South Ethiopia Region Road Authority

South Ethiopia Region Road Authority Official page of South Ethiopia Region Road Authority
(1)

✈️ በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ እየተገነባ ያለው መለስተኛ የአውሮፕላን ማረፊያ በፍጥነት እየተሠራ ነውበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙ አራት መለስተኛ የአውሮፕላን ማረፊ...
06/09/2026

✈️ በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ እየተገነባ ያለው መለስተኛ የአውሮፕላን ማረፊያ በፍጥነት እየተሠራ ነው

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙ አራት መለስተኛ የአውሮፕላን ማረፊያዎች መካከል፣ በደቡብ ኦሞ ዞን በዲመካ ከተማ እየተገነባ ያለው መለስተኛ የአውሮፕላን ማረፊያ አንዱ ነው።

ፕሮጀክቱን በተያዘው ዕቅድ መሠረት ለማጠናቀቅ ሥራው በፍጥነትና በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር እድሬ እርኮ፣ ፕሮጀክቱ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም ሥራው በትኩረት በማስቀጠል በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

© SERA Communication

መንገድ በከፍተኛ ወጪ የሚገነባ ልማት ነው፤ መጠበቅ ግን የሁላችንም ኃላፊነት ነው!መንገድ በከፍተኛ ገንዘብ፣ ጊዜና ሀብት የሚገነባ ዘላቂ መሠረተ ልማት ነው። ይህን ልማት በአግባቡ ካልጠበቅን...
03/09/2026

መንገድ በከፍተኛ ወጪ የሚገነባ ልማት ነው፤ መጠበቅ ግን የሁላችንም ኃላፊነት ነው!

መንገድ በከፍተኛ ገንዘብ፣ ጊዜና ሀብት የሚገነባ ዘላቂ መሠረተ ልማት ነው።

ይህን ልማት በአግባቡ ካልጠበቅንና ካልተንከባከብን በተለይም በዝናብ ወቅት ለጉዳት ሊጋለጥ ይችላል።

ከተበላሸ በኋላ ደግሞ መልሶ ለመጠገን ወይም ለመገንባት ከፍተኛ ወጪ፣ ጊዜና ሀብት ያስፈልጋል።

በተለይም በቀጣይ ግዜያት በአገሪቱ በርካታ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የክረምት ዝናብ ሊዘንብ እንደሚችል የሚቲዎሮሎጂ ትንበያዎች በማመላከታቸው፣ የመንገድ መሠረተ ልማትን ከዝናብና ከጎርፍ ጉዳት መጠበቅ የበለጠ ትኩረት ይጠይቃል።

የጎርፍ መፍሰሻ ቦዮችን ንፁህ ማድረግ፤ ቆሻሻን በመንገድና በጎርፍ መፍሰሻ ቦዮች ላይ አለመጣል፤ የውሃ ፍሰት እንዳይዘጋ መከላከል፤ የመንገድ ዳርቻን፣ የውሃ ማስወገጃ ቦዮችንና ተያያዥ መዋቅሮችን ከጉዳት መጠበቅና የመንገድ መሠረተ ልማቱን ሊያበላሹ ከሚችሉ ድርጊቶች መቆጠብ እያንዳንዱ ዜጋ ሊያበረክተው የሚችለው ቀላል ቢመስልም ወሳኝ አስተዋፅዖ ነው።

እነዚህ ጥንቃቄዎች ካልተደረጉ የጎርፍ ውሃ ከተፈጥሯዊ ፍሰቱ ወጥቶ በመንገድ ላይ ሊፈስ ይችላል።

ይህም መንገዱንና ተያያዥ መዋቅሮችን ከማበላሸት ባለፈ፣ በአካባቢው የጎርፍ አደጋ እንዲከሰትና በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ ሊያደርግ ይችላል።

ስለሆነም የመንገድ መሠረተ ልማትን ከብልሽት በመጠበቅ የመንገድ ልማቱን ዘላቂነት ማስጠበቅ እና በጎርፍ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ መቀነስ ሁለት ውጤቶችን በአንድ ሥራ የምናሳካበት ተግባር ነው።

የተገነባውን መንገድ ዛሬ እንጠብቅ፤ የመንገድ ልማት ዘላቂነትን እናረጋግጥ፤ ሕዝብንና ንብረትን ከጎርፍ አደጋ እንጠብቅ!

‎ኢንጂነር እድሬ ኢርኮ
‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

© SERA Communication

ከጊዶሌ–ቡሳ-ባሶ 15 ኪ.ሜ የመንገድ ደረጃ ማሻሻያ ሥራ ተጀመረነሐሴ 23/2018 ዓ.ምበጋርዱላ ዞን ከጊዶሌ ከተማ እስከ ቡሳ-ባሶ የሚዘልቀው 15 ኪ.ሜ የመንገድ ደረጃ ማሻሻያ ሥራ፣ ቀደም ...
29/08/2026

