21/08/2026
ይህች ልጅ የምታለቅስበትን ምክንያት ስትናገር እንዲህ ትላለች
"ስሜ ሰላም ይባላል፤ የምኖረው ጎንደር ውስጥ ነው። ልጅነቴ በአባቴ አጠገብ ሙሉ፤ በደስታና በብዙ ትልቅ ህልሞች የተሞላ ነበር..."
"አባቴ ትልቅ መደገፊያዬ ነበር፤ እኔን ለማስተማር፤ ትልቅ ደረጃ ደርሼ እንድኮራበት የማይፈነቅለው ድንጋይ አልነበረም።"
"ነገር ግን ያ ሁሉ ደስታ በአንድ ጀምበር ፈረሰ... አባቴ በሞት ተለየኝ። እሱን ያጣሁበት ቀን የህይወቴ ብርሃን ሙሉ በሙሉ ጨለመ።"
"ከእሱ ህልፈት በኋላ የህይወት ፈተና እርስ በእርሱ እየተደራረበ መጣብኝ፤ የሚያስተምረኝና ደግፎ የሚያቆመኝ ሰው አጣሁ።"
"የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ የአባቴን አደራ ላለመጣል፤ ያንን ሁሉ ችግር ተሸክሜ ላለመውደቅ ሌት ተቀን ታገልኩ" ትላለች
አባት ሲኖር መጠጊያ፣ ዋስትና እና የቤቱ ጠንካራ ምሰሶ ነው፤ እሱ ሲያልፍ ግን የመጠጊያው ጥላ አብሮ ይሸሻል
ሰላምን በቅርብ የሚታውቋት አፅናኗት አበረታቷት ደጋግ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሁኔታውን አመቻቹ ❤️