Dire Dawa ADM. Ethics & Anti Corruption Commission

Dire Dawa ADM. Ethics & Anti Corruption Commission Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dire Dawa ADM. Ethics & Anti Corruption Commission, Government Organization, Dire Dawa.

የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚታዩ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ አወጣ! | መጋቢት 5/2018 ዓ.ምየድሬዳዋ አስተዳደር ወቅታዊውን ...
14/03/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚታዩ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ አወጣ!
| መጋቢት 5/2018 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር ወቅታዊውን ዓለም አቀፋዊ የነዳጅ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ፣ በከተማችን ፍትሀዊ የነዳጅ ስርጭት እንዲኖርና ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ በዝርዝር አውጥቷል፦
#ዋና ዋና የአቋም መግለጫ ነጥቦች፡
1️⃣ መንግስት ነዳጅን በከፍተኛ ድጎማ እያቀረበ በመሆኑ፣ ስርጭቱ ለህብረተሰቡ ፍትሀዊና ህጋዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን ማረጋገጥ።
2️⃣ በፌደራል የገንዘብ ሚኒስቴር የተቀመጡ የነዳጅ ግብይት አቅጣጫዎችን በአስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋሉ ።
3️⃣ ወቅታዊ ሁኔታን ምክንያት በማድረግ ከተቀመጠው ዋጋ ውጭ ጭማሪ በሚያደርጉ ማደያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ።
4️⃣ ከ17 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች ባሉባት ድሬዳዋ፣ ነዳጅ እያለ "የለም" የሚሉና ክምችት የሚፈጥሩ ማደያዎችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ይካሄዳል ።
5️⃣ በጄሪካን፣ በኮዳና በየሱቁ የሚካሄድ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን እና ሽያጭ ተግባር ሙሉ በሙሉ መቆም ይገባል ።
6️⃣ በሁሉም ወረዳዎች የንግድ ቢሮ፣ ደንብ አስከባሪና የፀጥታ አካላትን ያካተተ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ቁጥጥር እንዲያደርግ ተመድቧል ።
7️⃣ የነዳጅ ሁኔታን ሽፋን በማድረግ በመሰረታዊ ፍጆታዎች ላይ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
8️⃣ ያላግባብ ዋጋ የጨመሩ የውሃ ፋብሪካዎች በአስቸኳይ ወደ ነበረበት እንዲመልሱ፤ ማንኛውም ማሻሻያ በጥናትና በውይይት ብቻ እንዲወሰን ተብሏል ።
9️⃣ ከዛሬ ጀምሮ የወረዳ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ተግባራትን የመቆጣጠርና የማስቆም ስራን በተቀናጀ መልኩ እንዲጀምሩ ታዟል።
🔟 ማህበረሰቡ ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላትና ለሚዲያ ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ:-የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ!

 'aa deeggarsan argame gabaa gurraachaaf kuusuun seeraan nama Gafachisa!"Benziili seeraan ala kuufame liitira 350 ol Tah...
28/02/2026

'aa deeggarsan argame gabaa gurraachaaf kuusuun seeraan nama Gafachisa!"

Benziili seeraan ala kuufame liitira 350 ol Tahatame.

Dhawaa| Gurraandhala 21,2018

Buufanni Poolisii Saabiyaan akka beeksisetti benziin liitira 350 ol kan seeraan ala Magaalaa Dirree Dhawaa Araddaa 02 naannolee ganda Ruwaandaa fi Booran jedhamuun beekaman keessatti kuufamee ture opireeshinii poolisiin gaggeeffameen to’annoo jala ooluu beeksise.

Buufata Poolisii Saabiyaaniti Qindeesitu Garee Qorannoo yakkaa tan Taate gargaartun Innispektara Dasta Ayyalawu yaada miidiyaa poolisii Dirree Dhawaaf Laataniin Beenzili kun kan argame odeeffannoo hawaasa irraa argame irratti hundaa’uun hordoffii cimaa taasifameen akka Toohatame ibsaniti jiru.

Itti dabaluudhaanis operaashini kanaan beenzila liitira 350 ol mana namoota dhuunfaa lamaa keessatti argamuu fi namoota dhuunfaa lama gocha kanaan shakkaman to’annoo jala ooluu fi qorannoon irratti gaggeeffamaa jiraachuu ibsaniiru.
"Boba'aa mootummaan deeggarsa ol'aanaan ummataaf dhiheessu seeraan ala gabaa gurraachaaf itti fayyadama dhuunfaaf gurguruun seeraan kan adabsiisudha waan taheef nutis Poolisiin Dirree Dhawaa callisnee hin ilaallu," jedhan Gargaartun Inispeektara Deestaa Ayyaaleewu, akkasumaas poolisiin hordoffii duraan gochaa ture sadarkaa fooyya’aa ta’etti guddisuun hojiiwwan seeraan alaa bakka fi mana jireenyaa kamittuu hordofuu fi to’annoo jala oolchuuf qophii ta’uu ibsanii jiru.

Poolisiin namoonni dhuunfaa gocha yakkaa kana keessatti hirmaatan itti gaafatamummaa seeraa jalaa akka hin baane fi tarkaanfiin cimaan akka isaan irratti fudhatamu cimsee Hojjachuu akka qabu, akkasumas Miidha gochi kun nagaa fi Tasgabbii magaalattii irratti fidu keessumaa gama balaa ibiddaatin fidu hubachuun of eeggannoo gochuu fi gocha isaanii kana irraa akka of qusatan Dhaamaniiru jiru.
Qajeelchi waliigalaa gochoota Seeraan Alaa ittisuu fi Tohachuu irratti cimsee kan itti fufuu yoo tahu Hawaasni gama isaanitin Eeruu fi sochii Taasiisa Jiru cimsee itti fufuu akka qabu waamicha dhiheesani jiru.
​ :- Qajeelcha waliigalaa poolisii dirree dhawaa

"በድጎማ የሚመጣውን ነዳጅ ለጥቁር ገበያ ማከማቸት በህግ ያስጠይቃል!"በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ ከ350 ሊትር በላይ ቤንዚን በቁጥጥር ስር ዋለ።​ #ድሬዳዋ | የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ....
28/02/2026

"በድጎማ የሚመጣውን ነዳጅ ለጥቁር ገበያ ማከማቸት በህግ ያስጠይቃል!"

በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ ከ350 ሊትር በላይ ቤንዚን በቁጥጥር ስር ዋለ።

​ #ድሬዳዋ |
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ ከተማ በወረዳ 02 ልዩ ስሙ ሩዋንዳ ሰፈር እና ቦረን ተብለው በሚጠሩ አካባቢዎች፣ በህገ-ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ350 ሊትር በላይ ቤንዚን በፖሊስ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር መዋሉን የሳቢያን ፖሊስ ጣቢያ አስታወቀ።

​በሳቢያን ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ደስታ አያሌው ለድሬ ፖሊስ ሚዲያ እንደገለጹት፤ ግኝቱ ሊገኝ የቻለው ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መነሻነት በተደረገ ጥብቅ ክትትል መሆኑን ገለፀው በኦፕሬሽኑ በሁለት ግለሰቦች መኖሪያ ቤት ውስጥ ከ350 ሊትር በላይ ቤንዚን እና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገለፀዋል ።

​መንግስት ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል በከፍተኛ ድጎማ የሚያቀርበውን ነዳጅ፣ ለግል ጥቅም በማዋል በህገ-ወጥ መንገድ ለጥቁር ገበያ ማቅረብ በህግ ያስቀጣል፣ እኛም ድሬዳዋ ፖሊስ በዝምታ አንመለከትም" ያሉት ረዳት ኢንስፔክተር ደስታ አያሌው፤ ፖሊስ ከዚህ ቀደም ሲያደርግ የነበረውን ክትትል ወደ ተሻለ ደረጃ በማሳደግ፣ በየትኛውም ቦታ እና መኖሪያ ቤት ውስጥ የሚደረጉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመከታተል በቁጥጥር ስር ለማዋል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

​በዚህ የወንጀል ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጡና ጠንካራ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው፤ እንዲሁም ድርጊቱ በከተማዋ ሰላምና ደህንነት በተለይም የእሳት አደጋ ስጋት ላይ የሚፈጥረውን አደጋ ተረድተው ጥንቃቄ እንዲያደርጉና ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ፖሊስ በጥብቅ አሳስቧል።

​ድሬዳዋ ፖሊስ መሰል ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የሚያደርገውን ክትትል አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ህብረተሰቡም እያደረገ ያለውን ጥቆማና ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

"Zero Tolerance" (ምንም ዓይነት ይቅርታ የሌለው)

​ #ምንጭ:- የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

በድሬዳዋ በጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊውል የነበረ ናፍጣ ከነአሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ዋለ። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በከተማዋ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ "መሬት ልማት ፊት ለፊት" ተብሎ በሚጠራው...
27/02/2026

በድሬዳዋ በጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊውል የነበረ ናፍጣ ከነአሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ዋለ።
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በከተማዋ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ "መሬት ልማት ፊት ለፊት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ በህገ-ወጥ መንገድ በጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ ሲጓጓዝ የነበረ 600 ሊትር ናፍጣ ከነአሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።

በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሀሎሌ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ም/ኮማንደር መሳይ ተስፋዬ ለድሬ ፖሊስ ሚዲያ እንደገለጹት፤ የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት 7:00 ሰዓት ላይ በፖሊስ አባላት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ነዳጁ ሲጓጓዝ የነበረው የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-73282 ኦሮ በሆነ የኤፍሳር ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻላቸው ተገልጿል።

​ም/ኮማንደር መሳይ እንደገለጹት፣ አሽከርካሪው በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ በምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ ገለፀው የነዳጅ ግብይት በህጋዊ ስርዓት ብቻ ሊከናወን እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይ ነዳጅን በመኖሪያ ቤትም ሆነ በተለያዩ ስፍራዎች ያለፈቃድ ማከማቸት በህግ የሚያስጠይቅ ከመሆኑ ባለፈ፣ በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ ሊያስከትል እንደሚችልም በመረዳት በእንደዚህ አይነት ተግባር ላይ የሚሰማሩ ግለሰቦች መጠናቀቁ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መሰል ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከልና ተጠርጣሪዎችን ለህግ ለማቅረብ የሚያደርገውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለጽ፤ ህብረተሰቡ መሰል ድርጊቶችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።

