08/09/2026
ጳጉሜ 3:-የጽናት ቀን!
በሀዲያ ዞን ''ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር '' በሚል መሪ ቃል የጽናት ቀን በድምቀት እየተከበረ ነው።
ሆሳዕና፣ጳጉሜ03/2018 ዓ.ም(ሌሞ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን)
ዛሬ ጳጉሜ 3 ነው::ቀኑ የጽናት ቀን ነው ። ቀኑም በዞኑ ''ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር!''በሚል መሪ ቃል በፖሊስ ትርዕትና በሌሎችም ዝግጅቶች በሆሳዕና ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።
የዕለቱ መርሃ ግብር የሀገራችን ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን በማውለብለብ እና በሰንደቀላማ ሥር ሀገራችንን በአንድነትና ሠላም በጽኑ ዓለት ላይ ለማቆም ቃለ ማሃለ በመፈፀም ተጀምሯል ።
በመቀጠልም ዕለቱን በማስመልከት ለሚካሄደው የውይይት መድረክ የመነሻ ሰነድ የሀዲያ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ በአቶ ደመቀ በዶሬ እየቀረበ ይገኛል።
በሥነ ሥርዓቱም የሀዲያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ_ጉባዔ ክብርት ወይዘሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣የሀዲያ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው፣የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዳኛ ጥላሁን ዴታሞን ጨምሮ የክልል የሆሳዕና ማዕከል አመራሮች፣የሀዲያ ዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣የሆሳዕና ከተማ አመራሮች፣የሀዲያ ዞን የፍትህ፣የሠላምና ፀጥታ አመራሮች፣የባህል ሽማግሌዎች፣የሀይማኖት አባቶች ፣ከሁሉም መምሪያ የተወጣጡ የማኔጅመንት አባላት፣የፖሊስ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ናቸው።
ሀዲያ ዞን ኮሚዩኒኬሽን