በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት This is the official H/Z Wera Woreda Agri. office page where you can get all the latest info

የወተት ሀብት ልማታችን ከድህነት መዉጫና የስራ ዕድል መፍጠሪያችን;- አቶ ኡስማን ሱሩር*********በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በከምባታ ዞን ጸዳል ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒዬን ሀ...
26/05/2026

የወተት ሀብት ልማታችን ከድህነት መዉጫና የስራ ዕድል መፍጠሪያችን;- አቶ ኡስማን ሱሩር
*********
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በከምባታ ዞን ጸዳል ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒዬን ሀምበርቾ የወተት ማምረቻ፣ማቀነባበሪያና ግብይት ማዕከል ምረቃና ርክክብ ፕሮግራም ተካሄደ።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባርና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በፕሮግራሙ መክፈቻ የብልጽግና ፓርቲ የራቀዉን በማቅረብ ፣የማይቻለዉን አስችሎ ፣የከበደዉን አቅሎ ፀጋን በማልማት የህብረተሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክረን እንሰራለን ብለዋል።

አቅሞችን በማስተባበርና በማቀናጀት፣ ወደተግባር ገብቶ በመስራቱ የአርሶ አደራችንን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገት ፀጋዎቻችንን በሚገባ ማልማት እንደሚገባም አብራርተዋል።

ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በመጨመር ገበያን ለማረጋጋት የከምባታ አርሶ አደሮች ጥሩ ማሳያ እንደሆነም ተናግረዋል።

የወተት ዕሴት በመጨመር ደህንነቱና ጥራቱን የጠበቀ ምርት በማምረት ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ልማት በማስተባበር፣ በማለቅ፣ በማስቀጠል እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ ግብርና በሀገራችን ለኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠን ወሳኝ ተቋማት ዉስጥ ቀዳሚ ተቋም እንደሆነ ተናግረዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አረጋ እሼቱ በመድረኩላይ ተገኝተዉ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጲያ በሁሉም ዘርፎች እያደገች ትገኛለች ለሀገርቱን ኢኮኖሚ እድገት የጀርባ አጥንት የግብርና ዘርፍ አማራጭ የሌለዉ ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል።

ጠባብ መሬት ባለባቸዉ አከባቢዎች እንደ ከምባታ ዞን የእንስሳ ዘርፍን በሚገባ በማላቅ አርሶ አደሮች በዘርፉ ተጠቃሚ መሆን አለባቸዉ ብለዋል።

የሀምበርቾ ወተት ማምረቻ በቀን እሰከ ሁለት ሺህ ሊትር የማምረት አቅም እንዳለዉ ጠቅሰዉ ምርቱን ትርፋማ ለማድረግ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰተዉ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
በፕሮግራሙ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አኒቶ አቡቶ፣የክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ አና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩርን ጨምሮ የፌዴራል ፣የክልል፣የዞንና የወረዳ የተለያዩ አመራሮችና አርሶ አደሮች ተሳታፊ ሆነዋል።ሲል የዘገበው ሀላባ ቲቪ ነው።

በወረዳው ከተረጅነት የመለቀቅ ጉዞ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት የመለቀቅ ጉዞ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል ።በዚህም በዛሬው ዕለት...
26/05/2026

በወረዳው ከተረጅነት የመለቀቅ ጉዞ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት የመለቀቅ ጉዞ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል ።

በዚህም በዛሬው ዕለትም ለሀማጣ ቀበሌ፣ ለምዕራብ ጎርጣንቾ ቀበሌና ለሙዳ ማያፋ ቀበሌዎች በቁጣባቸው መስረት ለእርባታ የሚሆን የፍየል ግዥ በመፈጸም ርክክብ መደረጉን የዌራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል እና አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሙበሽር ዴብሶ ገልጸዋል ።

አቶ ሙበሽር በርክክቡ ላይ ተገኝተው እንደገለፁት ተጠቃሚዎች የተሰጣቸውን ድጋፍ ተጠቅመው ራሳቸውን እንዲችሉና ከድህነት ወለል በዘላቂነት እንዲወጡ ፋይዳው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

በምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም የተረጅነት እና ጠባቂነት መንፈስን በማስወገድ ዜጎች ሰርተው እንዲለወጡ የሚያግዝ ፕሮጀክት ስለመሆኑም አቶ ሙበሽር የገለፁት ።

በወረዳው አብዛኛው ማህበረሰብ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እየተሸጋገር መሆኑን ጠቅሰው ይህ የፍየል ግዥ ቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች ትልቅ አስተዋፅዖ ያበረክታል ብለዋል፡፡

ዞናችን ከለውጡ ወዲህ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የብልጽግና ጉዞዋችንን እውን ለማድረግ በርካታ የልማት ስራዎችን ጀምሮ በፍጥነት በማጠናቀቅ ምሳሌ የሚሆን ነው -የሀላባ ዞን ...
25/05/2026

ዞናችን ከለውጡ ወዲህ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የብልጽግና ጉዞዋችንን እውን ለማድረግ በርካታ የልማት ስራዎችን ጀምሮ በፍጥነት በማጠናቀቅ ምሳሌ የሚሆን ነው -
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
የተከበሩ አቶ ሙህዲን ሁሴን

25/05/2026

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ አቦክቾ ከተማ የከተማዉ መዘጋጃ ጽ/ቤትና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ምረቃ ስነስርዓት እና ሰሞኑን የሚካሄደው ሀገራዊ እና ክልላዊ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ የፕሮግራሙ ድምቀት የሆኑት የሀላባ ዞን ባህል ቡድን ጭፈራ

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ አቦክቾ ከተማ የከተማዉ መዘጋጃ ጽ/ቤትና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ምረቃ ስነስርዓት እና የፊታችን ግንቦት 24/2018 የሚካሄደው ሀገራዊ እና ክልላዊ የምርጫ ቅስቀሳ በድ...
25/05/2026

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ አቦክቾ ከተማ የከተማዉ መዘጋጃ ጽ/ቤትና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ምረቃ ስነስርዓት እና የፊታችን ግንቦት 24/2018 የሚካሄደው ሀገራዊ እና ክልላዊ የምርጫ ቅስቀሳ በድሮን እና በካሜራ የተቀረጸ ምስል

በሃላባ ዞን የለውጡ መንግስት ትሩፋት የሆነው ፕሮጀክቶችን ጀምሮ ፈጥኖ የመጨረስ ግብ ተምሳሌትነት በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ!በዌራ ወረዳ አቦኪቾ ከተማ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመር...
25/05/2026

በሃላባ ዞን የለውጡ መንግስት ትሩፋት የሆነው ፕሮጀክቶችን ጀምሮ ፈጥኖ የመጨረስ ግብ ተምሳሌትነት በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ!

በዌራ ወረዳ አቦኪቾ ከተማ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።

በዌራ ወረዳ ከ11 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት የአቦክቾ ከተማ ማዛጋጃ ቤትና የስብሰባ አደራሽ በዛሬዉ ዕለት የክልል፣የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ተመርቋል።

የሃላባ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ ሙህዲን ሁሴን በምረቃ መረሐግብሩ ላይ ተገኝተዉ ባስተላለፉት መልዕክት የአቦክቾ ከተማ በከተማነት ምስረታዉ ረዥም አመታትን እንዳስቆጠረ ገልጸዉ የማዘጋጃ ቤት ግንባታ ለከተማው ዕድገትና መሰረት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የብልጽግና ፓርቲ ጀምሮ መጨረስ ልምዱ መሆኑን የጠቀሱት አስተዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ እሳቤ ከተሞችን ማሳደግና ዉብ ማድረግ ተግባሩ እንደሆነ አብራርተዋል።

ከተማዋን በከተማነት ለማሳደግ በዉስጧ የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን የመገንባት ኃላፊነታቸዉን መወጣት እንዳለባቸዉ አብራርተዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ጀምሮ የመጨረስ ተምሳሌትነቱን በአግባቡ ስለመወጣቱ እነዝህ ፕሮጀክቶች ማሳያ ናቸዉ ብለዋል።

መንግስት የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን በተሟላ ሁኔታ ተደራሻ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ሙህዲን የአቦኪቾ ከተማን ልዩ የሚያደርገዉ የአርቶ ፍል ዉሃ የመስህብ ስፍራ መገኛና ለቱሪዝም መዳረሻነት ትልቅ ምቹ ሁኔታነት ያላት መሆኗን ተናግረዋል።

