14/07/2023
👉 የንግድ ስራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሕገወጥ መንገድ እየነገዱ የተገኙት እና በወንጀል የተከሰሱት 1ኛ/ግርማቸው እያሱ መንግስቱ 2ኛ/ባያቸው እያሱ መንግስቱ ለእያንዳንዳቸው የሚታሰብ በ7 አመት ፅኑ እስራት እና በብር=3000 እንዲቀጡ ተወሰነ፦
➤ ተከሳሽዎች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ሕዳር 21 ቀን2015ዓ/ም በግምት ከለሊቱ 9:00 ሰአት ሲሆን 1ኛ/ተከሳሽ ሸፌር በመሆን የታርጋ ቀጥር ኮድ1 አ.ማ - 41748 በሆነ ባጃጅ 2ኛ/ተከሳሽን አሳፍሮ ከሽዋ ዳቦ ወደጊወርጊስ አደባባይ እያሽከረከረ በመምጣት ላይ እንዳለ በፀጥታ ኃይል ተይዘው ሲፈተሹ በሕገወጥ መንገድ የተጫነ 1ኛ/7 ጀሪካ ባለ 25 ሌትር ቤንዚል 2ኛ/5 ጀሪካ ባለ30 ሌትር ቤንዚል ጠቅላላ ዋጋው ብር=18,616 የሆነው ነዳጅ ተይዞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር 3ኛ ፓሊስ ጣቢያ በሰው እና በእግዚቪት ማሰረጃ አስደግፎ ምርመራ አጣርቶ ለማእከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ የኢኮኖሚ ነክ ወንጀል ጉዳዮች የስራ ሒደት በመላክ የዞን ዐቃቤ ሕግ የተላከለትን መዝገብ መርምሮ በተከሳሽዎች ላይ1ኛ/ክስ የንግድ ምዝገባ ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 አንቀፅ 22/1/እና49/2/እና የኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32/1/ሀ/ የተመለከተውን በመጥቀስ2ኛ/ ክስ ደግሞ የንግድ ዉድድር እና የሸማችዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/20.6 አንቀፅ 24/1/ሀ/ለ/አንቀፅ 43/4/5/የተመለከተውን በመጥቀስ ሁለት ክስ መስርቶ ለማእከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በማቅረብ ጉዳዩ በክርክር ቆይቶ ሰኔ 15 ቀን 2015ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽዎች በዐቃቤ ሕግ በኩል የቀረበባቸውን ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻላቸው ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ለያንዳንዳቸው የሚታሰብ በ7 አመት ፅኑ እስራት እና በብር=3,000 እንዲቀጡ ፍ/ቤቱ ወስኗል።በሕገወጥ መንገድ የተያዘው ነዳጅ ለመንግስት ውርስ ተደርጓል።
መረጃው
የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ የታ/ወ/ምርመራ ዋና ክፍል ነው