19/05/2026
የደ/ብርሀን ከተማ ገቢዎች መምሪያ ከ 2 ቢሊዬን ብር በላይ ወይም የእዱን 71.46 %ሰብሰቧል።
በቀን 11/09/2018 ዓ.ም እንደ መምሪያ የገቢ እቅድ አፈፃፀም የክልል ገቢዋች ቢሮ የድጋፍ ቡድን ፤ የመምሪያ ማኔጅመንት ፤የከፍለ ከተማ ሀላፊ እና የገቢ አሰባሰብ የሰራ ሂደት አስተባባሪዎች በተገኙበት ተገመገመ።
የመምሪያው እቅድ ክትትል የስራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ገዛህኝ ነገሰ አሰከ 10/09/2018 ከክፍለ ከተማ አስከ መምሪያ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር በእጥርት እና ጥንካሬ ሪፖርት ቀረቦ ሰፊ ግምገማ ተደርጎል።
የክልል ገቢዎች ቢሮ የድጋፍ ቡድን ከሪፖርቱ በመነሳት በቀሪ ወራት የበጀት ዓመት የገቢ ዕቅድን ሊያሳኩ የሚችሉ ተግባራትን ቆጥሮ መስጠት፣ ትኩረት ሚደረግባቸውን ተግባራት ከመምሪያሪያ እስከ ክፍለ-ከተማ ለይቶ መስራት እና ተግባራትን በስራ ክፍፍል እና በቅንጅት መምራት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
ዳግም ውሳኔ ያልተወሰነላቸውን መወሰን እና የተወሰነላቸውን ግብር ከፋዮች በማስከፈል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች ወርሃዊ ሪፖርት እንዲያደርጉ በቂ ክትትል ማድረግ እና ጠንካራ የደረሰኝ ክትትል ስራ በመስራት ችግር ያለባቸውን 50ሺ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በመቅጣት ለግብር ህጉ ተገዥ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግርዎል፡፡
ውዝፍ ግብር ያለባቸውን ግብር ከፋዮች መረጃ በማጥራት ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ ድርጅት በማሸግ፣ አካውንት በማገድ፣ ሃብት ንብረት በመያዝ ተቆራርጦ ገቢውን መሰብሰብ በቀሪ ወራት የሚጠበቅ እንደሆነ እና
ግብራቸውን ያልከፈሉ የንግድ ትርፍ እና ኪራይ ገቢ ፣ ቅድም ግብር ወይም 25 በመቶ ያልከፈሉ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮችን እና አማራጭ አነስተኛ ግብር ወይም 2.5 በመቶ መክፈል የሚገባቸውን ግብር ከፋዮች ተከታትሎ ማስከፈል እንደሚገባ የስራ አቅጣጫ ተሰቷል።የመምሪያው ም/ሀላፊ አቶ ወንደሰን ተገኝ የክልሉ የድጋፍ ቡድን የተሰጡ አሰተያየቶችን በመቀበል እና ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸውን የገቢ ኮዶችን በመለየት ትኩረት በሰጠት መሰራት ይገባል ብለዎል።
የመምሪያው ሀላፊ አቶ አበባየሁ ምገሰ ሲያጠቃልሉ ያልተሰበሰቡ የገቢ አርዓሰቶች እና ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸውን ተግባራት ከሂደት እና ምክንያት ከመቁጠር በመውጣት በቀሪ ወራት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ እቅዱን ለማሳካት መስራት እንደሚገባ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዎል።