Dejen ketema pp youth league

Dejen ketema pp youth league Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dejen ketema pp youth league, Political organisation, dejen, Debre Mark'os.

12/09/2022

ይህ ተአምር ሳታነቡና ሼር ሳታደርጉ አትለፉ

የፃድቃኔዋ ማርያም ተዓምር ስሜ ወለተ ማርያም ይባላል በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ቄራ አባባቢ ነው የተወለድኩት በ12 ዓመቴ በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአራተኛ ክፍል ትምህርቴን እየተከታተልኩ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል/ገና/ ካሳለፍኩኝ በኋላ በማይታወቅ ሁኔታ ድንገት ሁለቱም ዓይኖቼ ማየት ተሳናቸው። ቤተሰቦቼ አዲስ አበባ ውስጥ አሉ ከሚባሉ የዓይን እስፔሻሊስት ሀኪሞች ዘንድ ገንዘባቸውን ጨረሱ እንጂ መፍትሄ አላገኙም ነበር። እኔ ማየት ተስኖኝ ቤተሰቦቼ ዙሪያው ገደል በሆነባቸውና ግራ በተጋባንበት ወቅት
የእመቤታችን አማላጅነት ከጭንቅ ታደገን። ቤተሰቦቼ በተፈጠረብኝ ነገር በጣም ተረብሸው ነበር። እኔም ዓይኔ ጠፍቶ እንደት እንደምሆን ተጨንቄና አዝኜ ነበር። ሌትም ቀንም አለቅስ ነበር። በሀኪም መፍትሄ ያጡት ቤተሰቦቼ የተለያዩ የጠበል ቦታዎች እየወሰዱኝ እጠመቅ ነበር። ለውጥ ግን ማምጣት አልቻልኩም። በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ላይ እያለሁ አባቴ ለታናሽ ወንድሙ ለአጎቴ ስለእኔ ሁኔታ በጭንቅ ሲነግረው አጎቴ ባጋጠመኝ አደጋ አዝኖ ጊዜ ሳያጠፋ የአባቴ እህት ከሆነችው አክስቴ ጋር ሆነው በታህሳስ 21 ወደ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም ይዘውኝ መጡ። በሰው እየተመራሁ ወደ ገዳሙ ምሽት ላይ ደረስን።
ተዓምረ ማርያም ሰምተን ኪዳን አድርሰን ከጨረስን በኋላ ሁሉም ምእመናን እንደሚያደርገው ወደ ጠበል ቦታ በቤተሰቦቼ አማካኝነት ሄጄ ተጠመኩኝ። በወቅቱ ጠበሉ ገና ሰውነቴ ላይ ሲያርፍ ተሰማኝ ሰላምና የመረጋጋት ስሜት መቼም አረሳውም። ተጠምቄ ከወጣሁ በኋላ እምነቱን ዓይኔን ተቀባብቼና ጠበሉን ጠጥቼ ወደ ማረፊያ ቦታችን ሄድን። ትንሽ አረፍ እንዳልኩ ዓይኔን በጣም አሳከከኝ የሆነ ነገር ዓይን ወደ ውጪ ሲገፈው ታወቀኝ። በቃ ዓይ ተጎልጉሎ የወጣ መስሎኝ ተረበሽኩ አለቀስኩ ሁኔታየን ያስተዋለች አክስቴ ጊዜ ሳታጠፋ ወደ ዋሻ ይዛኝ ገባች። ይሁን እንጂ ፋታ ከማግኘት ይልቅ ዓይኔን በጣም ይቆረቁረኝ ጀመረ። የሚቆረቁረኝ ነገር ምን እንደሆነ አክስቴ ዓይኔን ገልጣ ብታይልኝም ምንም ነገር አላገኘችም።
በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ጥቂት ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ ድንገት ዓይኔ ለሶስት ጊዜ ብርት ጭልም እያለ በመጨረሻ ከፊት ለፊቴ የነበረው የእመቤቴን ሥዕል በደንብ ለማየት ቻልኩኝ።
ወዲያው እንባዬ እየፈሰሰ ለአክስቴ ዓይኔ እያየ ነው ብየ ነገርኳት። አክስቴ የምታየው ነገር ከቁጥጥር ውጪ ስለሆነባት እያለቀሰችና እየጮኸች የእመቤታችንን ድንቅ ተአምር በተሰበሰበው ሕዝበ ክርስቲያን አይተውና ሰምተው ወዲያው በእንባ እመቤታችንን ማመስገን ጀመሩ። የጸሎት ቦታው በአንድ ጊዜ በደስታና በለቅሶ ተሞላ፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በአንድ በእለተ ቀኗ ዓይኔን ብርሃን መለሰችልኝ። በጨለማ ሂጄ በብርሃን ተመለስኩኝ። አይቼ የመጣሁትን ቦታ እንዳመሰግን አደረገችኝ እንደገናም ፈጠረችኝ። እንደ ጓደኞቼ ትምህርቴን እንድቀጥል አደረገችኝ
ምስጋና ይድረሳት
የእህታችንን ዓይን ያበራች ለእኛም መልካም የሆነውን ብርሃን ታብራልን እሷን መድኃኒት አድርጎ የሰጠን ልጇ መድኃኔአለም ክብሩ ለዘለዓለም ይሁን። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተቸገርንበትና መልስ ባጣንበት ነገር ሁሉ ከጎናችን ትሆን ዘንድ መልካም ፈቃድ ይሁን አሜን

