11/06/2026
በኤፍራታና ግድም ወረዳ የ6 ኪ.ሜ የመንገድ ጥገና ስራ 70 በመቶ መጠናቀቁ ተገለፀ
ኤፌሶን፦ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም (ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን)
በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ከሰላማ በር እስከ ሌመን መገንጠያ የተዘረጋው 6 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት በ10.6 ሚሊዮን ብር ወጪ በመከናወን ላይ ሲሆን 70 በመቶ የአፈጻጸም ደረጃ መድረሱ ተገለጸ።
ቀደም ሲል በነዳጅ እጥረት ምክንያት የተጓተተው ፕሮጀክት አሁን በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን፣ በጎርፍ የተጎዱ የመንገድ ክፍሎችን መጠገንና የጋቢዮን ሥራዎችን ያካትታል።
የኤፍራታና ግድም ወረዳ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ኃላፊ አቶ ንጉሴ ኃይሌ እንደገለጹት፣ ቀሪው ሥራ እስከ ሰኔ 15 ድረስ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ኃላፊው በተጨማሪም ማህበረሰቡ የተገነቡ መንገዶችን በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅና በመንከባከብ ዘላቂ ጥቅም እና ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።