Wajjira Hojjii fi Lenjii Aanaa Dawwa caffaa

Wajjira Hojjii fi Lenjii Aanaa Dawwa caffaa የድዋ ጨፍ ወርዳ ስራ እና ክህሎት ጽ/ቤት

Ummanni Musliimaa Marti Baga ji'a  Ramadaanaa bara 2018tiin isin ga'e!ለማላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ እንኳንለ2018 ለረመዳን ወር በሰላም አደ...
17/02/2026

Ummanni Musliimaa Marti Baga ji'a Ramadaanaa bara 2018tiin isin ga'e!

ለማላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ እንኳንለ2018 ለረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ!

!

የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና  ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ - የመንግስት ቀዳሚው አጀንዳ! ክፍል አራት አዋጁ ምን ይላል? 👉በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተና...
14/02/2026

የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ - የመንግስት ቀዳሚው አጀንዳ!

ክፍል አራት

አዋጁ ምን ይላል?

👉በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ቀዳሚው አጀንዳ ነው፡፡ በዚህም አዲሱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 ላይ ከተካተቱትና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች አንዱ የቀጥታ ቅጥር አሰራር ነው። ይህ ድንጋጌ መንግስት የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ታሳቢ አድርጎ የቀረፀው የዜጎች የጥበቃ ማዕቀፍ ነው፡፡

🚫 ክልከላ የተደረገበት ጉዳይ

👉ማንኛውም አሠሪ በመንግሥት ወይም በሕጋዊ የሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ በኩል ካልሆነ በስተቀር፣ በቀጥታ ሠራተኛን መልምሎ መቅጠር አይችልም።

ይህ ክልከላ ምን ፋይዳ አለው?

👉ሕገ-ወጥ ዝውውርን መግታት
• አዋጁ በ"ቀጥታ ቅጥር" ስም ዜጎችን ለሚያታልሉና ለሚመዘብሩ አካላት እድል አይሰጥም፤

👉 የመንግሥት ጥበቃን ለማረጋገጥ
• ዜጎች የት ሀገር፣ ከማን ጋር እና በምን ሁኔታ እንደሚሠሩ መንግሥት አስቀድሞ አውቆ አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግ ያስችላል፤

📍ቀጥታ ቅጥር የሚፈቀድባቸው ልዩ ሁኔታዎች

1️⃣የአሠሪው ማንነት ሲታወቅ

• አሠሪው የኢትዮጵያ ሚሲዮን (ኤምባሲ) አባል ወይም የታወቀ ዓለም አቀፍ ድርጅት ከሆነ፤

2️⃣በግል ጥረት ለሚገኝ የሥራ ዕድል

• ባህረኞችን ጨምሮ ማንኛውም የሰለጠነ ወይም በከፊል የሰለጠነ ዜጋ በራሱ ጥረት የሥራ ዕድል ካገኘ፤

3️⃣የደህንነት ዋስትና ሲኖር

• በሚሄዱበት ሀገር መብታቸውና ክብራቸው እንደሚጠበቅ በሚሲዮኖች ወይም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል የአሠሪው ሕጋዊነት ሲረጋገጥ፤

5️⃣ የኢንሹራንስ ሽፋን

• በአዋጁ መሠረት ተገቢው የሕይወትና የአካል ጉዳት ካሣ ኢንሹራንስ ሽፋን መኖሩ ሲረጋገጥ፤

5️⃣ምቹ የመጓጓዣ አገልግሎት

• ከሥራ ውሉ ጋር አስተማማኝ የመጓጓዣ አገልግሎት ስለመኖሩ ማስረጃ ሲቀርብ፤

⚠️ ትኩረት የሚሻው ጉዳይ!

• ከግል ጥረት ከሚገኝ ሥራ ውጪ፣ በመንግሥት በኩል የሚደረግ ቀጥታ ቅጥር ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ ሊወጣ የሚችለው በሚኒስቴሩ ወይም አግባብ ባለው ባለሥልጣን በኩል ብቻ መሆኑን በመገንዘብ፤ ህብረተሰቡ ከአጭበርባሪዎች ራሱንና ቤተሰቡን እንዲጠብቅ እናሳስባለን፡፡

የካቲት 7/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

 ! የኦሮሞ ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ከማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ጋር በጋራ መገምገም ጀምሯል።በከሚሴ ከተማ "ፀደይ ባንክ አዳራሽ" እየ...
14/02/2026

!

የኦሮሞ ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ከማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ጋር በጋራ መገምገም ጀምሯል።
በከሚሴ ከተማ "ፀደይ ባንክ አዳራሽ" እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ መድረክ ላይ፦
የመንግስትና የግል ኮሌጆች፣
የየደረጃው ስራና ክህሎት ጽሕፈት ቤቶች፣
የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጣቢያዎች እና
ዋሊያ ካፒታል በጋራ ተገኝተዋል።
የመምሪያው ኃላፊ ወ/ሮ ዘምዘም መሀመድ የግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፣ ባለፉት ወራት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና ድክመቶችን በማረም በቀሪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ የጋራ ግምገማ በዘርፉ ያለውን የተቀናጀ አሠራር ከማጠናከሩ ባለፈ፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና ለከተማዋ የኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#በመጨረሻም በ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ከዞን #የደ/ጨ/ወ/ስራና ክህሎት ጽ/ቤት #1ኛ ወጥተናል ።

እንኳን ደስ አለን!
#ኦሮሞ ዞን #ስራናክህሎት #ማዕድንሀብት #የ6ወራትአፈጻጸም #ልማት #ኢትዮጵያ

📅 የካቲት 05/06/2018 በደዋ ጨፋ የሥራና ክህሎት ጽህፈት ቤት የ6 ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማና የድጋፍ መድረክ በዞን ስራ እና ክህሎት መምሪያ የድጋፈ ቡድን በተገኙቀት ተካሄደ።ተቋማ...
12/02/2026

📅 የካቲት 05/06/2018 በደዋ ጨፋ የሥራና ክህሎት ጽህፈት ቤት የ6 ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማና የድጋፍ መድረክ በዞን ስራ እና ክህሎት መምሪያ የድጋፈ ቡድን በተገኙቀት ተካሄደ።
ተቋማዊ ስኬት የሚለካው በዕቅድ ብቻ ሳይሆን፣ አፈፃፀምን በየጊዜው በመፈተሽና ክፍተቶችን በመሙላት ነው። ዛሬ ከተገመገሙ ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡-
✅ የ6 ወራት የሥራ ዳሰሳ፡ የታቀዱ ተግባራት የደረሱበት ደረጃ በዝርዝር ተገምግሟል።
✅ ክፍተቶችን መለየት፡ በድክመት የታዩ ነጥቦች ተለይተው፣ ተጨባጭ የማስተካከያ እርምጃዎች ተቀምጠዋል።
✅ የመፍትሔ ውይይት፡ የጽህፈት ቤቱ የቡድን መሪዎች በተገኙበት በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ስምምነት ተደርሷል።

#ደዋጨፋ #ሥራናክህሎት ጽ/ቤት።

Har'a 27/05/2018 Wajjira hojjiifi Ogummaa Aanaa Dawaa Caffaatti  ogeessoota waligalaa wajjiraa waliin qorannoo hojjilee ...
04/02/2026

Har'a 27/05/2018 Wajjira hojjiifi Ogummaa Aanaa Dawaa Caffaatti ogeessoota waligalaa wajjiraa waliin qorannoo hojjilee fi kallattii fulduraa irratti mariin godhamera.

18/01/2026

Amhara 2030 initiative launching program at Oromo zone

 -2030:   "የ20 30 የኢትዮጵያ ድጅታል ቴክኖሎጂን በመተግበር አለም አቀፍ የስራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ የሆነ ወጣትን መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ።"*****የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ስ...
18/01/2026

-2030:


"የ20 30 የኢትዮጵያ ድጅታል ቴክኖሎጂን በመተግበር አለም አቀፍ የስራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ የሆነ ወጣትን መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ።"
*****
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ስራና ክህሎት መምሪያ የድጅታል አማራ ኢንሼቲቭ የድጅታል ክህሎት ኢ- ለርኒንግ ትግበራ እቅድ ኦሬንቴሽን ላይ ለባለድርሻ አካላቶች ስልጠና ሰጥቷል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ጀማል አሊ እንደገለፁት ድጅታል ኢትዮጵያ የትውልድ ኢንሼቲቭ ሲሆን በተለይ ወጣቱን ቀጣይነት ላለው ልማት የበቃ ወጣትን በማፍራት አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ነው።
ወጣቶች አለማቀፋዊ እውቀቶችን እንዲያውቅ የሚያስችል ኢንሼቲቭ ሲሆን በዚህ ልክ ወጣቱ አውቆ መስራት ይገባል ብለዋል።

