14/03/2026
የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚታዩ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ አወጣ!
| መጋቢት 5/2018 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር ወቅታዊውን ዓለም አቀፋዊ የነዳጅ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ፣ በከተማችን ፍትሀዊ የነዳጅ ስርጭት እንዲኖርና ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ በዝርዝር አውጥቷል፦
#ዋና ዋና የአቋም መግለጫ ነጥቦች፡
1️⃣ መንግስት ነዳጅን በከፍተኛ ድጎማ እያቀረበ በመሆኑ፣ ስርጭቱ ለህብረተሰቡ ፍትሀዊና ህጋዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን ማረጋገጥ።
2️⃣ በፌደራል የገንዘብ ሚኒስቴር የተቀመጡ የነዳጅ ግብይት አቅጣጫዎችን በአስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋሉ ።
3️⃣ ወቅታዊ ሁኔታን ምክንያት በማድረግ ከተቀመጠው ዋጋ ውጭ ጭማሪ በሚያደርጉ ማደያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ።
4️⃣ ከ17 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች ባሉባት ድሬዳዋ፣ ነዳጅ እያለ "የለም" የሚሉና ክምችት የሚፈጥሩ ማደያዎችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ይካሄዳል ።
5️⃣ በጄሪካን፣ በኮዳና በየሱቁ የሚካሄድ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን እና ሽያጭ ተግባር ሙሉ በሙሉ መቆም ይገባል ።
6️⃣ በሁሉም ወረዳዎች የንግድ ቢሮ፣ ደንብ አስከባሪና የፀጥታ አካላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ቁጥጥር እንዲያደርግ ተመድቧል ።
7️⃣ የነዳጅ ሁኔታን ሽፋን በማድረግ በመሰረታዊ ፍጆታዎች ላይ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
8️⃣ ያላግባብ ዋጋ የጨመሩ የውሃ ፋብሪካዎች በአስቸኳይ ወደ ነበረበት እንዲመልሱ፤ ማንኛውም ማሻሻያ በጥናትና በውይይት ብቻ እንዲወሰን ተብሏል ።
9️⃣ ከዛሬ ጀምሮ የወረዳ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ተግባራትን የመቆጣጠርና የማስቆም ስራን በተቀናጀ መልኩ እንዲጀምሩ ታዟል።
🔟 ማህበረሰቡ ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላትና ለሚዲያ ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ:-የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ!