03/06/2026
የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች ከመለው ህዝብና ከሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ጋር በመሆን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት ግንባር ቀደም ተሳትፎ አቶ ተክሌ ስዩም ምስጋናቸውን አቀረቡ!
የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩሞ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሚናቸውን ለተወጡ ለፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም በምርጫ ሂደቱ ለተሳተፉ ተቋማትና አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፣
ምርጫ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አንዱ መገለጫና በህዝብ የተመረጠ መንግስት ለመመሠረት ትልቅ መሣሪያ ነው፣ ይህ ሂደት ለ7ኛ ዙር በሀገራችን በተካሄደበት በዚህ ወቅት በዞናችን የሚገኙ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ የሚመለከታቸው በሙሉ ከምርጫ ቅስቀሳ እስከ ድምጽ መስጫ ቀን ድረስ ላደረጉት ጠንካራ ተሳትፎ አቶ ተክሌ ስዩም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፣
የብልጽግና ፓርቲ 'ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!' በሚል መሪ ሀሳብ የምርጫ ቅስቀሳውን ሀገረ መንግስትና ብሔረ መንግስት ግንባታ እውን ለማድረግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በመደመርና እሳቤ በማህበራዊ፣ በኢኖሚያዊና በፖለቲካው በሁሉም ዘርፎች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ፓርቲው ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንም ይህም በሰላምና በዲሞክራሲያዊ ህደት የሚረጋገጥ ይሆናልም ነው ያሉት፣
ሰላም ለሁሉም እንቅስቃሴያችን ዋና ነገር በመሆኑ በምርጫ ህደት ውስጥ ለሰላም የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት፣ የመደመር፣ የመተባበርና የመደጋገፍ ባህል ማጎልበት፣ ከነጠላ ትርክት ይልቅ ገዥና አሰባሳቢ ትርክት ለማስፈን ትኩረት በመስጠት በልማትና በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታችን የአስተሳሰብ የበላይነት እንዲያገኝ ትኩረት እንደሚሰጥም በመልዕክታቸው ገልጸዋል፣
በመጨረሻም 7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላምና በውጤታማነት ግቦቹን ያሳካ እንዲሆን ያልተገደበ ድጋፋችሁን ያበረከታችሁ አመራር አካላት፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች፣ ፀጥታ አስከባሪ አካላት እና በምርጫው ህደት ውስጥ ለተሳተፉ በሙሉ አቶ ተክሌ ስዩም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፣
ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት