የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

  • Home
  • Ethiopia
  • Gofa
  • የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office አስተማማኝ የልማት አቅም እንፈጥራለን !!!

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የ2018 የግብር አሰባሰብና የ2019 የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ዘመቻ አስመልክቶ የተካሄደ የማስፈጸሚያ መድረክ #ሣውላ፣ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም የሣዉላ ከተማ ገቢዎች ጽ ...
06/07/2026

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የ2018 የግብር አሰባሰብና የ2019 የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ዘመቻ አስመልክቶ የተካሄደ የማስፈጸሚያ መድረክ

#ሣውላ፣
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
የሣዉላ ከተማ ገቢዎች ጽ ቤት

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የ2018 የግብር ዓመት የግብር አሰባሰብና የ2019 የንግድ ሥራ ፈቃድ ዕድሳት ሥራዎችን በተቀናጀና ውጤታማ መንገድ ለማስፈጸም ያለመ የማስፈጸሚያ መድረክ በከተማው ተካሂዷል። በመድረኩ የከተማው አመራሮች፣ የገቢ፣ የንግድ፣ የፋይናንስ፣ የማዘጋጃ ቤት፣ የመሬት አስተዳደር፣ የህግ አስከባሪ አካላት፣ የቀበሌ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በስፋት ተሳትፈዋል።

ሰነዱን ያቀረቡት የሣውላ ከተማ ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ኩማ እንዳብራሩት፣ የ2018 የግብር ዓመት የግብር አሰባሰብና የ2019 የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ሥራ በቅድመ ዝግጅት፣ በቅንጅትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፎ መፈጸም የሚገባ ሀገራዊ ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የገቢ ጽ/ቤትና የንግድ ጽ/ቤት በጋራ የማስፈጸሚያ ዕቅድ በማዘጋጀት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርብ በመቀናጀት እንደሚሰሩ አስረድተዋል።

አቶ ጌታሁን ኩማ እንደገለጹት፣ በ2017 የግብር ዓመት የተመዘገቡ ጠንካራ አፈጻጸሞች ለ2018 ሥራ ጥሩ መነሻ ቢሆኑም የታዩ ጉድለቶችን በመለየት እንዳይደገሙ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይ የግብር ከፋዮች መረጃን ማጥራት፣ የሲስተም አጠቃቀምን ማስፋት፣ የቴሌብር ክፍያን ማሳደግ፣ የታክስ ከፋዮችን ሕግ ተገዥነት ማጠናከርና የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ማሳደግ የዘመቻው ዋና ትኩረቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም የግብር አስተዳደሩን ለማዘመን በSIGTAS ሲስተም፣ በኢ-ፋይሊንግ፣ በኢ-ፔይመንትና በቴሌብር የሚሰጠው አገልግሎት የግብር ክፍያን ቀላል፣ ፈጣንና ግልጽ እንደሚያደርገው ጠቅሰው፣ በቀጣይ ሁሉም የግብር ከፋዮች ዘመናዊ የክፍያ ሥርዓትን እንዲጠቀሙ የማስተዋወቅና የድጋፍ ሥራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል።

በተጨማሪም ሰነድ ያቀረቡት የሣውላ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ሰለሞን እንዳብራሩት፣ የ2019 የንግድ ሥራ ፈቃድ ዕድሳት ሥራ ከግብር አሰባሰብ ጋር በአንድ ማዕከል ተቀናጅቶ እንደሚከናወን ገልጸዋል። ይህም የአገልግሎት ፍጥነትን በማሻሻል የተገልጋዮችን እንግልት እንደሚቀንስና የንግድ ፈቃድ ዕድሳትን በጊዜው እንዲፈጽሙ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

አቶ ታደለ አክለውም ሕገ-ወጥ ንግድን መከላከል፣ ያልታደሱ ፈቃዶችን በጊዜው ማደስ፣ ከግብር ሥርዓቱ ውጭ ያሉ ነጋዴዎችን ወደ ሥርዓቱ ማስገባትና ከሌሎች ተቋማት ጋር የመረጃ ልውውጥን በማጠናከር ገቢን ማሳደግ የተቋሙ ቀዳሚ ተግባራት መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የሣውላ ከተማ ክብር ከንቲባ አቶ በላይነህ ባህሩ እንደገለጹት፣ የግብር አሰባሰብ የመንግሥት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ የከተማውን ልማት የሚያጠናክር መሠረታዊ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም ሁሉም አመራር፣ ባለሙያ፣ የቀበሌ አመራሮች፣ የህግ አስከባሪ አካላትና የህብረተሰቡ ክፍሎች በተጠናከረ ቅንጅት እንዲሰሩ አሳስበዋል።

ከንቲባው በተለይ የግብር ከፋዮች ግዴታቸውን በወቅቱ በመወጣት ለከተማው ልማት ያላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ሁሉም ተቋማት በአገልግሎት ጥራት፣ በፍትሃዊነትና በተጠያቂነት በመስራት የህዝቡን እምነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በተመሳሳይ የሣውላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ አቶ ከተማ ከበድ እንደገለጹት፣ የግብር አሰባሰብ የመንግሥት ሥራ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም የፓርቲ አደረጃጀቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች ክንፎች፣ የታክስ አምባሳደሮችና ሌሎች ማህበራዊ አደረጃጀቶች በቅስቀሳ፣ በግንዛቤ ፈጠራና በሕዝብ ንቅናቄ ሥራ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ከተማ ከበድ አክለውም፣ የሕግ ተገዥነትን በማጠናከር፣ የግብር አጭበርባሪነትን በመከላከልና ህብረተሰቡ ደረሰኝ የመጠየቅ ባህሉን እንዲያጠናክር በተቀናጀ መንገድ መስራት የሚያስፈልግ መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት የ2018 የግብር አሰባሰብና የ2019 የንግድ ፈቃቭ
ድ ዕድሳት ሥራዎችን በተቀናጀ አመራር፣ በውጤታማ ቅንጅትና በህዝብ ተሳትፎ በማከናወን የታቀደውን ግብ ለማሳካት በጋራ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
Facebook
የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office
Telegram
t.me/SawlaTownRevenueOffice

05/07/2026

የ2018 ግብር ዘመን የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ዓመታዊ የግብር መክፈያ ወቅትን አስመልክቶ ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ የተሰጠ መግለጫ

05/07/2026
የ2018 የግብር ዘመን ዓመታዊ ግብር አሰባሰብ ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በይፋ የሚጀመር መሆኑ ተገለፀየዓመታዊ ግብር አሰባሰብ ሂደቱን አስመልክቶ የደቡብ ኢት...
05/07/2026

የ2018 የግብር ዘመን ዓመታዊ ግብር አሰባሰብ ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በይፋ የሚጀመር መሆኑ ተገለፀ

የዓመታዊ ግብር አሰባሰብ ሂደቱን አስመልክቶ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዓለምነሽ ደመቀ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም እንዲሁም የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2019 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ዓመታዊ ግብራቸውን እንዲሚከፍሉ ተገልጿል።

በክልሉ 7 ሺህ 330 የደረጃ 'ሀ' እና 121 ሺህ 745 የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ያሉ ሲሆን ከሐምሌ 1/2018 እስከ ጥቅምት 30/2019 ከ13.834 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ወ/ሮ ዓለምነሽ ተናግረዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 65/2018 መሠረት የክልሉ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ የግብር ግዴታቸውን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚወጡ ይሆናሌ።

የታክስ ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥም በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ምክንያት በየ3 ዓመቱ የሚካሄደዉ ግመታ ባለመካሄዱ የማዕከላዊ ስታትስትክስ መረጃን በመጠቀም የዋጋ ግሽበት ማስተካከያ መደረጉን ተናግረዋል።

የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች መክፈያ ጊዜ ከሐምሌ 1/2018 የሚቆይ ቢሆንም በ10 ቀን ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ኃላፊዋ ገልጸዋል።

ግብር ከፋዮች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ዓመታዊ ግብራቸዉን በመክፈል ከቅጣት እና ወለድ ራሳቸዉን ነፃ እንዲያደርጉ ኃላፊዋ አሳስበዋል ።

ግብር ከፋዮቻችን የ2018 የግብር ዘመን ዓመታዊ ግብራቸውን ውድ የሥራ ጊዜያቸውን ሳያባክኑ ምቹና ተደራሽ በሆኑ አማራጮች፤ በቴሌብር፣ CBE birr እና በአካባቢ በሚገኙ ባንኮች በመሄድ በደራሽ የክፍያ አማራጮች ግብራቸውን እንዲከፍሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተገልጿል።

በዚህም በክልላችን ከሚገኙ 136 የታክስ ማዕከላት ውስጥ በ105ቱ የሲግታስ ቴክኖሎጂ ተደራሽ መደረጉን እንዲሁም 101 ተጨማሪ ማዕከላት የተዘጋጁ በመሆኑ ግብር ከፋች በተቀመጡት አማራጮች ግብራቸውን መክፈል እንደሚችሉ ተመላክቷል።

ግብር ከፋዮቻችን የተቀመጡትን አማራጮች በመጠቀም ዓመታዊ ግብራቸውን በሚከፍሉበት ጊዜ በተለይ ቴሌ ብር ሲጠቀሙ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ግብር ከፋዮቻችን በሁሉም የታክስ ማዕከላት የቴሌ ብር ኤጄንቶች ተገኝተው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
መረጃው
የ South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/
Gofa Zone Revenue Department ነዉ

የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ዓመታዊ የግብር መክፈያ ጊዜው ደረሰ። #የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም፣ #የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018...
05/07/2026

የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ዓመታዊ የግብር መክፈያ ጊዜው ደረሰ።

#የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም፣

#የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2019 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ዓመታዊ ግብራችሁን እንድትከፍሉ ስናስታውሶ በአክብሮት ነው፡፡

የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

04/07/2026
የ2018 ዓ.ም የገቢ አሰባሰብና የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ በሣውላ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።ሰኔ 27/2018 ዓ.ም የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና ንግድና ኢንዱስትሪ ል...
04/07/2026

የ2018 ዓ.ም የገቢ አሰባሰብና የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ በሣውላ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ሰኔ 27/2018 ዓ.ም

የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ በጋራ ያዘጋጁት የ2018 የግብር ዘመን የገቢ አሰባሰብና የንግድ ፈቃድ ዕድሳት ስራዎችን ለማፋጠን የታለመ ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በሣውላ ከተማ በይፋ ተጀምሯል።

መድረኩን የከፈቱት የጎፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምናሴ ኤልያስ፤ የመንግስት ጥንካሬ የሚለካው የአካባቢውን የገቢ አቅም በሙሉ በመጠቀም ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣንና ተገቢ ምላሽ መስጠት ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ምናሴ ገለፃ፣ በጎፋ ዞን የገቢ አሰባሰብ አቅም ከዓመት ወደ ዓመት እያደገ የመጣ ቢሆንም፣ የኤክስፖርት ሰብሎችን በስፋትና በጥራት በማምረት የገቢ ምንጮችን ማስፋት፣ ያሉ ውስንነቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አቶ ምናሴ አክለውም የገቢ አሰባሰብ ስራውን ከተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ቀድሞ በማጠናቀቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማፋጠን እና የህዝቡን ፍላጎት ለመመለስ እንደሚያስችል ገልጸው፣ ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በመቆጣጠር የገቢ አቅምን ማጠናከር እና የንግድ ፈቃድ ዕድሳትን በህጋዊ ስርዓት ማከናወን የሁሉም ተቋማት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ጉጃ፣ የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ውጤታማ ለማድረግ ከወረቀት ወደ ዲጂታል የሚቀየር ስርዓት በስፋት እየተዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ኃላፊው ገለፃ፣ በ2018 የግብር ዘመን ከዚህ ቀደም በሶስት ደረጃ የነበረው የግብር ከፋይ ምደባ ወደ ሁለት ደረጃዎች ብቻ ተቀይሯል። በዚህም 487 የደረጃ "ሀ" እና 10,563 የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች እንዳሉ በመጠቆም፣ ቀሪውን 25 በመቶ የገቢ አሰባሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ጠንካራ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

በመድረኩ የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቦረና ቦላዶ፣የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን ደምሴ የዞን አመራሮች፣የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣የገቢዎች እና የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ለበለጠ መረጃ
Gofa Zone Government Communication Affairs Department

የዕውቅና እና የሽልማት መርሃ-ግብር 🏆🎉​የፓርቲ ሥራዎችን በላቀ አፈጻጸም በመምራት የተመዘገበ ስኬት!​በሣዉላ ከተማ አስተዳደር የፓርቲ ሥራዎችን በላቀ ቁርጠኝነትና ስኬታማነት በማከናወን ረገ...
04/07/2026

የዕውቅና እና የሽልማት መርሃ-ግብር 🏆🎉
​የፓርቲ ሥራዎችን በላቀ አፈጻጸም በመምራት የተመዘገበ ስኬት!
​በሣዉላ ከተማ አስተዳደር የፓርቲ ሥራዎችን በላቀ ቁርጠኝነትና ስኬታማነት በማከናወን ረገድ የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ ለልማት ቤተሰብ አባላት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል። ይህንን ተከትሎም የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት የእነዚሁ የገቢ ለልማት ቤተሰብ አባላት ከብልጽግና ፓርቲ በክብር ከንቲባ አማካኝነት ታላቅ የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
​የጽህፈት ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች በጋራ በመሆን የዋንጫ እና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሽልማታቸውን ከክብር ከንቲባው እጅ በክብር ተቀብለዋል። ይህ ሽልማት ሰራተኞቹ ለከተማዋ ዕድገትና ለፓርቲው ስራዎች ስኬታማነት ያበረከቱትን የማይተካ ሚና የሚያሳይ ነው።
በፓርቲ ሥራዎች ግንባር ቀደም መሆን፦ የፓርቲውን እቅዶችና ግቦች በላቀ ደረጃ በመተግበር ረገድ የተሳለጠና ውጤታማ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉ፣
​የተቀናጀ የቡድን ስራ፦ የገቢ ለልማት ቤተሰብ አባላት ባሳዩት ከፍተኛ የውስጥ አንድነትና ቁርጠኝነት ለዚህ ክብር መብቃት መቻላቸው፣
​ለከተማዋ ልማት መፋጠን፦ የገቢዎች ጽ/ቤት በፓርቲውም ሆነ በመንግስት የተጣሉበትን ኃላፊነቶች በአግባቡ በመወጣት ለሣዉላ ከተማ ሁለንተናዊ ብልጽግና የበኩሉን አሻራ እያኖረ መሆኑ።
​ይህ የዕውቅና ሽልማት በቀጣይም ይበልጥ ጠንክሮ ለመስራትና የተጀመሩ የልማትና የፖለቲካ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማስቀጠል ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥር ነው።
​ለመላው የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ ለልማት ቤተሰብ አባላት እንኳን ደስ አላችሁ እያልን፣ በቀጣይም የስራ ዘመናችሁ የላቀ ስኬትና ድል የሚመዘገብበት እንዲሆን እንመኛለን!
​"በትጋትና በታማኝነት ወደ ላቀ ብልጽግና!"
Telegram
t.me/SawlaTownRevenueOffice
Facebook
የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

📢 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከተሰጡት ታላላቅ ኃላፊነቶች መካከል በየደረጃው ለሚገኙ አስፈጻሚ መዋቅሮችና ከተማ አስተዳደሮች የቅርብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ አንዱ ነው።​በዚሁ መሠረ...
03/07/2026

📢 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከተሰጡት ታላላቅ ኃላፊነቶች መካከል በየደረጃው ለሚገኙ አስፈጻሚ መዋቅሮችና ከተማ አስተዳደሮች የቅርብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ አንዱ ነው።
​በዚሁ መሠረት፣ ከቢሮው የተወከለ የድጋፍ ሰጪ ቡድን በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ በመገኘት ከከተማዋ የማኔጅመንት አባላት (አመራሮች) ጋር በጋራ መሥራት የሚያስችል ሰፊ ውይይት አካሂዷል።
​ቢሮው የክልሉን የገቢ አቅም ለማሳደግና ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን ለመዘርጋት በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

​📌 የውይይቱ ዋና ዋና ዓላማዎች፦
🔐​የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ፦ በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወነ ያለው የገቢ አሰባሰብ ሂደት ካለበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር መገምገም።
🔐​ክፍተቶችን መለየትና መደገፍ፦ በገቢ አሰባሰቡ ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ መዋቅራዊና የአቅም ክፍተቶችን በውይይት በመለየት፣ ቀጣይነት ባለው መልኩ ድጋፍ የሚደረግበትን አግባብ መቀየስ።
🔐​ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፦ በክልሉ ገቢዎች ቢሮ እና በየደረጃው በሚገኙ የማኔጅመንት አካላት መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር የህግ ተገዢነትን ማረጋገጥ።
​የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ድጋፍ ሰጪ ቡድን በሳውላ ከተማ ካሉ የማኔጅመንት አባላት ጋር ያደረገው ይህ ውይይት፣ በቀጣይ የከተማዋን የውስጥ ገቢ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመሰብሰብና ለልማት ስራዎች የሚውል በጀት ለማመንጨት ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። ቢሮው መሰል የሱፐርቪዥንና የድጋፍ ስራዎቹን በሁሉም አካባቢዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል።
​"ታማኝ ግብር ከፋይነት ለሀገርና ለወገን ኩራት ነው!"


የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 65/2018፤ የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን ከሐምሌ 1/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም፣የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ከሀምሌ...
02/07/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 65/2018፤
የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን ከሐምሌ 1/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም፣
የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ከሀምሌ 1/2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 30/2019 ዓ.ም መክፈል እንዳለባቸው ይገልፃል፡፡

በዚህም መሰረት፡-
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 የግብር ዘመን የግብር አከፋፈል ሂደቱ ለግብር ከፋዮቻችን ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ እንዲሆን ከዚህ ቀደም ያልነበሩ አዳዲስ አማራጭ የክፍያ ዘዴዎችን ጨምሮ እነሆ ሊያገለግሎ ተዘጋጅቷል፡፡

በመሆኑም የተከበራችሁ ውድ ግብር ከፋዮቻችን! ዓመታዊ ግብራችሁን፡-
1. ቴሌ ብርን በመጠቀም፣
2. በ CBE birr እና
3. በደራሽ ማለትም የሰነድ ቁጥራችሁን በመያዝ እቀራቢያዎ ወደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመሄድና የተዘጋጀውን ቅፅ በመሙላት አመታዊ ግብራችሁን መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ዓመታዊ ግብርዎን ባሉበት ሆነው በወቅቱ በመክፈል ለሀገሮ ብልጽግና የድርሻዎን ይወጡ!
Facebook የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office

Address

Gofa, Sawla , Ethiopia �
Gofa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሣዉላ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት/Sawla Town Administration Revenue Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share