Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department

Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department, Government Organization, North Shewa Debre Birhan, Debre Birhan.

በኤፍራታና ግድም ወረዳ የ6 ኪ.ሜ የመንገድ ጥገና ስራ 70 በመቶ መጠናቀቁ ተገለፀኤፌሶን፦ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም (ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን)በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ከሰላማ በር እስ...
11/06/2026

በኤፍራታና ግድም ወረዳ የ6 ኪ.ሜ የመንገድ ጥገና ስራ 70 በመቶ መጠናቀቁ ተገለፀ

ኤፌሶን፦ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም (ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን)

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ከሰላማ በር እስከ ሌመን መገንጠያ የተዘረጋው 6 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት በ10.6 ሚሊዮን ብር ወጪ በመከናወን ላይ ሲሆን 70 በመቶ የአፈጻጸም ደረጃ መድረሱ ተገለጸ።

ቀደም ሲል በነዳጅ እጥረት ምክንያት የተጓተተው ፕሮጀክት አሁን በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን፣ በጎርፍ የተጎዱ የመንገድ ክፍሎችን መጠገንና የጋቢዮን ሥራዎችን ያካትታል።

የኤፍራታና ግድም ወረዳ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ኃላፊ አቶ ንጉሴ ኃይሌ እንደገለጹት፣ ቀሪው ሥራ እስከ ሰኔ 15 ድረስ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ኃላፊው በተጨማሪም ማህበረሰቡ የተገነቡ መንገዶችን በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅና በመንከባከብ ዘላቂ ጥቅም እና ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

መምሪያው የ11 ወራት እቅድ አፈፃፀም  ከወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በዙም ግምገማ አካሔደ።ደብረ ብርሃን፦ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን መን...
10/06/2026

መምሪያው የ11 ወራት እቅድ አፈፃፀም ከወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በዙም ግምገማ አካሔደ።

ደብረ ብርሃን፦ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ዝርዝር ዝርዝር ግምገማ አካሂዷል።

በግምገማው በዕቅድ ከተያዙት ሥራዎች ውስጥ በጥንካሬ የተከናወኑ ተግባራትና በእጥረት የታዩ ችግሮች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸው የቀጣይ መፍትሔ አቅጣጫ ተቀሞጧል።

በውይይቱ በመንገድ ዘርፍ እና በትራንስፖርት ዘርፍ በቀሪ ጊዜ በልዩ ትኩረት ተይዘው የሚሰሩ ተግባራት ተለይተው የጠበቀ ተልዕኮ ተሰጥቷል።

የግምገማ መድረኩን የዞኑ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ መርተውታል።

በግምገማው የመምሪያው ማኔጅመንት አባላት ፣ የወረዳና ከተማ የመንገድ ትራንስፖርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና የወረዳ ትራፊክ ፖሊሶች ተገኝተዋል።

ከወንጭት እስከ ጀማ ያለው የፌደራል መንገድ  ጥገና ስራ መጀመሩ ተገለፀበሰሜን ሸዋ ዞን በመርሐቤቴ ወረዳ ከወንጭት እስከ ጀማ ያለው የፌደራል መንገድ  በፌደራል መንገዶች አስተዳደር(ERA) ...
03/06/2026

ከወንጭት እስከ ጀማ ያለው የፌደራል መንገድ ጥገና ስራ መጀመሩ ተገለፀ

በሰሜን ሸዋ ዞን በመርሐቤቴ ወረዳ ከወንጭት እስከ ጀማ ያለው የፌደራል መንገድ በፌደራል መንገዶች አስተዳደር(ERA) ጥገና ስራ ተጀምሯል።

የመንገድ ጥገና ፎርማን አቶ ደመቀ ሎኃ እንደገለፁት ከጃማ ደጎሎ እስከ ወንጭት ጥገናውን እንዳጠናቁ አንስተው፤ በወረዳው ከወንጭት እስከ ጀማ ያለውን የፌደራል መንገድ ጥገና ስራ በማከናወን ላይ ነን ያሉ ሲሆን እስከ ሰኔ 15 ድረስ የመንገድ ጥገናውን ለማጠናቀቅ አቅደው እየሰሩ እንደሆነና በጣም የተጎዱ መንገዶችን እየጠገንን እንገኛለን ሲሉ አንስተዋል።

የመርሐቤቴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታው በላይግዛው እንደገለፁት ከጃማ እስከ ወንጭት ያለው መንገድ መጠናቀቁን አንስተው፤ አሁን ላይ ከወንጭት እስከ ጀማ ያለው የፌዴራል መንገድ ጥገና እየተከናወነ እንደሆነና አሁን ላይ በመርሐቤቴ ወረዳ በአገሪት ቁምአምባ ቀበሌ ልዩ ስሙ መጋያጃ እየተባለ በሚጠራው ቦታ የጥገና ስራ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

