22/05/2026
በምዕራብ ጎጃም ዞን የጅጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት " በላቀ የወጣቶች ተሳትፎ ኢትዮጽያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ የአደባባይ ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ፣ የምርጫ ምልክት እና የእጩዎች የትውውቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ ።
በሰላማዊ ሰልፉ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጅጋ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ምስጋናው ድንቁ "ብልፅግና ለወጣቶች ተጠቃሚነት በልዩ ትኩረት ይሰራል" ብለዋል።
በፕሮግራሙ የምዕ/ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ መዝገቡ ውቤ እንዲሁም የጅጋ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።