Bachuma town Administration government communication affairs office

  • Home
  • Mizan
  • Bachuma town Administration government communication affairs office

Bachuma town Administration government communication affairs office Bachuma city is found in western part of Ethiopia in west omo zone

በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የእርሻ ስራ  ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ላይ ያለመ የንቅናቄ መድረክ በባቹማ ከተማ እየተካሄደ ነው   ሚያዝያ 14   ባቹማበምዕራብ ኦሞ ዞን በባቹማ...
22/04/2024

በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ላይ ያለመ የንቅናቄ መድረክ በባቹማ ከተማ እየተካሄደ ነው

ሚያዝያ 14
ባቹማ

በምዕራብ ኦሞ ዞን በባቹማ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ዩኒት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ዙሪያ አስመልክቶ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በንቅናቄው መድረክ የባቹማ ከተማ አስተዳደር የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ከድር ኮምትኬስ በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እንደገለፁት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የእርሻ ግብር ስራ ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ላይ በመወያየት በቂ ግንዛቤ በመያዝ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ የስራ ገቢ ግብር በጋራ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት የንቅናቄው መድረክ ዋና አላማ እንደሆነ ገልፀዋል ።

የባቹማ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ አቶ ብርሀኑ ቡጳይ በመድረክ መክፈቻ ንግግራቸው እንደተናገሩት በከተማችን የሚገኙ የገቢ አማራጮችን ለመጠቀም ተሻሻሎ የቀረበው የግብር አዋጅ አስፈላጊ በመሆኑ የአካባቢያችንን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ በቀጣይ ተፈፃሚ ለማድረግ ከባለድርሻ በአሰራር ስርዓት ተፈፃሚ እንደሚሆን
ገልፀዋል ።

በመድረኩም የከተማው ገቢዎች ዩኒት አስተባባሪ አቶ አራጋው አሊ የ2016 ዓም የ9 ወራት አፈፃፀምና የስራ ግብር አዲሱ የግብር መክፈያ አዋጅን በሰነድ እያቀረቡ ይገኛል ።

በንቅናቄው መድረክ የባቹማ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራሮች የሚመለከታቸው የሴክተር ባለድርሻ አካላት የ5ቱም ቀበሌ ሊቀመንበሮች ፣ ስራ አስኪያጆች ፣ የቀበሌ መሬት አስተዳደሮች ፣ የቀበሌ የግብርና ባለሙያዎች ሌሎች የቀበሌ የፊት አመራሮች ጨምሮ በንቅናቄው መድረክ እየተሳተፉ ይገኛል ።

በ41 ዓመቱ ፈጣኑን የማራቶን ሠዓት ያስመዘገበው አትሌት - ቀነኒሳ በቀለአትሌት ቀነኒሳ በቀለ በለንደን በተካሄደው የማራቶን ውድድር ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ከ2019 ወዲህ ፈጣ...
21/04/2024

በ41 ዓመቱ ፈጣኑን የማራቶን ሠዓት ያስመዘገበው አትሌት - ቀነኒሳ በቀለ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በለንደን በተካሄደው የማራቶን ውድድር ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ከ2019 ወዲህ ፈጣኑን ሠዓት በማስመዝገቡ አድናቆት ተችሮታል፡፡

አትሌት ቀነኒሳ የዛሬውን የለንደን ማራቶን ውድድር 2 ሠዓት ከ4 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቅቋል፡፡

የዓለም አትሌቲክስም አትሌቱ የገባበት ይህ ሠዓት ከ2019 ወዲህ ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ዘንድ ሲመዘገብ የመጀመሪያው መሆኑን በመግለጽ አድናቆቱን ገልጿል፡፡

አትሌቱ ባለፈው የፈረንጆቹ ታኅሣስ ወር ላይ በቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር 2 ሠዓት ከ4 ደቂቃ ከ19 ሠከንድ መግባቱ የሚታወስ ሲሆን በለንደን ማራቶን ደግሞ ይህን ሠዓት በአራት ሰከንድ ዝቅ በማድረግ አሻሽሎታል፡፡

በመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር እና የግብርና ምርቶች ስራ ገቢ ግብር አዋጅ  ደንብ ላይ አጠቃላይ በየደረጃው ከሚገኙ ባለ ድርሻ አካላት በተገ...
20/04/2024

በመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር እና የግብርና ምርቶች ስራ ገቢ ግብር አዋጅ ደንብ ላይ አጠቃላይ በየደረጃው ከሚገኙ ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት በወረዳው ማዕከል የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ሚያዝያ 12 ቀን 2016ዓም የመኤኒት ጎልድያ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ባቹማ

በምዕራብ ኦሞ ዞን በመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የግብርና ምርቶች ስራ ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ዙሪያ የወረዳው አጠቃላይ የቀበሌ ሊቀመንበሮች ፣ ስራ አስኪያጆች ሌሎች የቀበሌ የፊት አመራሮችና የቀበሌ የግብርና ባለሙያዎች የወረዳ አመራሮች የገቢ ጽ/ቤት ማኔጀመንት አካላት ጨምሮ በተገኙበት የንቅናቄው መድረክ እየተካሄደ ነው።

የመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ የገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደሰ ጌናይ በእንኳን ደህና መጣችሁ መድረክ እንደገለፁት በተሻሻለው የገጠር መሬት መጠቀሚያ እና የግብርና ምርቶች ስራ ገቢ ግብር አዋጅ እና ደንብ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቂ ግንዛቤ በመፍጠር በቀጣይ የግብር አሰባሰብ ስራን አተኩሮ ለመስራት ያለመ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል ።

የመኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዶማ በመድረክ መክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያ አዋጅ እና ደንቡን ለመተግበር የአካባቢውን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የስራ ገቢ ግብር አዋጅ በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የጠራ ግንዛቤ በመፍጠር ስራውንም ተግባራዊ ለማድረግ የንቅናቄው መድረክ ዋና አላማ እንደሆነ ገልጸዋል ።

አክለውም ባለድርሻ አካላት በአካባቢያችን ያሉንን ሀብቶችን አሟጦ በመጠቀም ግዴታ የሆነውን የመንግስት ግብር ተፈፃሚ ለማድረግ በቅንጅት በመስራት የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያና የግብርና ስራ ገቢ ግብር ላይ ከመቸውም ግዜ በተለይ መልኩ ሊሰራ እንደሚገባ
ተናግረዋል ።

የ2016 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ90 ቀናት ዕቅድ ዙሪያ የተዘጋጀ መድረክ የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ንኡስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እያካሄደ ይገኛል ። 11/08/...
19/04/2024

የ2016 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ90 ቀናት ዕቅድ ዙሪያ የተዘጋጀ መድረክ የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ንኡስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እያካሄደ ይገኛል ።

11/08/2016 ዓ/ም
የባቹማ ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ንኡስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ90 ቀናት ዕቅድና ፣የመሠረታዊ ድርጀትና የአባላት ኮንፈረንስ የተዘጋጀ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ።

የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ንኡስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃለፊ አቶ በላይ ወርቅነህ የ3ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ90 ቀናት ዕቅድ ዙሪያ የተዘጋጀ የመሠረታዊ ድርጀትና የአባላት ኮንፈረንስ ሪፖርት አቅርቦ ውይይት እየተደረገ ነው ።

ከፖርቲው አባላት ጋር በጋራ በመሆን በተሰሩ ስራዎች ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች በመለየት ውይይት አድርገዋል ።

የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ቡጳይ በመድረኩ እንደተናገሩት የአመራሩንና የህዝብ ግንኙነት በማጠናከር የከተማይቱን ዕድገትን በማሳደግ ወደ ብልጽግና መሸጋገር እንዳለብን አንስተዋል ።

ከንቲባው አክለውም የሰራ አጥ ወጣቶች ስራ በመፍጠር ረገድ ትኩረት በመሰጠት በቀጣዩ ምቹ ሁኔታዎች በመፍጠር መስራት ይጠበቃል ብልዋል ።

በስተመጨረሻም ከተተከሉት የአረንጓዴ አሻራ ችግኞች መንከባከብ እንዳለበት ከንቲባው ገልጿል ።

ከዛሬ ጀምሮ ሚዲያውን የሚሰጠው መረጃዎች ህጋዊ መሆኑን እንገልፃለን ።
19/04/2024

ከዛሬ ጀምሮ ሚዲያውን የሚሰጠው መረጃዎች ህጋዊ መሆኑን እንገልፃለን ።

የባቹማ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ከ50 በላይ የሚሆኑ አቅመ  ደካሞችን ፣ አረጋውያን እና አካለ ጉዳተኞች  ጋር  የምገባ  ፕሮግራም  አድርጓል ።ታህሳስ  29/2016...
08/01/2024

የባቹማ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ከ50 በላይ የሚሆኑ አቅመ ደካሞችን ፣ አረጋውያን እና አካለ ጉዳተኞች ጋር የምገባ ፕሮግራም አድርጓል ።

ታህሳስ 29/2016 ዓ/ም
የባቹማ ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ከ50 በላይ የሚሆኑ አቅመ ደካሞች ፣አረጋውያን እና አካለ ጎዶሎዎች የጋራ ማዕድ አድርጓል ።

በፕሮግራሙ ላይ የባቹማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ በለጠ ግርማ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኃላ የተቸገሩትን መርዳት ባህላችን በማድረግ እና በበዓል ወቅቶች ከጎናቸው በመሆን የሚያስፈልጋቸውን አቅማችን በሚፈቅደው ልክ እገዛ በማድረግ የደስታቸው ተካፋይ መሆን መቻል አለብን ብለዋል ።

ከንቲባው አክለውም ለዚህ ፕሮግራም ስኬት አስተዋፅኦ ያደረጉ አካላት እንዲሁም የሲቪል ሰርቫንት በፍላጐታቸው ገንዘብ በማዋጣት ለዚህ በጎ ተግባር ውጤት ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

52 የሚሆኑ አቅመ ደካሞች ፣አረጋውያን እና አካለ ጉዳተኞች የማዕድ መጋራት ፕሮግራም ሲካሄድ የባቹማ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ሚድያ ተመልክቷል ።

በፕሮግራሙ ከፍተኛ አመራሮች ፣ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።

በስተመጨረሻም ከዚህ ቀደም ቤት ተሰርቶላት የነበረውን ምስኪን እናት አስቤዛ ድጋፍ ተደርጓል ።

06/01/2024

የምዕራብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸዉ ኬኒ የገናን በዓል አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉዋል።

ጀሙ፤ታህሳስ 27 ቀን 2016 ዓ.ም የምዕራብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸዉ ኬኒ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በየአመቱ የሚከበረውን የገናን በዓል አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው ላይ አክለዉ አንደገለፁት በዓሉን ስናከብር የተቸገሩት በመርዳትና ያለው ለሌለው በማካፈል በደስታ፣ በፍቅርና በአብሮነት ማሳለፍ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በዓሉን ስናከብር አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከርና በማጎልበት ሊሆን ይገባል።

የጀመርነው ጎልቶ የመውጣት ጉዞ ይበልጥ እንዲሰምር ኅብረታችንን አጠናክረን አንድ መሆንም ይኖርብናል።

በፈተናዎቻችን ትምህርት፣ በችግሮቻችን ጥንካሬ፣ በእንቅፋቶቻችን ብርታት እያገኘን፣ ከእያንዳንዱ ጨለማ ወዲያ ንጋት መኖሩን እያመንን፣ ዐይናችንን ወደ ወጋጋኑ አቅንተን በተራመድን ቁጥር ችግሮቻችን ወደኋላ ይሸሻሉ፤ እኛ ይበልጥ በበረታን ቁጥር የሚንመኘውን ብልጽግናን እናረጋግጣለን፡፡

ሁላችንም በቁጭት ከሰራን እና አንድነታችንን ካጠናከርን ሩቅ የመሰለን ህልም በእጃችን መዳፍ ስር እንደሚሆን መጠራጠር የለብንም፡፡

በዚህ ወሳኝ ወቅት ሁላችንም ዐቅማችን የፈቀደውን መሥራት ከቻልን፣ ያለ ጥርጥር ነገ ብሩህ ይሆናል፤ የመከራ ዘመንም እስከ ወዲያኛው ይሸኛል። ኢትዮጵያም የማትደፈር፣ የማትታፈር ሀገር ሆና በዐለት ላይ ትቆማለች።

ለሁሉም ነገር መሠረት የሆነውን ሠላማችንን እንደዓይን ብሌናችን መጠበቅ ከሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የሚጠበቅ ስለሆን ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አከባቢያችን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡

አክለውም በግጭት ፈንታ ሰላም የሚነግስበት፤ ፍቅር ጥላቻን የሚያሸንፍበት በህዝቦች ዘንድ መቻቻልና መከባበር የሰፈነበት አንድነትን በማጠናክር የአገራችን ህዝቦች ህልሞቻችን የሚያሳኩበትና የብልፅግና ጉዞዓቸው እውን የሚያደርጉበት ብሩህ ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በመጨረሻም በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር ፣ የደስታና የብልጽግና እንዲሆን ለመላው የክርስትና እምነቱ ተከታዮችና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተመኝተዋል።

በባቹማ ከተማ የገና በዓል ግብይት የተወሰነ ዋጋ ጨምረዋል ።-------------------------------//--------------------------ባቹማ ፦27/04/2016የቁም እንስሳ...
06/01/2024

በባቹማ ከተማ የገና በዓል ግብይት የተወሰነ ዋጋ ጨምረዋል ።

-------------------------------//--------------------------
ባቹማ ፦27/04/2016

የቁም እንስሳቶች ከባለፈው ግብይት የተጋነነ የዋጋ ንረት እንደሌለ ያነጋገርናቸው የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ነዋሪዎች ገለፁ ።

በገበያው ያነጋገርናቸው ሰዎች መካከል አቶ ግርማ ጎንጥዬ፣አቶ ጌታቸው ባልቲዬች ፣ አቶ ዬሰፍ ኮሌሺ እና አቶ ኤልያስ ጌባ እንደተናገሩት የከብቶች ዋጋ 15ሺህ እስከ 40 ሺህ አየተሸጡ ሲሆን በጎችና ፈየሎች ደግሞ ከ2ሺህ 500 እስከ 13ሺህ እየተገባዩ ሲሆን ከአለፉት ግብይት ትንሽ የተወሰነ ዋጋ ጨምረዋል ።

የቁም እንሳሳት የአቅርቦት ችግር እንዳለ አንስተዋል ።

ግብይቱ የከተማ አሰተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ቃኝተዋል ።

እንኳን ለጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ /አደረሰን፦የባቹማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ  አቶ በለጠ ግርማ --------------------------...
06/01/2024

እንኳን ለጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ /አደረሰን፦የባቹማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ግርማ
-------------------------------//--------------------------
ባቹማ ፦27/04/2016

በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ግርማ የገና በዓልን በማሰመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል ።

የባቹማ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ በለጠ ግርማ እንደገለፁት የገና በዓል እንደ ዓለም ህዝበ ክርስታያን የሚያከብር ትልቅ ትርጉም ያለው በዓል ነው።

በዓሉን በማስመልከት ከልክ ያለፋ መጠጥ ለጥላቻ ይዳርጋል ፣ከዚህ አልፎም ወጣቶች ሰክሮ ማሽከርከር ለአደጋ ስለሚያጋልጥ ከነዚህ ተግባራት እንዲቆጠቡ፣ቅባት የበዛ ምግቦች ለጤና እክል በመሆኑ በተመጣጣኝ መመገብ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ መክረዋል ።

ከበኣል ጋር ተያይዞ ልፈጠር የምችለው የፀጥታ ችግሮች ከፀጥታ ሀይሎች ጋር ጎን በመሆን ሁሉም የህብረተሰቡ ክፍል አካባቢያቸውን ሰላም ከማስጠበቅ ረገድ የድርሻቸውን ልወጡ ይገባልም ብልዋል

ከዚህ በተጨማሪ በአካባቢው ችግር ሲፈጠር ለጸጥታ ሀይሎች ጥቆማ በመሰጠት ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል ።

ይህ በዓል ህዝበ ክርስቲያን በአንድነት ሆኖ በፍቅር የሚያሳልፉት በመሆኑ የተቸገሩትም አንድ ሆነን በማክበር ፣ አቅመ ደካሞች በመርዳት በጋራ እንዲያሳልፉ ጠይቀዋል ።

በድጋሜ መላው ህዝበ ክርስትያን እንኳን ለጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ልደት በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን ብልዋል ።

04/01/2024

Aawa gɛdɛshike maante unɔɔy!!!

Address

Bachuma
Mizan
BACHUMA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bachuma town Administration government communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bachuma town Administration government communication affairs office:

Share