ 562 የምርጫ ታዛቢዎችን ማሰማራታቸውንም ነው ሰብሳቢዋ የጠቀሱት።

59 አባላት ያሉት የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት አሁሩ ኬንያታ እየተመራ ሥራውን እንደሚሠራ አስታውቀዋል።

ኢጋድ በበኩሉ 26 አባላት ያሉት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን እንደሚያሰማራ ጠቅሰዋል።

በአዲስ አበባ የሚገኙ ዲፕሎማቶችም የምርጫውን ሂደት ተዘዋውረው እንዲመለከቱ የእንግድነት ማለፊያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል ሰብሳቢዋ።

#ኢትዮጵያ #ዴሞክራሲ #ምርጫ Ethiopian Broadcasting Corporation

29/05/2026
በየትኛውም የምርጫ ጣቢያ 200 ሜትር ርቀት ውስጥ ሆኖ ለመዘገብ ባጅ የተሰጣቸው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚከተሉትን ግዴታዎች ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡-👉 የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባህ...
29/05/2026

በየትኛውም የምርጫ ጣቢያ 200 ሜትር ርቀት ውስጥ ሆኖ ለመዘገብ ባጅ የተሰጣቸው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚከተሉትን ግዴታዎች ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡-

👉 የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባህልና ልምድ ማክበር፤

👉 በቦርዱ የተሰጠውን የመታወቂያ ባጅ በሚታይ መልኩ በመያዝ መንቀሳቀስ፤

👉 የመራጭ ምዝገባ መረጃዎችን በሰነድ ላይ ሲሰፍሩ ወይም መራጩ በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የምርጫ ምልክት ሲያደርግ አለመቅረጽ ወይም ፎቶግራፍ አለማንሣት፤

👉 ግለሰቡ በግልጽ እየተቃወመው መራጮችን እና ሌላ ማንኛውንም ሰው ፎቶ ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል አለመቅረጽ እና ቃለ-መጠይቅ አለማድረግ፤

👉 የመራጮች ግላዊ ማንነትን በሚነካ አኳኃን መዝገብ፣ የመራጮችን ምዝገባ መታወቂያ ወይም ማንኛውንም ተመሳሳይ ሰነድ በፊልም አለመቅረጽ፣ ፎቶግራፍ አለማንሳት ወይም ኮፒ አለማድረግ፤

👉 የሕዝብን ሰብዓዊ መብትና መሠረታዊ ነፃነቶች ማክበር፤

👉 የቦርዱን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፀጥታና የደኅንነት እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት አካላትን ሚና እና ሥልጣን ማክበር፣

👉 ለምርጫ አስፈጻሚዎች ስለ ኃላፊነታቸው ምክር ወይም መመሪያ አለመስጠት፣

👉 መራጩ ድምፁን ለማን እንደሰጠ አለመጠየቅ፣

👉 የሕግ ጉዳዮችን በራስ አለመተርጎም እና የምርጫ ሂደትን የሚመለከት ሕጋዊ ያልሆነ መረጃ ወይም መመሪያ አለማስተላለፍ፣

👉 ለድምፅ መስጫ የተከለለ ቦታ ካሜራም ሆነ ሌላ የድምፅ ወይም የምስል መቅጃ መሣሪያ አለመጠቀም፣

👉 ከአድሎና ከወገንተኝነት በፀዳ አኳኋን ተግባራትን ማከናወን ይጠቀሳሉ።

የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልበቅሎ ሰኞ ፣ ግንቦት 21፣ 2018 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡የክልሉ ምርጫ ጽሕፈት ቤት ...
29/05/2026

የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል

በቅሎ ሰኞ ፣ ግንቦት 21፣ 2018 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

የክልሉ ምርጫ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪ አቶ አብርሃም አንጁሎ እንደገለጹት÷ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በመጭው ሰኞ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉን አቀፍ ዝግጅት ተደርጓል፡፡

በክልሉ የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑን የገለጹት አስተባባሪው÷ የቁሳቁስ ስርጭቱ በጥንቃቄና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በጸጥታ ኃይል ታጅቦ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የድምጽ መስጫ ወረቀትን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሰራጨት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ጽሕፈት ቤቱ በተደራጀ መልኩ የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ በሚገኙ 56 የምርጫ ክልሎች 3 ሺህ 941 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን አንስተው÷ በበሁሉም ምርጫ ጣቢያዎቹ የፊታችን ሰኞ ድምጽ እንደሚሰጥ አመልክተዋል።

ዜጎችም በምርጫው ዕለት የነቃ ተሰትፎ በማድረግ በወሰዱት ካርድ ድምጽ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የወላይታ ዲቻ ሰፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ  አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አሰተላለፉ።ክቡራን የስፖርት ቤተሰቦች፣ የወላይታ ህዝብ፣...
28/05/2026

የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የወላይታ ዲቻ ሰፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አሰተላለፉ።

ክቡራን የስፖርት ቤተሰቦች፣ የወላይታ ህዝብ፣ የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች፣ ውድ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች፤

የወላይታ ድቻ የ2018 ዓ.ም የደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የኢትዮጵያ ወንዶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ የተሰማኝ ደስታ ከፍተኛ ነው።

ይህ ድል የአንድ ቡድን ውጤት ብቻ ሳይሆን የወላይታ ህዝብ ኩራት፣ የወጣቶቻችን ተስፋ፣ የጠንካራ ስራና የትጋት ፍሬ ነው።

በዘንድሮው ውድድር ስድስት ክለቦች በተሳተፉበት ፉክክር ወላይታ ድቻ ከ9 ጨዋታዎች 21 ነጥብ በማሰባሰብ ሻምፒዮን መሆኑ ታላቅ ታሪካዊ ስኬት ነው።
ይህ ድል በተጫዋቾች ጥንካሬ፣ በአሰልጣኞች ብቃት፣ በደጋፊዎች ድጋፍና በአመራሩ ቅን ትብብር የተገኘ ውጤት ነው።

ስፖርት ከውድድርና ከዋንጫ በላይ ትልቅ ሀገራዊና ማህበራዊ ፋይዳ አለው።
ስፖርት ወጣቶችን ከአሉታዊ ተግባራት ይጠብቃል፣ የዲሲፕሊን ባህል ያሳድጋል፣ አንድነትንና መተባበርን ያጠናክራል። በተጨማሪም የአካልና የአእምሮ ጤናን ያጎለብታል፣ ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴም አስተዋፅኦ ያደርጋል።

ዛሬ ወላይታ ድቻ ያስመዘገበው ድል ለብዙ ወጣቶች “በትጋት ከሰራን ወደ ስኬት መድረስ እንችላለን” የሚል ትልቅ መልዕክት ያስተላልፋል ድል ነው።
የወላይታ ህዝብ ለስፖርት ያለው ፍቅርና ድጋፍ የዛሬው ውጤት መሠረት ነው።
እኛም እንደ አመራር የስፖርት መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ ወጣቶች ችሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር እና ክለቦቻችንን በተሻለ አቅም ለማጠናከር ያለንን ሁሉንም ድጋፍ እንቀጥላለን።

በመጨረሻም ለዚህ ታሪካዊ ድል አስተዋፅኦ ላደረጉ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች፣ የክለቡ አመራሮች፣ ደጋፊዎችና መላው የወላይታ ህዝብ ከልብ አመሠግናለሁ።
ይህ ድል የመጨረሻ አይደለም፤ ወላይታ ድቻ ወደ ተጨማሪ ድሎችና ከፍታዎች እንደሚጓዝ ሙሉ እምነት አለኝ።
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ!
ኑናራ ድያጌ ኡባ ጦኒያጋ!

አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ
ወላይታ ዞን ም/ አስተዳዳሪና የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊና
የዲቻ ርፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ

7ተኛዉ አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ ከዞን ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተመደቡ አባላት የሥራ ስምሪት እና ኦረንተሽን ተሰጠወላይታ ሶዶ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም (ወዞመኮአ)...
28/05/2026

7ተኛዉ አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ ከዞን ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተመደቡ አባላት የሥራ ስምሪት እና ኦረንተሽን ተሰጠ

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም (ወዞመኮአ)

ለሰባተኛዉ አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ የተመደቡ የፖሊስ አባላት የሥራ ስምሪት እና ኦረንተሽን የሰጡት የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸዉ ምርጫዉ በሠላም እንዲጠናቀቅ በእያንዳንዱ ምርጫ ጣቢያ የተመደቡ የፖሊስ አባላት ነፃ እና ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸዉ ተናግረዋል።

ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ድህረ ምርጫ ድረስ በተመደባችበት ምርጫ ጣቢያ የተሰጠዉን የሥራ ኃላፊነት ስትወጡ በቅንነትና በታማኝነት የምርጫ ህጉን ባከበረ ሁኔታ መሆን እንዳለብን አጽንኦት ሰጥተዋል።

ምርጫዉ በሠላም እንዲጠናቀቅ የምርጫ ቁሳቁስ ጥበቃ በተጠናከረ ሁኔታ መሆን እንዳለበት ያነሱ አዛዡ በሁሉም ምርጫ ጣቢያ የተመደቡ የፖሊስ አባላት ከግንቦት 21/2018 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ምርጫ ጣቢያ በመግባት የአካባቢዉን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በመተዋወቅ የሥራ ግዴታዉን መወጣት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የመራጩን ህዝብ፣የፖሊቲካ ፓርቲዎች፣የዕጩ ተፎካካሪዎች፣የምርጫ አስፈጻሚዎች ደህንነት እና የምርጫ ቁሳቁስ በሙሉ በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ እንዳለበት ተናግረዋል።

የጸጥታ ሥራ ሲሰራ ፍጹም ገለልተኛ መሆን ከማንኛዉም ፓርቲ ዉግንና ነጻ በመሆን በገለልተኝነት ከአድልዎ ነጻ በመሆን ሁሉንም እኩል ማየት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ሁሉም ተፎካካሪ ለእኛ እኩል ናቸዉ ያሉት አዛዡ እኩል ማስተናገድ እኩል እይታ ማየት የምርጫ ሥነ ምግባር ህግ ብቻ መሠረት አድርጎ መሠራት አለበት ብለዋል።

በምርጫ ጣቢያ የተመደቡ አመራርና አባላት የሥራ ምደባ የሰጡት የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ማህረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ዘዉዱ ኩሩ በበኩላቸዉ ሁሉም የተጣለበትን የሥራ ኃላፊነት በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲወጡ አሳስበዋል።

በመጨረሻም በምርጫ ጣቢያ የተመደቡ የፖሊስ አመራርና አባላት ሠላማዊ ምርጫ እንዲካሄድ የተጣለባቸዉን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንደሆኑ በመግለጽ የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ ያላቸዉን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸዉን ጨምሮ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ማኔጅሜንት አካላት እና የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አባላት ተገኝተዋል።

የወላይታ ድቻ  የወንዶች ቡድን ቮሊቦል የኢትዮጵያ ወንዶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፈሰር ሳሙኤል ተሰማ የእንኳን ደስ አላችሁ መ...
28/05/2026

የወላይታ ድቻ የወንዶች ቡድን ቮሊቦል
የኢትዮጵያ ወንዶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፈሰር ሳሙኤል ተሰማ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ ።

"የወላይታ ድቻ የወንዶች ቮሊቦል ቡድን የ2018 የደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የኢትዮጵያ ወንዶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ ለቮሊቦል ቡድኑ፣ ለደጋፊዎች፣ ለክለቡ አመራሮች እንዲሁም ለአጠቃላይ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ።

ቡድኑ በዘንድሮው የደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የኢትዮጵያ ወንዶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ከስድስት ተሳታፊ ቡድኖች አንደኛ በመሆን የሻምፕዮንነት ድል ተቀዳጅቷል።

ይህ ውጤት እንዲያው የተገኘ ሳይሆን የትጋት፣ የቁርጠኝነት፣ የአልሸነፍ ባይነትና የአንድነት ፍሬ ነው።

የቡድኖቻችን የአሸናፊነት ሚስጢር የዞኑን ህዝብ በመወከል ቅድሚያ ለወከሉት ህዝብ በሚያደርጉት ትግል እንጂ በዋዛ የተገኘ ባለመሆኑ በቡድኑ ውጤት ኮርተናል።

በመሆኑም በሁሉም መስክ ተስፋ ባለመቁረጥ፣ በትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሁም በአንደነት ብንቆም ማሸነፍ እንደምንችል ማሳያ ነው፣ በመሆኑም በሁሉም ረገድ በአንድነት መቆም ወሳኝ ነው።

ለውጤቱ መሳካት ለደከሙ የቡድኑ ተጫዋቾች፣ አመራሮችና ደጋፊዎች ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

የቡድኑ ድል ቀጣይነት እንዲኖረው የዞኑ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጣለሁ።"

የወላይታ ዞን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት  የተሰጠ መግለጫ!!!የወላይታ ዞን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በዞኑ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎ...
28/05/2026

የወላይታ ዞን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ!!!

የወላይታ ዞን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በዞኑ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች በጋራ ጉዳዮች ላይ የሚመክሩበት፣ የሃሳብ ልዩነቶችን በውይይት የሚፈቱበትና የአካባቢውን ሠላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚያግዙበት መድረክ ነው።

የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ዓላማ በዞኑ ዘላቂ ሠላምና የፖለቲካ መረጋጋት እንዲሰፍን ማድረግ፣ የሕዝብን አንድነት መጠበቅ እና የፓርቲዎች የፖለቲካ ምህዳር በማስፋት በፍትሃዊነትና በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ነው።

ምክር ቤቱ በአካባቢው የፖለቲካ ሂደት ላይ የጎላ እና በጎ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል።

በተለይም በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሊፈጠሩ የሚችሉ ግጭቶችንና አለመግባባቶችን አስቀድሞ በመከላከል፣ የዴሞክራሲ ባህል እንዲዳብርና የፖለቲካ ምህዳሩ ጤናማ በሆነ መንገድ እንዲመራ በማድረግ ረገድ የምክር ቤቱ ሚና የጎላ ነው።

የ7ኛውን አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የጋራ ምክር ቤቱ ሰፊ የምርጫ ቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

ምርጫው ፍፁም ሠላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን ከምርጫ አስፈጻሚ አካላት፣ ከጸጥታ መዋቅሩና ከሕዝብ ጋር የተቀናጀ ዝግጅት የተደረገ ሲሆን፣ የጋራ ምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎችም ለአገራዊ ግብ ስኬት በቁርጠኝነት እየሰሩ ይገኛሉ።

የጋራ ምክር ቤቱ 7ኛውን አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሚከተሉትን 5 ዋና ዋና ነጥቦች ለሕዝብና ለሚዲያ አካላት በዝርዝር ያሳውቃል፡-

1.ሠላማዊ የመራጮች ምዝገባ መከናወኑ፡-
በወላይታ ዞን በሚገኙ በ13 የምርጫ ክልሎች እና 980 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ ሂደት ፍፁም ሰላማዊ፣ ነጻና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ተከናውኗል። ሕዝቡም ሂደቱን በሰከነ መንገድ ደግፎታል።

2.የምርጫ ቅስቀሳ በሠላም መጠናቀቁ፡-
በዞኑ ውስጥ ሲካሄድ የነበረው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ (ካምፔይን) ያለምንም የጸጥታ ችግር ተፈጽሟል፡፡ በአንዳንድ ምርጫ ክልሎች የሚፈጠሩ ጥቃቂን ችግሮችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር እየተፈታ የምርጫ ቅስቀሳው በስኬት መጠናቀቁን ምክር ቤቱ በታላቅ አክብሮትና ኩራት ይገልፃል።

3.የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ኃላፊነት፡-
ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ሁሉም ዜጎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሃይማኖት አባቶችና ባለድርሻ አካላት እጅ ለእጅ ተያይዘውና ተቀናጅተው ታሪካዊ አሻራቸውን እንዲያሳርፉና ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ እናቀርባለን።

4.የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ማክበር፡-
ሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎችና ደጋፊዎቻቸው በምርጫ ስነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2013 መሠረት የተጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነትና ግዴታ በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸውም በጥብቅ ያሳስባል።

5.የዜግነት ግዴታን በምርጫ ዕለት መወጣት፡-
የምርጫ ካርድ የወሰዳችሁ የዞናችን ሕዝቦች በሙሉ፣ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በነቂስ ወጥታችሁ "አገሬን ይመራል፤ ካለችበት ፈተና ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሻግራል!!" ለምትሉት ፓርቲ በነፃነት ድምፃችሁን በመስጠት የዜግነት ግዴታችሁን እንድትወጡ ምክር ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

“7ኛው አገራዊ ምርጫ ፍፁም ሠላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሥነ-ምግባራዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ የዜጎችና የባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ወሳኝ ነው!!”

የወላይታ ዞን ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

ግንቦት 20/2018 ዓ/ም
ወላይታ ሶዶ፣

በኦፋ ወረዳ ከ255 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባ 115 ሄክታር ማሳ የሚያለማ  የጋልዳ ሶላር መስኖ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል። በወረዳው የገሱባ-ጋልዳ-ጋርቤ 15 ኪ....
27/05/2026

በኦፋ ወረዳ ከ255 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባ 115 ሄክታር ማሳ የሚያለማ
የጋልዳ ሶላር መስኖ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በወረዳው የገሱባ-ጋልዳ-ጋርቤ 15 ኪ.ሜትር ሎት1 መንገድና ከ64.4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከ40 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም (ወዞመኮአ)

በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የሥራ መመሪያ የሰጡት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሪሁን ፍቅሩ የመንገድ ፕሮጀክቱን መጠናቀቅ አስመልክቶ የዚህ አካባቢ ህዝብ በመንገድ ችግር ምክንያት ሲሰቃይ የነበረ በመሆኑ አሁን ለዚህ በመብቃቱ እጅግ ደስ ብሎኛል ብለዋል።

ዶክተር መሪሁን አያይዘውም ዛሬ ሥራው በይፋ የሚጀመረው የጋልዳ ሶላር መስኖ ከግቡ እንዲደርስ የሁሉንም ትብብር ይጠይቃል ሲሉ ተናግረዋል።

መስኖን መገንባት ህይወትን ማስቀጠል ነው ያሉት ኃላፊው የመስኖና የውሃ ተቋማትን መገንባት ህይወትን የማስቀጠል ዓላማ የያዘ ነው ሲሉ ተናግረው ከሁሉም ነገር ቅድሚያ ሰጥተን የምናስፈጽመው ነው ሲሉ አስረድተዋል።

መተባበርን ቁርጠኝነትን እና መስዋእትነትን የሚጠይቅ ነው ሁሉም በባለቤትነት ለመፈጸም መዘጋጀት እንዳለበትም ተናግረዋል።

ቢሮው ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እና ጥራት ሥራውን እንዲጨርስ የመከታተል ሥራ እንደሚሠራ እንዲሁም ሁሉም የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የመንገድ የውሃ እና የመብራት መሠረተ ልማት ችግሮችን በተመለከተ ከህዝቡ ጋር መድረክ መፈጠሩን አስታውሰው መንግሥት የታየውን ችግር ለመፍታት ባደረገው ጥረት ፕሮጀክቶቹ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር እድሬ ኢርኮ ገሱባ- ጋርቤ- ጋልዳ መንገድ ከሚመለከታቸው ጋር በመመካከር የተጀመረ ሲሆን 128 ሚሊዮን ብር ያህል ወጪ መደረጉን ተናግረዋል።

ለፕሮጀክቱ በጊዜ መጠናቀቅ ህዝቡ በአጠቃላይ ተባባሪ እንደነበርና ሥራው እንዲሳካ አስተዋጽኦ መኖሩን ተናግረዋል።

መንገድ ሲከፈት ብቃት ያላቸው አገልግሎቶች ሁሉ ይቀርባሉ ሲሉ ተናግረው ለሁሉም አገልግሎቶች መሠረት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የኦፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዲሱ ወርቁ የለውጡ መንግስት በርካታ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል ሲሉ ተናግረው የህዝባችንንም ችግሮች በቅርበት በመከታተል እየፈታ ነው ብለዋል።

በኦፋ ወረዳ ከ64.4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከ40 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል ሲሉም ተናግረው የጋልዳ ሶላር መስኖ ፕሮጀክት 255 ሚሊዮን 115 ሄክታር ከ105 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት በይፋ ሥራ እንደሚጀምር አብራርተዋል።

ለፕሮጀክቶቹ መሳካት የበኩላቸውን ለተወጡ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።

Address

Bayra Koysha Woreda
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bayra Koysha Woreda Government Communication/የባይራ ኮይሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share