የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office

የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office ይህ ትክክለኛ የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ገጽ በመሆኑ ይከታተላሉ ።

Permanently closed.
03/06/2026

7ኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ!

03/06/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እቴነሽ በየነ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስመልክተው ለክልሉ ሴቶች የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ።

ኃላፊዋ በመልዕክታቸው 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና የክልሉ ሴቶች በስፋት ተሳታፊ የሆኑበት ሆኖ መጠናቀቁ ትልቅ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ታሪካዊ ሂደት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶች ያደረጉት ንቁ ተሳትፎ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ጠቅሰው፣ በመራጮች ምዝገባ፣ በምርጫ ስነ-ምግባር ማክበር፣ ግንዛቤ በመፍጠርና በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ያሳዩትን ኃላፊነት አድንቀዋል።

የክልሉ ሴቶች ያለባቸውን ተደራራቢ ኃላፊነት በብቃት ከመወጣት ባለፈ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲያዊ ሂደት ስኬት ያሳዩት ቁርጠኝነት በታሪክ የሚወሳ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይም የለሊቱ ብርድ፣ የቀኑ ፀሐይ፣ በየምርጫ ጣቢያው የነበሩ ረጃጅም ሰልፎች ሳይበግራቸዉ በፅናት ድምፃቸውን ለሰጡ ነፍሰ-ጡር እናቶች፣ አራስ እናቶች፣ ከህመማቸው ጋር እየታገሉ ድምፃቸውን ለሰጡ ሴቶች በሙሉ ያላቸው ክብር ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ሴቶች ይህንን ንቁ ተሳትፎና ሀገራዊ ኃላፊነት በማስቀጠል በድህረ-ምርጫ ስራዎች፣ መንግስትን ለማፅናት በሚከናወኑ ተግባራትና በአጠቃላይ በሁለንተናዊ ብልፅግና ስራዎች ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የምርጫው ይፋዊ ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስኪገለፅ ድረስ ሁሉም ሴቶች ህግና ሥርዓትን በማክበር በትዕግስት እንዲጠባበቁ አሳስበዋል።

በዲላ ከተማ የሚገኙ 60 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ህዝቡ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ድምጽ መስጠቱ ተገለጸዲላ፡ግንቦት፣25/09/2018 ዓ.ም በዲላ ሪጂዮ ፖሊስ ከተማ በ2 ክፍለ ከተ...
02/06/2026

በዲላ ከተማ የሚገኙ 60 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ህዝቡ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ድምጽ መስጠቱ ተገለጸ

ዲላ፡ግንቦት፣25/09/2018 ዓ.ም በዲላ ሪጂዮ ፖሊስ ከተማ በ2 ክፍለ ከተማና 12 ቀበሌያት በሚገኙ 60 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ድምጽ መስጠቱን የዲላ ከተማ ሠላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጂክሶ ተናግረዋል።

አቶ አለማየሁ አክለውም የመጡ ውጤቶችን በጸጋ በመቀበል ወጣቶችም ሆኑ መላው የማህበረሰብ ክፍሎች በድምጽ መስጫ ወቅት ያሳዩትን ጨዋነት ማስቀጠል እንደሚገባቸው ገልጸው ህብረተሰቡም ሆነ የጸጥታ ተቋማቱ በሰላም ምርጫውን በማከናወናቸው የጸጥታ አካላትን አመስግነዋል።

በተያያዘ ዜና በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁ ታውቋል።

የጌዴኦ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽብሩ ሚጁ እንደገለጹት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግብ ጥለው መንቀሳቀሳቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ በሚገኙ 5 መቶ 47 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ሂደቱ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር መጠቃለሉን የገለጹት አቶ ሽብሩ ከዞን እስከ ቀበሌ የጸጥታውን ሥራ በተገቢው መንገድ ያከናወኑ ሰላም አስከባሪዎችን አመስግነዋል።

የዲላ ከተማ የአስፓልት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) አሳሰቡዲላ፡ግንቦት፣25/2018ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲላ ከተማ አስተዳደር የታቀዱ...
02/06/2026

የዲላ ከተማ የአስፓልት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) አሳሰቡ

ዲላ፡ግንቦት፣25/2018ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲላ ከተማ አስተዳደር የታቀዱ የአስፋልት እና የኮሪደር ልማት ግንባታ ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) አሳሰቡ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዲላ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ ልዩ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይም ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ላይ አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት እስካሁን ባለው ሂደት በተቋራጩ በኩል የተደረገው ቅድመ ዝግጅትና ለአስፋልት ግንባታ የሚውል የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅርቦት አፈጻጸም መልካም የሚባል እንደሆነ አንስተዋል።

