03/03/2023
ይካቲት 23/2015 ዓ.ም
በአንዳቤ ወረዳ የ127ኛው የአድዋ የድል በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ
በደቡብ ጎንደር ዞን በአንዳቤ ወረዳ የ127ኛው የአድዋ የድል በዓል "አድዋ የጀግንነት፣ የአንድነትና የነፃነት ቀን!" በሚል መሪቃል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል። በበዓሉም የተለያዩ የወረዳችን ማህበረሰብ፣የአባት አርበኞች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የጸጥታ አካላት እንዲሁም መምህራንና ተማሪዋች የተገኙ ሲሆን በለተያዩ መነባንብ፣ ሽለላ፣ ድራማና በልዩልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል። በውይይቱም የአድዋ በዓል ምንነትና ጠቀሜታው:የንባብ ባህልን ማሳደግና የአፍመፍቻ ቀቋንቋ በዓልን ማክበርና መናገር የሚል ሰነድ በወረዳው ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ያለው አመራ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የቀደሙት አባቶቻችን በመስዋትነት ነፃነቷን ጠብቀው የቆዩንን ከእነክብሯና ነፃነቷ ተጠብቃ ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ የሁሉም ሀላፊነት በመሆኑ ታሪካችንና ቅርሳችን እንዲሁም ባህላዊ ትውፊታችንን በመጠበቅ በ127ኛው የአድዋ የድል በዓል ኢትየጵያዊያኖች ፋሺስት ኢጣሊያንን ድል ሲያደርጉ በአለም ህዝብ ዘንድ የጥቁሮች አፍሪካውያን ድል አድራጊነት የነፃነት ጮራ ያበሰረ ሲሆን ለኢትዮጵያውያን የህብረብሄራዊ አንድነትና በአለም ዘንድ ከፍ ብላ እንድትታይና አዲስ ታሪክ የተፃፈበት ሆኖ አልፏል። በፋሺስት ኢጣሊያን ወረራ ወቅት የሐይማኖት አባቶች ከፈተኛ ድርሻ የወሰዱ ሲሆን የኢትዮጵያዊን አርበኞች፣ ወጣቶችና ሴቶች ለሀገራቸው ሲሉ እንዳሁኑ ዘመናዊ መሳሪያ ሳይኖር በጦር በጎራዴ ትልቅ መስዋት በመክፈል ተፋልመው ሀገራቸውን ነፃ አውጥተዋል።
የኢትዮያን ጠላቶች አሁንም ገና ያልጠፉ ስለሆነ ከአባቶቻችን ታሪክ በመማር ኢትዮጵያን ማስከበርና ታሪካችንና ባህላችን አስጠብቀን ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ )በሚያስችል ሁኔታ 127ኛው የአዋድል የድል በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል
"አድዋ የኢትዮጵያውያን ህብረት የአፍሪካ የነፃነት ጮራ!!!"
የአንዳቤት ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት