10/03/2026
በገቢ ተቋሙ እና በየደረጃው ባለ አመራር ተከታታይ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለፀ
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የበጀት ዓመቱ ዕቅድ 5,382,020,929 ብር ሲሆን እስከ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድረስ የተሰበሰበ ገቢ መደበኛ 2,951,715,066 ብር አፈፃፀም 61.45% የከተማ አገልግሎት 280.004,389 ብር አፈፃፀም 48.39% በድምሩ 3,231,719,456 ብር አፈፃፀም 60.05% ሲሆን ከ2017 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በብልጫ በ1,019,445,751 ብር ወይም 46.1% እድገት አሳይቷል ሲሉ ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ መምሪያ ሀላፊዋ ገልፀዋል አያይዘውም ለውጤቱ መምጣት በአመቱ መጀመሪያ ተገቢ የሆነ የእቅድ መግባባት በመፍጠር በትልቅ መድረክ የታክስ ንቅናቄ በማድረግ እና በተሰጠው ዕቅድ ላይ ከሁሉም ወረዳና ከተማ ጋር መግባባት በመፈጠር፤ ለሁሉም ወረዳና ከተማ የቀን የገቢ ዕቅድ ቆጥሮ መሰጠት፤ የመምሪያው የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ወረዳና ከተማን በቀጠና በመከፋፈል በአካል እና በየቀኑ በስልክ መደገፍና መከታተል በመቻሉ፤ እንዲሁም በየቀኑ ለስራ የሚያነሣሣ ግብረ-መልስ በመስጠትና የተሻለ ለፈፀሙ ወረዳና ከተማ እውቅናና ማበረታቻ በመስጠት ፉክክር ውስጥ ማስገባት በመቻሉ፣ በሁሉም ወረዳና ከተማ ከፖለቲካ አመራሩ ጋር የጋራ በማድረግ ጥረት የሚጠይቁ ገቢዎችን በመለየት ግብር ከፋዮን የመቀስቀስ ስራ በየጊዜው በመሠራት፤ በየሣምንቱ ወረዳና ከተማን በዙም በመደገፍ የተደረሰበትንና የገጠሙ ችግሮችን ለይቶ መፍታት በመቻላችን የተሸለ ውጤት አስመዝግበናል፡፡ እንዲሁም ከዞን አስተባባሪዎች ጀምሮ የገቢ ስራን ከፀጥታ ስራው ቀጥሎ በመያዝ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች በየደረጃው ያሉ አመራሮች ገቢ በመሰብሰብ ልማታችንን የማስቀጠል ጉዳይ ወሳኝነት በመረዳት በትኩረት ተቋሙን እየደገፉና እያገዙ ሲሆን በዋናነት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወረዳና ከተማን በዙም ሚቲንግ ጭምር በመገምገም በትኩረት እየደግፉ ስራውን እንዲያግዙ በማድረጋቸው ለመጣው ውጤት ባለድረሻ ናቸው፡፡ አጋር አካላትም የገቢ መሰብሰብ ስራውን በሁሉም ዘርፍ በመደገፍና በማገዝ ላይ ናቸው፡፡ የንግዱ ማህበረሰብም ቢሆን በአዳዲስ አሰራሮች ላይም በሚጠሩ ውይይትና መድረኮች በመገኘት ሃሣብ የመስጠትና ግብር የምከፍለው ለራሴ እና ለሃገሬ ልማት ነው የሚለው አስተሳሰቡ በመሻሻሉ የገቢ አሰባሰቡ የተሸለ እንዲሁን አግዟል ብለዋል መምሪያ ሀላፊዋ በቀጣይም ትኩረት የሚደረግባቸውን ነጥቦች ሲያነሱ በሁሉም የገቢ አርእስት ያልተሰበሰበ ገቢን በትኩረት በለየነው መሠረት ወረዳና ከተማ ገቢውን እና ውዝፍን ቆጥሮ መሰብሰብ እንዲሁም የንግድ ትርፍ፤ የኪራይ ገቢ፤ የደረጃ “ለ” እና “ሀ” በዝርዝር ለይቶ በትኩረት መሰብሰብ በዚሁ ጎን ለጎን ሁሉም የገቢ ተቋሙ አመራሮችና ሙያተኞች ስራውን በየቀኑ እየገመገሙ መምራት፣ ጥቅል የፖለቲካ አመራሩና ባለድርሻ አካላት ገቢ መሰብሰብ የህልውና ጉዳይ ነው በማለት ተቋሙን ማገዝ፣ የከተማ አገልግሎት ገቢ በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ መሠረት በትኩረት መስራት ይገባል ሲሉ ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ አሳስበዋል፡፡
የግብር ትምህርትና ኮሙንኬሽን ዋና የስራ ሂደት 01/07/2018 ዓ.ም