01/03/2023
እንኳን ለ127ኛው የአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
የአድዋ የድል በዓል ሲነሳ የአፍሪካውያን ብሎም የኢትዮጵያውን የይቻላል መንፈስ እንደብረት የጠነከረበትና ከነጮች ጥገኝነት መላቀቅ የሚያስችል ወኔን በተግባር የተላበስንበት አስተማሪ ታሪካችን ነው፡፡የአድዋ ድል መተባበርን፣ አንድነትንና ነጻነትን በአፍሪካውያን በተለይም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ እንደማህተም ቀርጾ ዘላለማዊ የአልሸነፍም ወኔን በተግባር ያጎናፀፈን የእምየ ምኒሊክ እና የእትጌ ጣይቱ የተጋድሎ ውጤት ነው፡፡
እድዋና አፄ ሚኒሊክ ለኢትዮጵያችን የዘመናዊ ስልጣኔ ፈር ቀዳጅ፣የአለምአቀፋዊ ግንኙነት መሰረት፣የአስተዋይነትና የብልህ አመራር ጥበብ የታየበት፣ሰብዓዊነት፣ርህራሄና በጎነት የመነጨበት ህያዊ ታሪካችን በመሆኑ እኛም የአያት ቅድመ-አያቶቻችን ታሪክ በተግባር ለመድገም ቀደምት ታሪካችን ማወቅ መመራመርና መተግበር ይጠበቅብናል፡፡አፄ ሚኒሊክን ስናስታውስ በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በአእምሯችን ይቀረፃሉ፤ከበርካታዎቹ መካከል ውሃ ኢትዮጵያ በቧንቧ ማግኘት የጀመረችበት ዘመን በእርሳቸው ዘመን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ክብርና ምስጋና ለስልጣኔ ፈር ቀዳጆችና ነፃነት ላጎናፀፉን አፄ ሚኒሊክ እና ለእትጌ ጠይቱ