የወጣቶችን ክህሎትና የቴክኖሎጂ አቅም ሊፈፅም የሚችል ቴክኖሎጂ ሲሆን ቀጣይነት ላለው ልማት የነገ ሀገር ተረካቢ ወጣቱን ማዘጋጀት ይገባል ነው ያሉት።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ስራና ክህሎት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ዘምዘም መሀመድ እንደተናገሩት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ሲስተምን በማስፋት እውቀትን ሳንሰስት ማሳካት ይገባል ብለዋል ።
ድጅታል ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ የታገዘ ወጣትን በማፍራት ወደ አለም ገበያ ማምጣት እንደሚገባ ሀላፊዋ ገልፀዋል።

ስልጠናው ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ሲሆን የ2030 ኢትዮጵያ ድጅታል ቴክኖሎጂ በመተግበር አለም አቀፍ የስራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ መሆን ይገባል ብለዋል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ስራና ክህሎት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰይድ እንድሪስ የ2030 ኢትዮጵያ ድጅታል ቴክኖሎጂ ለወጣቶች አዲስ የስራ እድል ሊፈጥር የሚችል የድጅታል ቴክኖሎጂ ሲሆን የአለም የስራ ገበያ ውስጥ ለማስገባት አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ድጅታል ቴክኖሎጂ እንደሆነም ገልፀዋል።

13/01/2026

D/C brave boy

Well come 🙏በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደዋ ጨፋ ወረዳ ቱቼ ቀበሌ ተወላጅ  የሆነው የፈጠራ ባለቤቱ ሰይድ አህመድ መሀመድ በነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ የፈጠራ ውድ...
13/01/2026

Well come 🙏
በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደዋ ጨፋ ወረዳ ቱቼ ቀበሌ ተወላጅ የሆነው የፈጠራ ባለቤቱ ሰይድ አህመድ መሀመድ በነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ የፈጠራ ውድድር ላይ 5ኛ ደረጃን በመያዝ የ100,000 ብር ሽልማት እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለ ምንም መያዣ የ10 ሚሊየን ብር ብድር እድል ያገኘው በዛሬው እለት የደዋ ጨፋ ወረዳ ምክር ቤት በምክር ቤቱ አባል ፍት እውቅና የሰጠው ሲሆን፣ የደዋ ጨፋ ወረዳ አሰተዳደርም በቱቼ ንዑሰ መዘጋጃ ቤት ለማበረታቻ የ200 ካሬሜትር የመኖሪያ ቤት ቦታ በመለገሰ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

"እንኳን ደስ አለህ! ጀግናው ወጣት ሰይድ አህመድ መሀመድ!በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን (ደዋ ጨፋ ) የTuche kebele ልጅ የሆነው ሰይድ አህመድ መሀመድ በነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግ...
11/01/2026

"እንኳን ደስ አለህ! ጀግናው ወጣት ሰይድ አህመድ መሀመድ!

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን (ደዋ ጨፋ ) የTuche kebele ልጅ የሆነው ሰይድ አህመድ መሀመድ በነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ የፈጠራ ውድድር ላይ 5ኛ ደረጃን በመያዝ የ100,000 ብር ሽልማት እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለ ምንም መያዣ የ10 ሚሊየን ብር ብድር እድል አግኝቷል።

ሰይድ በሬዎችን ጡረታ ለማስወጣት የረዳውን የእጅ ሚኒ ትራክተር በመፍጠር የፈጠራ ችሎታውን አሳይቷል። ይህ ለሀገራችን የግብርና ልማት ትልቅ አስተዋፅኦ ነው።

ሰይድ አህመድ መሀመድ ለዚህ ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናችንን እናቀርባለን! ለወደፊት ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

#ኢትዮጵያ #ፈጠራ #ወጣት #ስኬት #ግብርና"

በሬን ጡረታ አስወጣለሁ - ሰይድ አሕመድ መሐመድ በዱአ የተገኘው ነኝ!  አባትና እናቴ አምስት ሴት ልጆች ብቻ ስለነበራቸው ÷ ወንድ ልጅ ማግኘት የዘወትር ጸሎታቸው ነበር፡፡ ጸሎታቸው ተሰምቶ...
09/01/2026

በሬን ጡረታ አስወጣለሁ - ሰይድ አሕመድ መሐመድ

በዱአ የተገኘው ነኝ!

አባትና እናቴ አምስት ሴት ልጆች ብቻ ስለነበራቸው ÷ ወንድ ልጅ ማግኘት የዘወትር ጸሎታቸው ነበር፡፡
ጸሎታቸው ተሰምቶ ወንድ ልጅ ተሰጣቸው፡፡
ወሎ ከሚሴ ቱቼ ቀበሌ ነው የተወለድኩት፡፡
የበሬና የገበሬ ውለታ አለብኝ፡፡

ዩኒፎርም ለራሴ ገዝቼ የተማርኩ ነኝ!

ቤተሰቦቼ የተማረ ይወዳሉ፡፡
እኛም የተማርን እንድንሆን ይፈልጋሉ፡፡
በትምኀርት ሕይወቴ ፊዚክስና ሒሳብ ላይ ጎበዝ ነኝ፡፡
በልጅነቴ ፓይለት መሆን እፈልግ ነበር፡፡

ሂሊኮብተር ነበረኝ!

በትምኀርቴ 1ኛ የምወጣ ተማሪ ነበርኩ፡፡
ከትምኀርት ጎን ለጎን ተጨማሪ የግብርና ሥራ እሠራለሁ፡፡
በነበረኝ ገንዘብ ከገበሬነት እና ከተማሪነት በተጨማሪ የንግድሥራዎች እሠራ ነበር፡፡
ፀጉር ቤት ÷ ዳቦ ቤት ጭምር ከፍቼ አውቃለሁ፡፡
በልጅነቴ ከግብርና እና ከተማሪነት በተጨማሪ የተለያዩ የፈጠራሥራዎችን እሰራ ነበር፡፡
የሠራዋት ሂሊኮፍተር ለሰከንዶች በሰማይ በራልኝ ታውቃለች፡፡
ከሂሊኮብተሯ በተጨማሪ ድሮን ሰርቼ አውቃለሁ፡፡
ስንቅ እናደርስባት ÷ የመድኃኒት መርጫ አገልግሎት እንሰጥባት ነበር፡፡

እርሻችን ከበሬ መላቀቅ አለበት

በበሬ እያመረትን የምንኖረው የማኀበረሰብ ሕይወት ፈቅ አላደረገንም፡፡
ሌሎቹን ፈጠራዎቼን ገታ አድርጌ ÷ ዓይናችን ሥር ያለውን ችግርመቅረፍ ግዴታዬ ነው አልኩ፡፡
የበሬ ዘመንን ÷ በትራክተር ዘመን መተካት ይገባል ብዬ በቀን እናበምሽት የምትሰራ ማረሻ ማሽን ሰራሁ፡፡
በበሬ አርሶ ላሳደገኝ ገበሬ ቀን ላወጣለት በእጅ የምትሰራት ራክተር ሰርቼ ሕይወቱን ላሻሽል ቆረጥኩ፡፡

የነጋድራስ ውድድርን አሸንፋለሁ!

በአገራችን ከገበሬ የቀረበን እውነት የለም፡፡
እኔም ሕልመኛ ገበሬ ነኝ፡፡
የኔ ሕልም የሂሊኮፍተር ፕሮጀክቴን ከመቀጠል በላይ ÷ የድሮን ሥራዬን ከመቋጨት ባልተናነሰ ÷ በልጅነት የሰራሁትን አውሮፕላን ከመጨረስ በላቀ ÷ ለአንድ ገበሬ አንድ ትራክተር ማዳረስ የዕለት ሥራና ጸሎቴ ነው፡፡
የገበሬውን ሕይወት ስቀይር የአገሬን እውነት መቀየር ይቻላልብዬ ስለማምን ፕሮጀክቴ የነጋድራስ የምዕራፍ 4 የፍፃሜውድድር አሸናፊ እንደምሆን አምናለሁ፡፡

ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር የምዕራፍ 4 የፍፃሜ ውድድር እሑድ ይካሄዳል።

Address

Kemise City
Kemise

Opening Hours

Monday 14:00 - 23:00
Tuesday 14:00 - 23:00
Wednesday 14:00 - 23:00
Thursday 14:00 - 23:00
Friday 14:00 - 23:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wajjira Hojjii fi Lenjii Aanaa Dawwa caffaa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share