ከጊዶሌ–ቡሳ-ባሶ 15 ኪ.ሜ የመንገድ ደረጃ ማሻሻያ ሥራ ተጀመረ

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም

በጋርዱላ ዞን ከጊዶሌ ከተማ እስከ ቡሳ-ባሶ የሚዘልቀው 15 ኪ.ሜ የመንገድ ደረጃ ማሻሻያ ሥራ፣ ቀደም ሲል በነዳጅ እጥረት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ሥራ እንደገና ተጀምሮ በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።

የጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግንኙነት ኪታሞ እንደገለጹት፣ የ15 ኪ.ሜ የመንገድ ማሻሻያ ሥራው ጋርዱላ ዞንን ከአሌ እና ጋሞ ዞኖች ጋር በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች የሚያስተሳስር አስፈላጊ የመንገድ መሠረተ ልማት ነው።

መንገዱ ሙሉ በሙሉ ተሻሽሎ ለአገልግሎት ሲዘጋጅ፣ የአካባቢውን የሰዎችና የሸቀጦች እንቅስቃሴ በማቀላጠፍ፣ የአርሶ አደሩን ምርት በቀላሉና በተሻለ ሁኔታ ወደ ገበያ ለማድረስ እንዲሁም በዞኖቹ መካከል ያለውን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አቶ ግንኙነት ገልጸዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ካራት ዲስትሪክት እየተከናወነ ያለው ይህ የመንገድ ማሻሻያ ሥራ፣ በቀድሞው የነዳጅ እጥረት ሳቢያ ተቋርጦ እንደነበር የዲስትሪክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ተክሉ ንጋቱ ገልጸዋል።

እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ፣ የመንገዱ ደረጃ ማሻሻያ ከዚህ በፊት ከነበረው 6 ሜትር ስፋት ወደ 7.5 ሜትር እንዲሻሻል በማድረግ፣ የመንገዱን ደረጃ ከDC2 ወደ DC4 ለማሳደግ በጥራት እየተሠራ ይገኛል።

የመንገዱ ስፋትና ደረጃ መሻሻሉ የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስፋፋትና የመንገደኞችን እና የሸቀጦችን እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

የመንገዱን የግንባታ ሥራ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ኢንጂነር ተክሉ ጠቁመዋል።

ሥራው በተያዘለት ጊዜ፣ በሚፈለገው ጥራትና ደረጃ እንዲጠናቀቅ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሠራ ሲሆን፣ ለፕሮጀክቱ ስኬታማ አፈጻጸም የአካባቢው ማኅበረሰብ ቀደም ሲል ያደረገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።

የመንገድ ማሻሻያ ሥራ ጋርዱላን፣ አሌንና ጋሞን በተሻለ የመንገድ ትስስር በማገናኘት፣ የአካባቢውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማፋጠን እና የሕዝቡን የተሻለ የመንገድ ተደራሽነት ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

Communication

29/08/2026
የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነውነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ከክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለአቅመ...
28/08/2026

የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው

ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ከክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለአቅመ ደካሞች እያስገነባ የሚገኘው ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።

የቤቶቹ ግንባታ በተያዘለት ዕቅድ መሠረት በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ ሲሆን፣ ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ቤቶቹን በአጭር ጊዜ ለተጠቃሚ ቤተሰቦች ለማስረከብ እየተሰራ ነዉ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ከመንገድ ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን በሰው ተኮር የልማት ተግባራት ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ይገኛል።

ይህ የመኖሪያ ቤት ስራ አቅመ ደካማ ዜጎችን በተሻለ የመኖሪያ ሁኔታ በማጠናከር የኑሮ ሁኔታቸውን በዘላቂነት ለማሻሻል ጉልህ አስተዋፅዖ የሚኖረው መሆኑ ተገልጿል።
© SERA Communication

በጋሞ ዞን የላካ–ውሳሞ–ፃይቴ–ማዞዶይሳ 19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክት የሥራ አፈጻጸም ተገመገመ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ...
27/08/2026

በጋሞ ዞን የላካ–ውሳሞ–ፃይቴ–ማዞዶይሳ 19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክት የሥራ አፈጻጸም ተገመገመ

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ እና የክልሉ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር እድሬ እርኮ የተመራው ቡድን፣ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የላካ–ውሳሞ–ፃይቴ–ማዞዶይሳ 19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክት በመስክ ተገኝቶ የሥራ አፈጻጸሙን ገምግሟል።

ፕሮጀክቱ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ከላካ ከተማ እስከ አሰቃቂው የመሬት መንሸራተት አደጋ የደረሰበት ማዞዶይሳ ቀበሌ የሚዘልቅ ሲሆን፣ ኃላፊዎቹ የግንባታው ሂደትና የተከናወነው ሥራዎችን በቦታው ተገኝተው ገምግሟል።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ፣ ፕሮጀክቱ በክልሉ ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በመሆኑን አሁን ያለውን ምቹ የአየር ሁኔታ በአግባቡ በመጠቀም የሥራ ፍጥነቱን ማሳደግና ተጨማሪ የሥራ ሰዓት በመጠቀም ዝናብ ከመምጣቱ በፊት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲያበቃበ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የክልሉ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር እድሬ እርኮ በበኩላቸው፣ የ19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ በአሁኑ ወቅት የተፈጠረውን ምቹ የአየር ሁኔታ በመጠቀም በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠሉን አስረድተዋል።

የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀክሜ አየለ፣ ከዞንና ከወረዳ መዋቅሮች ጋር በቅርበት በመቀናጀት ፕሮጀክቱ በታቀደው የጊዜ ሰሌዳና በሚፈለገው ጥራት እንዲጠናቀቅ የተጠናከረ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው የፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ እንደሚገኝ የተገመገመ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችም በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራት እንዲጠናቀቁ የሚያስችሉ የሥራ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
© SERA Communication

27/08/2026
በጋሞ ዞን የቆላ ሻራ–ሱሌ–ሳንጋ 48 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረነሐሴ 21/2018 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ፣ ዲታ እና ጨንቻ ወረዳዎችን የሚያገናኘ...
27/08/2026

በጋሞ ዞን የቆላ ሻራ–ሱሌ–ሳንጋ 48 ኪ.ሜ የመንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ፣ ዲታ እና ጨንቻ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የቆላ ሻራ–ሱሌ–ሳንጋ 48 ኪ.ሜ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት በይፋ ተጀምሯል።

ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን የሚገነባ ሲሆን፣ የመንገዱ ግንባታ የአካባቢውን ህዝብ ለብዙ ዓመታት ሲያነሳ የቆየውን የመንገድ ልማት ጥያቄ ለመመለስ ከሚደረጉ ሥራዎች አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ፣ የመንገድ ልማት ለህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ፣ ለምርት ግብይት፣ ለጤና አገልግሎትና ለማህበራዊ ትስስር ወሳኝ መሠረተ ልማት መሆኑን ገልጸዋል።

ይሄ የ48 ኪ.ሜ መንገዱ በአካባቢው የሚገኙ አራት ወረዳዎችን በማገናኘት የህዝቡን የመንገድና የትራንስፖርት ተደራሽነት ለማሻሻል ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም አክለዋል።

መንገዱ የአርሶ አደሩን ምርት ወደ ገበያ በማድረስ፣ የታመሙ ሰዎችን ወደ ጤና ተቋማት ለማድረስ እና የህዝቡን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር ተጨማሪ እድል እንደሚፈጥርም አብራርተዋል።

መንግስት ከምርጫ በኋላ ትላልቅ የልማት ሥራዎችን በማከናወን የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ያለውን ቁርጠኝነት እያረጋገጠ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የክልሉ መንግስትም የ48 ኪ.ሜ መንገድ ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲውል በትኩረት እንደሚሰራ ገልጿል።

የመንገዱ ግንባታ በተፈለገው ደረጃና በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ህብረተሰብና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ወስደው አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ አቶ ተወልደ ጥሪ አቅርበዋል።

የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳሪና የሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀክሜ አየለ በበኩላቸው፣ የክልሉ መንግስት የዞኑን ህዝብ የዘመናት የልማት ጥያቄ ለመመለስ እያከናወነ ላለው ሥራ በዞኑ ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የወረዳዎቹንና የአካባቢውን ህዝብ በማስተባበር ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከባለሥልጣኑ ጋር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር እድሬ እርኮ፣ የቢሮና የባለሥልጣኑ ምክትል ኃላፊዎች፣ የዞንና የወረዳዎች የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
Communication

27/08/2026

፣በድልድይ፣በትራንስፖርት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በከፊል

በጋሞ ዞን ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ -አርባምንጭ አዲስ የትራንስፖርት ስምሪት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ አስጀመረነሐሴ 20/2018 ዲላ በጋሞ ዞን...
26/08/2026

በጋሞ ዞን ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ -አርባምንጭ አዲስ የትራንስፖርት ስምሪት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ አስጀመረ

ነሐሴ 20/2018 ዲላ

በጋሞ ዞን ሰላምበር ከተማን ከአርባምንጭ ከተማ ጋር የሚያገናኝ አዲስ የትራንስፖርት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) አስጀምረዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) ዛሬ በይፋ ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ-አርባምንጭ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን መንገዱ የህዝቦችን መስተጋብር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

መንገዱ ሰላም በር -ዛዳ-ጨንቻ-አርባምንጭ ከተማ ህዝቦችን የሚያስተሳስር ነው ብለው መንገዱ በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነው ብለዋል።

የታሪፍ ሁኔታው በገጠር መንገዶች በተቀመጠ መስፈርት መነሻ ተመን ወጥቶ ከነገ ጀምሮ የትራንስፖርት ሲስተሙ በይፋ መጀመሩን የቢሮው ምከትል ኃላፊና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) ገልፀዋል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ እንደገለፁት 6 አዲስ የስምሪት መስመር መከፈቱና ከዚህ ቀደም ከነበረው የጉዞ ርቅት ሰላምበር -ወላይታ ዶሶ - አርባምንጭ እና ዋጫ-ወላይታ ሶዶ-አርባምንጭ ጉዞን በ106 ኪ.ሜ የቀነሰ መሆኑን ገልፀዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር) የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶክተር) የክልሉ የጋሞና የቁጫ ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

Address

Dilla Front Of Donbosko School
Dilla
P.O.BOX404

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Region Road Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share