በከተማዋ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዲላን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለሕዝቡ ያላቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የጎላ መሆኑን ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

በመሆኑም እነዚህ የልማት ሥራዎች በሚቀጥሉት ጊዜያት በፍጥነትና በጥራት መከናወን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ለዚህም ከክልሉ ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ጋር በጋራ በመሥራት ግንባታዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አብድሳ ኩፎ በበኩላቸው የአስፋልትና የኮሪደር ልማት ሥራዎቹ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ተቋማቸው የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።

ኢንተርፕራይዙ የተጣለበትን የማማከር፣የቅርብ ክትትልና የቁጥጥር ሥራ በትጋት እንደሚወጣ ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶቹ ያለምንም መስተጓጎል በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን የቅርብ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ከንቲባው አረጋግጠዋል።

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በነቂስ ለወጣው የከተማው ማህበረሰብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀረቡ #ዲላ ግንቦት 25/2018ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ ሁ...
02/06/2026

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በነቂስ ለወጣው የከተማው ማህበረሰብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀረቡ

#ዲላ ግንቦት 25/2018

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከተሎ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ አቶ መንግስቱ ተክሌ ለከተማው ነዋሪዎች ደማቅና ልባዊ የደስታና የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

ነዋሪዎቹ ለአስተማማኝ የሀገር መንግሥት ግንባታ፣ ለዴሞክራሲ ባህል መጎልበትና ለሀገር ቀጣይነት ሲሉ ያሳዩት በጎና ታሪካዊ ሚና እጅግ የሚደነቅ መሆኑን አቶ መንግስቱ ገልጸዋል።

አቶ መንግስቱ ተክሌ ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ነዋሪው ያደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ የሕዝቡ የፖለቲካ ብስለትና ለሀገር ሰላም ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

ነዋሪው ያሳየውን ወደር የለሽ ጽናትና ታሪካዊ ተጋድሎ ያወሱት ኃላፊው፣ የከተማው ሕዝብ የጠዋቱን ብርድና የቀትሩን የፀሐይ ሐሩር በጽናት ተቋቁመው፣ ለግል ምቾቱና ለሆዱ ሳይጨነቅ፣ የምሽት እንቅልፍ ሳይገታው ሀገራዊ ጥሪውን አስቀድሟል።

ጠንካራና ጽኑ መንግሥት ለመትከል ካለው ብርቱ ፍላጎት የተነሳ፣ ከማለዳው 11:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ድረስ ረጅም ሰዓታትን በሰልፍ በመሰለፍ የበኩሉን አሻራ በማኖር የከተማ ሕዝብ በምርጫ ካርዱ የሀገርን አንድነትና ቀጣይነት ማስቀደሙን በኩራት ገልጸዋል።

"ውድ የከተማችን ነዋሪዎች፤ እናንተ በተግባራችሁ ኢትዮጵያን መርጣችኋል! በመሆኑም ለዚህ ታላቅና ታሪካዊ ተግባራችሁ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባችኋል" ሲሉ አክብሮታቸውን ገልጸዋል።

ይህ ታሪካዊ ስኬት ለከተማዋም ሆነ ለሀገሪቱ ቀጣይ የልማትና የዲሞክራሲ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሰነቀ ምዕራፍ መሆኑ ተመልክቷል።

የዲላ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን አስታወቀ‎‎ዲላ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ/ም ‎‎በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራ...
02/06/2026

የዲላ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን አስታወቀ

‎ዲላ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ/ም

‎በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን የዲላ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታዉቋል።

‎የጋራ ምክር ቤት የምርጫ ሂደቶችን በሚመለከት ችግር አለመኖሩን እና ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን የዲላ ከተማ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ታጠቅ ወርቁ አንስተዋል።

‎እንደ ዲላ ከተማ እስከ አሁን ድረስ ምንም አይነት ቅሬታ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች አለመቅረቡን የተናገሩት አቶ ታጠቅ የምርጫ ዉጤትም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል ።

‎ጌዴኦ ቲቪ

02/06/2026

የርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የምስጋና መልዕክት ፦

ኢትዮጵያ በታሪክ ሰሪ ልጆቿ ዳግም አሸንፋለች!

በትላንትናው ዕለት የተካሄደዉ ታሪካዊው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እጅግ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ጠብቆ በስኬት በመጠናቀቁ የተሰማኝን ልባዊ ደስታ ለመግለፅ እወዳለሁ፡፡

መላው የክልላችን ህዝቦች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እና አሁን ደግሞ በድህረ ምርጫ ወቅት ለሀገራችን መፃይ ብሩህ ተስፋ ቀናኢ በመሆን በምታሳዩት ትጋት እና ፅናት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዟችንን በማፅናት ዳግም አሸናፊ እንድንሆን አስችሎናል።

ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና እጩዎች ህዝብ በነፃነት የሰጠውን ድምፅ እና የገለጸውን ፍላጎት ሁሉም በፀጋ እና በክብር በመቀበል በጋራ በመተባበር ሀገርን ለማሻገር ትልቅ አደራ ተቀብለናል።

በዚህ አጋጣሚ በክልላችን እንደ ሀገር ለምናልመው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ዕውን መሆን በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ድምጻችሁን የሰጣችሁ ዜጎች እንዲሁም በምርጫው የተሳተፋችሁ የተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ተወዳዳሪዎች የምርጫው ሂደት ሰላማዊ፤ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላችሁን ሚና በመወጣት ላበረከታችሁት ጉልህ አስትዋጽኦ በክልሉ ህዝብና መንግስት ስም ልባዊ ምስጋና ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

እንደዚሁም የምርጫ አስፈጻሚዎች፤ ታዛቢዎች፤ የሲቪክ ማህበራትና ሚዲያዎች እንዲሁም የፀጥታና ደህንነት አካላት የምርጫው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እጅግ ሰላማዊ፤ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ ሁኔታ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከታችሁት የላቀ አስትዋጽኦ ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡

በመጨረሻም በቅድመ ምርጫና በምርጫው የታየዉ ህዝባዊ አንድነት የድህረ ምርጫው ሂደትም እጅግ በሰከነና በሰላማዊ በሆነ መንገድ በማስኬድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ስኬት በጋራ በመረባረብ የህዝባችን ተጠቃሚነት እዉን ለማድረግ ሁላችንም የድርሻችንን እንድንወጣ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ይባርክ!

በዲላ ከተማ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ከንቲባው ምስጋና አቀረቡ #ዲላ ግንቦት 25/2018በዲላ ከተማ የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬትና በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ...
02/06/2026

በዲላ ከተማ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ከንቲባው ምስጋና አቀረቡ

#ዲላ ግንቦት 25/2018

በዲላ ከተማ የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬትና በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ፣ የከተማዋ ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ለነዋሪዎችና ለባለድርሻ አካላት በሙሉ "ልዩ ምስጋና" አቀረቡ።

ከንቲባው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሰኞ ዕለት መራጩ ህዝብ ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በነፃነት ድምፁን ለመስጠት ያሳየውን ፅናት እና የሀገር ፍቅር እጅግ የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ኢትዮጵያ በማንኛውም ወጀብ የማትበገር እና የራሷን ዕጣ ፈንታ በራሷ መወሰን የምትችል ብርቱ ሀገር መሆኗን ዛሬም በፅናት ያረጋገጠችበት ሂደት ነው ብለዋል።

የምርጫውን ሂደት አስመልክቶ ከንቲባው በሂደቱ ላይ የተሳተፉ ሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላሳዩት መልካም ሥነ-ምግባር እና ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላደረጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ምስጋና ይገባቸዋል ስሉ ገልጸዋል።

የምርጫው የመጨረሻ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ሲደረግ የሚታወቅ ስሆን ለዴሞክራሲ ባህል መጎልበት የበኩላቸውን ለተወጡ መራጮች፣ ዕጩዎች፣ የምርጫ አስፈፃሚዎች፣ ታዛቢዎች እንዲሁም በፀሎት ላገዙ የእምነትና የባህል አባቶች በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሳቸው ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

"ፈጣሪ ዲላንና ኢትዮጵያን ይባርክ!"

02/06/2026
02/06/2026

እንኳን ደስ አለን! 🇪🇹 ኢትዮጵያ መርጣለች! 🇪🇹

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ያስከበረና ያረጋገጠ ምርጫ ኢትዮጵያ መርጣለች!

🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share