​ተቋሙ ከዚህ ቀደምም መሰል የኢኮኖሚ አሻጥር ተግባራትን በመከላከል ረገድ ውጤታማ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወሳል።
ምንጭ :-የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

26/02/2026

#ዜና በድሬዳዋ አስተዳደር የባህል ፍርድ ቤት ምክር ቤት ተቋቋመ

የድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህ ጸጥታ እና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ከድሬዳዋ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ጋር በመተባበር በዛሬው እለት የባህል ፍርድቤት ምክር ቤት በይፋ ተቋቁሟል።

በአስተዳደሩ ምክር ቤት የባህል ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 87/2017 መቋቋሙ ይታወቃል ባህላዊ ፍርድቤቶች ባህላዊ ህጎች እና እሴቶችን በመጠበቅ እና በማሳደግ የፍትህ ተደራሽነትን በማረጋገጥ የማይተካ ሚና አላቸው።

በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ንግግራቸው እንዳስታወቁት በፍትህ ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የፍትህ ስርዓቱን በማዘመን ብሎም የትራንስፎርሜሽን እቅድ በማሳካት ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል።

የማህበረሰብን ፍትህ አገልግሎትን ለማሻሻልም
ባህላዊ ፍርድ ቤቱ የህብረተሰቡን ወግና ባህልን ተከትለው በህግ እውቅና ተሰጥቷቸው የፍትህ ስርዓቱን ውጤታማ በማድረግ በኩል አይነተኛ ሚና አንደሚጫወቱ ገልጸዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህ ጸጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አቡዱሰላም መሀመድም በበኩላቸው ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ግጭቶችን ከማስወገድም ባለፈ የተለያዩ ጉዳዮችንም ጭምር የሚዳኝ በመሆኑ የመደበኛ ፍርድ ቤት ጫናን በእጅጉ የሚቀንስ መሆኑንም ነው ያስረዱት።

በመርሃ ግብሩም የባህላዊ ፍርድ ቤቶች እውቅና ማቋቋሚያ ላይ የተዘጋጀ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር፣በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎች ኡጋዞች የጸጥታ አካላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ሰላም ለማ
ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ
የካቲት 19/2018

02/02/2026
ናፍጣ ለመቅዳት የተሰለፉ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ገንዘብ ሲጠይቁ የነበሩ የማድያ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
02/02/2026

ናፍጣ ለመቅዳት የተሰለፉ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ገንዘብ ሲጠይቁ የነበሩ የማድያ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

Tumsa Malaammaltummaa dhabamsiisuuf taasifamu keeysatti gumaachi shamarranii olaanaa tahuun ibsame.
17/01/2026

Tumsa Malaammaltummaa dhabamsiisuuf taasifamu keeysatti gumaachi shamarranii olaanaa tahuun ibsame.

👉ከንቲባ ከድር ጁሀር ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።የድሬዳዋ  አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለገና በዓል የእንኳን አደረሳች...
06/01/2026

👉ከንቲባ ከድር ጁሀር ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከንቲባው በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረው የገና በዓል የስጦታ እና የልግስና በዓል መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በዓሉን ስናከብር በተለያዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ወገኖችን በተለይም ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው አቅመ ደካማ አረጋውያንን፣ ወላጆቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ያጡ ህጻናትን፣ታምመው አልጋ ላይ የዋሉ ሕሙማንን በማሰብና የበዓሉ ደስታ የእነሱም እንዲሆን በማድረግ ልናሳልፍ ይገባል ብለዋል።

ከንቲባው በዓሉ የሰላም የፍቅር፣ የጤና፣ የብልጽግና የመደጋገፍና የመተጋገዝ ይሁንልን ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል ።

መረጃው - የድሬዳዋ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው

 #ዜና /ስነ-ምግባራዊና ቅንጅታዊ አሰራርን በማሳደግ የማህበረሰቡን እርካታ የሚጨምር አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተጠቆመ  ታህሳስ 14/2018
23/12/2025

#ዜና /ስነ-ምግባራዊና ቅንጅታዊ አሰራርን በማሳደግ የማህበረሰቡን እርካታ የሚጨምር አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተጠቆመ
ታህሳስ 14/2018

 # Oduu | Duudhaalee hawaasaa fayyadamuun malaammaltummaa fi hojimaata badaa ittisuun ga'ee  hawaasa hundaati jedhame  M...
17/12/2025

# Oduu | Duudhaalee hawaasaa fayyadamuun malaammaltummaa fi hojimaata badaa ittisuun ga'ee hawaasa hundaati jedhame

Mudde 7/2018

Yaasin Abdallaatiin
Suuraa:-Teedroos Lulsag

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa ADM. Ethics & Anti Corruption Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share