30/05/2026
ዜና ችሎት
በኮሬ ዞን ኬሌ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት እጅ ከፍንጅ ተይዘው በከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሰው በቀረቡ 5 ተከሳሾች ላይ ውሳኔ መስጠቱን አስታወቀ።
ኬሌ ፦ግንቦት 22/2018ዓ.ም
በከሌ ከተማ አስተዳደር 01 ከተማ ቀበሌ ቀጠና 3 ልዩ ስም ኤፍትስ/ፋጫ ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ ተከሳሾች:-
1ኛ ምህረቱ መከሩ
2ኛ ማርቆስ ዮሐንስ
3ኛ ጌቱ አበበ
4ኛ ደስታ ደረሰ
5ኛ ቀቸለ ቦይለ የተባሉት በጋራ በመተባበር ጨለማን ተገን በማድረግ በቀን 21/9/2018 ዓ/ም ዕለተ ዓርብ ከለሊቱ 8:00 ሰዓት ገደማ ግል ተበዳይ ከሆነዉ ከአቶ ደሳለኝ ዱባሌ መኖርያ ቤት ዉስጥ ዘልቆ በመግባት ከከብቶቹ መሐል ትልቁን ኮርማ ዳላቻ በሬ ዋጋዉ 95 ሺህ ብር የሚያወጣውን ከታሰረበት ገመዱን በመፍታት ከባድ የስርቆት ወንጀል ፈፅመዉ ሲያመልጡ እጅ ከፍንጅ ተይዘው በቁጥጥር ስር ውለዋል በማለት ዓቃቤ ህግ በወንጀል ህግ አንቀጽ 32/1/ሀ/ እና 669 ንዑስ 3/ለ/መሠረት ክስ መስርቶባቸዉ አቅርቧል።
በዚህም መሠረት 1ኛ ተከሳሽ የሆነዉ እጅ ከፍንጅ ከበሬዉ ጋር እንደ ተያዘና ሌሎች ተከሳሾች ሮጠዉ ካመለጡበት ተይዘዉ እንደቀረቡ ዓቃቤ ህግ በክሱ አስረድቷል።
3ኛ ተከሳሽ አጠገብ ከምዕራብ ጉጅ ዞን ሰርቀዉ ካመጣቸዉ ከብቶች ስሸጡ ከቀሩት 2 ሴት ጥጃዎችን ኤግዚብት በማቅረብ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት በ35 መሠረት የእምነት ክህደት ቃላቸዉን በመቀበል ክስ መስርቶ ለፍርድ ቤት አቅርቧል።
ተከሳሾችም ፍርድ ቤት ቀርበዉ የክስ ቻርጅ እያንዳንቸዉን ደርሶ አንብበዉ ከተረዱ በኃላ ፍርድ ቤት የክሱን ተቃዉሞ ጠይቆ ክሱን አንቃወምም በማለት ሃሳባቸዉን ሰጥተዋል።
ፍርድ ቤቱም በግላቸው ወይም በጠበቃ እንደምከራከሩና ጠይቆ በራሳቸዉ እንደሚከራከሩ አስረድተዉ 1ኛ, 2ኛና 3ኛ ተከሳሾች ወንጀሉን ፈጽመናል ስሉ 4ኛና 5ኛ ተከሳሾች አልፈፀምንም በማለት ክደዉ ተከራክረዋሉ።
ዓቃቤ ህግ አጠቃላይ በተፈፀመዉ ወንጀል ላይ የሚያስረዱ ምስክሮች አሉኝ በማለት 5 የሰዎችን ማስረጃ በማቅረብ በእያንዳንዳቸው አስመስክሮ ተከሻሾችም የመስቀለኛ ጥያቄዎችን ዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ጠይቀዋል።
በዚህም መሠረት ፍርድም ቤቱ እያንዳቸውን ያስተምራል ሌሎችንም ያስተምራል ያላቸዉን
1ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ5 ወር
2ኛተከሳሽ 7 ዓመት ከ5 ወር
3ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ5 ወር
4ኛ ተከሳሽ 8 ዓመት
5ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ5 ወር በአጠቃላይ ተከሳሾችን በፅኑ እስራት ተቀተዋሉ።
በመጨረሻም ፖሊስና የፍትህ ተቋም በጋራ በሰጡት አስተያየት በዝህ መልክ በአካባቢያችን የሚከሰቱ ወንጀሎችን ለመከላከል ከፖሊስ ጎን በመቆም የተለመደዉን ድጋፍ እንድያደርግ ሀሳባቸዉን ሰጥተዋሉ።