12/09/2022

አናንያን አዛሪያን ሚሳሄልን ከሚነደው እሳት ያዳንካቸው መላዐኩ ቅዱስ ገብርኤል እኛንም ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ አድነን ሀገራችንንም ከክፉ ነገር ጠብቅልን።
ገብርኤል_ኃያል
ገብርኤል ኃያል መልአከ ሰላም መልአከ ብሥራት
የምታወጣ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከሚነድ እሳት
ፍቅርህ ተስሏል በልባችን
ፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን
አዝ፡--------------------------//
የጽናታቸው ዝናው ሲሰማ
ከዛ ባቢሎን ከሞት ከተማ
ህፃናት ሳሉ በራ እምነታቸው
ቆመህ ተገኘህ መሐከላቸው
አዝ፡--------------------------//
ውኃው ሲዘል ቢያስደነገጥም
በጋኖቹ ውስጥ ቢነዋወጥም
ፀንተው ዘመሩ ልጅና እናቱ
አንተ ስትደርስ ከዚያ ከእሳቱ
አዝ፡--------------------------//
ቂርቆስም ፀና ሞተን ሳይፈራ
አንተ ስላለህ ከነርሱ ጋራ
አትፍሪ አላት ስለምን ትፍራ
አምነው ድል ነሱት ያንን ተራራ
አዝ፡--------------------------//
እኔም አምናለሁ አድነኝ ብዬ
ፈጥነህ አማልደኝ ከቸር ጌታዬ
ክፉውን ዘመን የማልፍበት
ፅናቱን ስጠኝ ድል ልንሳበት አሜን(፫)
የመላዕከ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ምልጃ በረከት ፀሎት ጥበቃው አይለየን!
🤲ኢትዮጵያን ጠብቃት🤲

04/08/2022
19/11/2021
23/10/2021

ህዝቤ ሆይ ሃገር እንድትደፈር፣ ማንነት እንዲጠፋ እያየ የሚፈቅድ #የአባ ኮስትር በላይ ዘር የለም ፡፡
አቶ አብርሃም አያሌው
የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳደሪ

የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር ውስጥ ያላችሁ ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲዎች እና የፋኖ አደረጃጀቶች በዞናችን ያላችሁ ሁሉም የግል እና የመንግስት የጦር መሳሪያ ያላችሁ እና በህዝባዊ አደረጃጀት ስልጠና የወሰዳችሁ በሙሉ ነገ ጀምሮ ሁሉም ደሴ ላይ ይክተት! ግንባር ላይ ለጀግናዊ ሰራዊታችን ደጀን በመሆን በየ አደረጃጀታችሁ ህዝባችንን ከጭቆና ቀንበር ለማላቀቅ ተጋድሏችንን እንድናደርግ ሁሉም የዞኑ ነዋሪዎች የክተት ጥሪ አስተላልፏል፡፡

አሸባሪው ትህነግና ኦነግ ሸኔ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በማበር ኢትዮጵያን ለማፍረስ፣ አማራን ለማጥፋት ለሩብ ክፍለ ዘመናት የአሴረውን በአማራ ህዝብ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው እኩይ ተግባር እየፈጸሙ ነው፡፡

እነዚህ አሸባሪዎች በአጭር ጊዜ ካልተደመሰሱ ወይም መቀበራቸው ካልተረጋገጠ የአማራ ህልውና የኢትዮጵያ ሉአላዊነት መቸም ቢሆን ሊያረጋግጥ አይችልም፡፡
ስለሆነም ይህንን ጥምር የአሸባሪ ቡድን እንደ ቀደምት አባቶቻችን አንድ ሆነን በአጭር ቀን በመደምሰስ ህልውናችንን ልናረጋግጥ፤ ጠላትን ግብአተ መሬት በማስገባት የአባቶቻችንን ታሪክ ዛሬም እንደ ትናንቱ ልንደግም ግድ ብሏል፡፡

በመሆኑም የምስራቅ ጎጃም ህዝብ በአሸባሪው ትህነግና ኦነግ ሸኔ ትብብር ህዝባችንን በወሎ በጎንደር በዋግ የሚደርሰውን የግፍ ግፍ በመረዳትና በማወቅ የግልና የመንግስት የጦር መሳሪያ ያለህ መሳሪያህን በመያዝ፣ ጦር መሳሪያ የሌለህ ለሰራዊቱ ስንቅና ውሃ በማቀበል፣ የተጎዱትን በማግለልና ሌሎች የደጀንነት ስራዎቸን በመስራት እንደ አባቶቻችን አባኮስትር በላይ ታሪክ የምትሰራ በመሆኑ የዞኑ ነዋሪዎች ከጥቅምት 13/2014 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ወሎ እንድትከት ጥሪ ቀርቦልሃል፡፡

ይህንን ክፉ ቀን በተባበረ ክንዳችን እናልፈዋለን!!!

የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ህዝብ ተነስ ጠላትን ደምስስ ድሮም ያባትህ ነውና ባንዳን መቅበር!

29/09/2021
29/09/2021

Address

Dejen
Debre Mark'os

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dejen ketema pp youth league posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share