South Ethiopia Region Road Authority

South Ethiopia Region Road Authority Official page of South Ethiopia Region Road Authority

ከየትነበርሽ-በርካ-ቶልታ መንገድ ሥራ ተጀምሯል በክልሉ ገጠር መንገድ ድስትርክት በኣሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ የትነበርሽ በርካ ቶልታ የመንፐድ ሥራ ተጀምሯል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች...
06/06/2026

ከየትነበርሽ-በርካ-ቶልታ መንገድ ሥራ ተጀምሯል

በክልሉ ገጠር መንገድ ድስትርክት በኣሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ የትነበርሽ በርካ ቶልታ የመንፐድ ሥራ ተጀምሯል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ጂንካ ድስትርክት ስራ አስኪያጅ አቶ ል ልየው ከአሪ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛዉ ሃይሌ በጋራ በመሆን በዞኑ ደቡብ ኣሪ ወረዳ የትነበርሽ-በርካ-ቶልታ መንገድ ሥራ ከክልሉ ገጠር መንገድ ድስትርክት ጨረታ አሸናፎ የነበረው ኮንትራክተር እያከናወነ ያለዉን ስራ ምልከታ አድርገዋል።

የተጀመረዉ የመንገድ ጥገና ስራ ከምርጫ ማግስት ጀምሮ ወደ መደበኛ ስራዉ መግባቱን ኃላፊዎቹ በቦታዉ ተገኝተዉ ተመልክተዋል።
መረጃው የኣሪ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ቢሮ ከገደብ እስከ ባንቆ ጣጣቱ ድረስ እየተገነባ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት ጎበኘ #ዲላ ግንቦት 27/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን በወረ...
04/06/2026

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ቢሮ ከገደብ እስከ ባንቆ ጣጣቱ ድረስ እየተገነባ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት ጎበኘ

#ዲላ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን በወረዳው ከገደብ እስከ ባንቆ ጣጣቱ ቅልጤ ድረስ እየተገነባ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት ጉብኝት አድርጓል።

በጉብኝቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ኃላፊ አቶ ተሾሜ ሩፎ ፣ የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ታደሰ ፣ የክልሉ የማኔጅመንት አካላት እና የወረዳው ወንዱ አየለ የትራንስፖርት እና መንገድ ጽ/ቤት ኃላፊ ተገኝቷል።

ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ለማህበረሰቡ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድሰጥ በትኩረት እየተሰራበት ስሆን አሁን ያለበት ደረጃም ጥሩ መሆኑንም በጉብኝት ወቅቱ ተመላክቷል።

@ዘገባው የጌዴኦ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው!

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስ...
02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!!!
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!!!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ *******************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋ...
01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ
*******************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልሎት ክፍት ተደረጉ‎‎ ግንቦት 19-2018 ዓ/ምበዞኑ ወናጎ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ  ፕሮጀክቶች ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ...
27/05/2026

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልሎት ክፍት ተደረጉ

‎ ግንቦት 19-2018 ዓ/ም

በዞኑ ወናጎ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።

‎ለአገልግሎት ክፍት ከተደረጉ አገልግሎት ሰጪ ፕሮጀክቶች መካከል የህዝብ ፓርክ፣ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ቤት እና የእናቶች ማዋለጃ አገልግሎት ማስፋፍያ ይገኙበታል።

‎በምረቃ መርሃግብር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳር አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር)፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር)፣ የወናጎ ከተማ ከንቲባ አቶ ብርሃኑ ተካዬ ጨምሮ የክልልና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ የባህል መሪዎች እና ህብረተሰብ ክፍል ተገኝቷል።

‎@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተደድር አበባየሁ ታደሰ (ዶክተር) የተመራ የስራ ኃላፊዎች በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ የመንገድ ስራ ምልከታ አደረጉግንቦት 19/2018 ዲላበጌዴኦ ዞን ...
27/05/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተደድር አበባየሁ ታደሰ (ዶክተር) የተመራ የስራ ኃላፊዎች በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ የመንገድ ስራ ምልከታ አደረጉ

ግንቦት 19/2018 ዲላ

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ከአዲስቆፌ- ሞኮኒሳ-ባንቆ ኦክቶ ጥገና መንገድ ስራ እንዲሁም ሞኮኒሳ-ዶዶሮ አዲስ መንገድ ከፈታ ስራ ያለበት ደረጃ ምልከታ ተደርጓል

መንገዱ በአከባቢው በስፋት የሚመረተውን የቡና ምርት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማሳለጥ በአከባቢው የሚመረተው ምርት በጥራትና በስፋት ወደ ገበያ በማቅረብ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተመላክቷል።

በምልከታው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራ ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶክተር) የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶክተር) የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ ተሾመ ሩፎ ተገኝተዋል።

በወላይታ ዞን ኦፋ ወረዳ ከ 6.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው ድልድይ ተመረቀግንቦት 19/2018 ዓ.ምበወላይታ ዞን ኦፋ ወረዳ ከ 6.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው...
27/05/2026

በወላይታ ዞን ኦፋ ወረዳ ከ 6.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው ድልድይ ተመረቀ

ግንቦት 19/2018 ዓ.ም

በወላይታ ዞን ኦፋ ወረዳ ከ 6.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው ድልድይ ተመርቋል።

ድልድዩን በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሪሁን ፍቅሩ፣ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መለሰ መና እንዲሁም የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በጋራ መርቀዉ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርገዋል።

ድልዲዩ ለረጅም ጊዜያት የሕብረተሰብ ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን የኦፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዲሱ ወርቁ ተናግረዋል።

ከ 6.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባው ድልድይ በዞኑ ሁምቦ፣ ኦፋ እና ባይራ ኮይሻ ወረዳዎችን የሚያገናኝ እንደሆነ አስረድተዋል።

በወረዳው ኦፋ ወረዳ ቡሻ ቀበሌ የተገነባዉ የኦፋ ኤሾ ድልዲይ አስፈላጊውን የጥራት ደረጃዎች የተሟሉለት መሆኑም ተመላክቷል።

በመርሃ-ግብሩ የክልል፣ የወላይታ ዞንና የኦፋ ወረዳ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና እንግዶች ተገኝተዋል።

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን፣ በዓሉ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የሰላምና በበረከት የተሞላ እንዲሆንላ...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን፣ በዓሉ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የሰላምና በበረከት የተሞላ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።

ዒድ አል-አድሃ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳት፣ የመቻቻልና የእምነት ጽናት ምልክት የሆነ ታላቅ በዓል ነው። ስለሆነም በዓሉን ስናከብር ለተቸገሩ ወገኖች እጅ በመዘርጋት፣ ፍቅርን በመጋራትና አንድነታችንን በማጠናከር ልናከብር ይገባል።

አላህ የሰላም፣ የጤናና የበረከት በዓል ያድርግልን!!
🌙 ዒድ ሙባረክ! 🌙
እንጂነር እድሬ እርኮ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ-አል-አድሃ( ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ
27/05/2026

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ-አል-አድሃ( ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ

Address

Dilla Front Of Donbosko School
Dilla
P.O.BOX404

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Region Road Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share