7ኛው ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትኃዊና ሰላማዊ ሆኖ እንጠናቀቅ የህብረተሰብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የለዉጡ መንግስ እንደ ሃላባ ዞን በርካታ ትሩፋቶችን እንዳሰገኘ የተናገሩት አቶ ሙህዲን ባለፉ ወራቶች የዞን አስተዳደር ህንፃ ፣የሃላባ አለም አቀፍ ስታድየም የመጀመርያ ዙር ግንባታ ፣በዌራ ወረዳ የአቦክቾ ከተማ ማዘጋጃ ቤት፣የስብሰባ አደራሽና የቁፌ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ከበርካታ ፕሮጀክቶች ዉስጥ ተጠቃሾች እንደሆኑ አብራርተዋል።

የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ከድር ኢማም የሴ በበኩላቸው የዛሬዉ ሁለቱ ፕሮጀክቶች ምረቃ ስነ ስረዓትን ልዩ የሚያደርገዉ 7ተኛዉ ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ላይ መሆኑ እጅግ አስደሳች እንደሆነ ተናግረዋል።

የዌራ ወረዳ አቦክቾ ከተማ ማዘጋጃና የስብሰባ አደራሽ በ11.5 ሚሊየን ብር ወጭ በአምስት ወራት ዉስጥ የግንባታ ሂደቱ ተጠናቆ ለምራቃ መብቃቱን አቶ ከድር ተናግረዌል።

መንግስት የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን የሟሟላት ኃላፊነቱን እንደሚወጣ የተናገሩት አቶ ከድር ከተሞችን የማሳደግና የአገልግሎት ተቋማትን በመገንባት በሟሟላት ከተማዋን ለማሳደግ የአከባቢዉ ባለሃብቶች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል ።

ፕሮጀክቶቹ ለከተማ ዕድገትና የተገልጋዩን ህብረተሰብ ወጭ፣ጉልበትና ጊዜን የሚቀንስ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የሚያቀላጥፍ እንደሆነም አብራርተዋል።

ሁለቱም ፕሮጀክቶች በአምስት ወራት የግንባታ ሂደቱ የተጠናቀቀ መሆኑን የጠቀሱት አስተዳደሩ በ11.5 ሚሊየን ብር ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በተገኝ ገንዘብ ወጪው መሸፈኑን አክለዋል።

7ተኛዉ ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፊትኀዊና ቅቡልነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አክለዋል።

በመጨረሻም ለተገኙ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች የዕዉቅና ሰርተፍኬትና ስጦታ ፕሮግራም ተካሄዷል።

በምረቃ መረሃግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት መነቴ ሙንዲኖ፣የሃላባ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ ሙህዲን ሁሴን፣የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሐመድከማል ኑሪዬ ፣የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምዘናና ጥራት ዳይሮክተሬት አቶ ራመቶ ቦካን ጨምሮ የክልል ፣የዞንና የወረዳ አመራሮች የሃገር ሽማግሌዎች፣የሃይማኖት አባቶች እንዲሁምሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Halaba Tv

25/05/2026
‎ በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በሶርጌ ቀበሌ አርሶአደር የተገኘው እርጥበት በመጠቀም በቅድመ በልግ የተዘራ ቦሎቄ ሰብል አሁናዊ ገጽታ በምስል!
22/05/2026

‎ በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በሶርጌ ቀበሌ አርሶአደር የተገኘው እርጥበት በመጠቀም በቅድመ በልግ የተዘራ ቦሎቄ ሰብል አሁናዊ ገጽታ በምስል!

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌያት በአርሶአደር ማሰልጠኛ ተቋም ላይ የጃክፍሩት (Jackfruit) ፍራፍሬ የመላመድና የማስተዋወቅ ሥራዎች እና ተከላ እየተከናወነ ይገኛል ።የጃክፍሩት ...
22/05/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌያት በአርሶአደር ማሰልጠኛ ተቋም ላይ የጃክፍሩት (Jackfruit) ፍራፍሬ የመላመድና የማስተዋወቅ ሥራዎች እና ተከላ እየተከናወነ ይገኛል ።

የጃክፍሩት ፍራፍሬ የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ፣ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ከፍ ለማድረግና የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ከመገንባት ባለፈ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ይረዳል ።

በዚህ መሠረት በዛሬው ዕለት በሀብቦ ፉራና እና በአይማሌ ቀበሌያት በአርሶአደር ማሰልጠኛ ተቋም ላይ የጃክፍሩት (Jackfruit) ፍራፍሬ ተከላ ተፈፅሟል ።

Address

Alaba K'Ulito
Shewa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share