06/06/2026
ከየትነበርሽ-በርካ-ቶልታ መንገድ ሥራ ተጀምሯል
በክልሉ ገጠር መንገድ ድስትርክት በኣሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ የትነበርሽ በርካ ቶልታ የመንፐድ ሥራ ተጀምሯል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ጂንካ ድስትርክት ስራ አስኪያጅ አቶ ል ልየው ከአሪ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛዉ ሃይሌ በጋራ በመሆን በዞኑ ደቡብ ኣሪ ወረዳ የትነበርሽ-በርካ-ቶልታ መንገድ ሥራ ከክልሉ ገጠር መንገድ ድስትርክት ጨረታ አሸናፎ የነበረው ኮንትራክተር እያከናወነ ያለዉን ስራ ምልከታ አድርገዋል።
የተጀመረዉ የመንገድ ጥገና ስራ ከምርጫ ማግስት ጀምሮ ወደ መደበኛ ስራዉ መግባቱን ኃላፊዎቹ በቦታዉ ተገኝተዉ ተመልክተዋል።
መረጃው የኣሪ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው