02/06/2026
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
#ጅግጅጋ:- 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ በግንቦት 24 ቀን ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ድምጽ ሲሰጥ የዋለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል ብለዋል።
በድምጽ ምስጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ ከተማ በጣም ረጃጅም ሰልፎች እንደነበሩ አንስተው÷ በሲዳማ፣ ጋምቤላ፣ አማራ፣ ሶማሌ ክልሎች የድምጽ ቆጠራ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል።
በዚህም የመራጮች ቁጥር እስካሁን ተጠቃልሎ አለመግባቱን ተናገረዋል።
ቦርዱ የተለያዩ ቅሬታዎች በተለያየ መንገድ ሲያስተናግድ መቆየቱን አንስተው÷ በሕግ ክፍል በኩል በቀጥታ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ የስራ ክፍል አማካይኝነት በቅድመ ማስጠንቀቂያ 6214 ስልክ ቁጥርና በአጭር መልዕክት መቀብያ 7555 የመጡ ጥቆማና ቅረታዎች እንደነበሩ አመልክተዋል።
በዚህም ጥቆማውን በመከተል ከስር ከስር አስፈላጊውን የእርምት ርምጃ ቦርዱ ሲሰጥ መቆየቱን እንዲሁም የማጣራት፣ የማረጋገጥና ማስረጃ ማጠናቀር በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።