የመንገድ ጥገና ስራውን የመርሐቤቴ ወረዳ አስተዳደር አመራሮች በቦታው በመገኘት ምልከታ አድርገዋል።

በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል!*******በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ ጠንገጎ ቀበሌ የተገነባው የአጥዋ ወን...
27/05/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል!
*******
በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ ጠንገጎ ቀበሌ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ 22 ሜትር ኮንክሪት ድልድይ ሥራ ተጠናቆ በይፋ ተመርቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

ፕሮጀክቱ በክልሉ መንግስት በጀት ድጋፍ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎ የተገነባ ሲሆን፣ የአካባቢውን ቀበሌዎች ከማስተሳሰር ባሻገር ከሁለት በላይ አጎራባች ወረዳዎችን በማገናኘት ለህዝቡ የትራንስፖርት፣ የንግድ እና የማህበራዊ ትስስር አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል።

ድልድዩ በተለይ በክረምት ወቅት በወንዙ ምክንያት ይፈጠሩ የነበሩ የመንቀሳቀስ ችግሮችን በመቅረፍ የህዝቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዲቀላጠፍ ያግዛል ተብሏል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዞኑና የወረዳው አመራሮች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተው የድልድዩን ጠቀሜታ በማጉላት የርክክብ ሥነ-ሥርዓት አካሂደዋል። ድጋፍና ትብብር ላደረጉ የዞንና ወረዳ አስተዳደር አካላት፣ ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት ምስጋና ይገባል።

ከ4ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባዉ ተጠልጣይ ድልድይ ተመረቀ።በአብክመ ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ በወደራ ቀበሌ ድርግሚት ጎጥ የተገነባዉ  ተጠልጣይ ድልድይ  የወረዳዉ አመራርና...
20/05/2026

ከ4ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባዉ ተጠልጣይ ድልድይ ተመረቀ።

በአብክመ ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ በወደራ ቀበሌ ድርግሚት ጎጥ የተገነባዉ ተጠልጣይ ድልድይ የወረዳዉ አመራርና መንግስት ሰራተኞች በተገኙበት ተመርቋል።

በወረዳዊዉ ዋና አስተዳዳሪ የተመራ ልዑክ ቡድን ሪቫን በመቁረጥ የተጠልጣይ ድልድዩ መገባቱን ደስታቸዉን ገልፀዋል።

ተጠልጣይ ድልድዩ በመገንባቱ የአካባቢዉ ማህበረሰብ ከዘርፈ ብዙ ችግር መላቀቅ ችለዋል ።

ተጠቃሚዉ ማህበረሰብ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብራቸዉን ወደ ተሻለ ደረጃ ያሸጋገራቸዉ በመሆኑ ደስታቸዉን ገልፀዋል።

የሞጃና ወደራ ወረዳ አመራርና መንግስት ሰራቸኞች እንዲሁም ተጠቃሚ ማህበረሰቦች በተገኙበት የምረቃ ስነስርዓት ተከናዉኗል።

የሞጃና ወደራ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

በሰ/ሸዋ ዞን በአላላ ቀበሌ የአባይ ውሃ አነስተኛ ድልድይ በደማቅ ስነ-ስርዓት ተመረቀ******በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ በአላላ ቀበሌ የተገነባው የአባይ ውሃ አነስ...
19/05/2026

በሰ/ሸዋ ዞን በአላላ ቀበሌ የአባይ ውሃ አነስተኛ ድልድይ በደማቅ ስነ-ስርዓት ተመረቀ
******
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ በአላላ ቀበሌ የተገነባው የአባይ ውሃ አነስተኛ ድልድይ በዛሬው ዕለት በአስደሳች ሁኔታ ተመርቋል።

ድልድዩ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ (FSRP) ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ በክልሉ ግብርና ቢሮ እና በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተገነባ ሲሆን፣ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተወስዶበታል።

ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል፣ የግብርና ስርዓትን ለመጠናከር እና የአካባቢ ማህበረሰቦችን ከድርቅና ከአየር ለውጥ አደጋ ለመጠበቅ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

አቶ አበራ እንኳን አደረሳችሁ ካሉ በኋላ የተገነባው ድልድይ አላላን ፣ይምልዎን ፣መንተኬ ሸረፋን ና ከሰንበቴ አካባቢዎችን በማገናኘት ለነዋሪዎች የመጓጓዣ እና የንግድ እንቅስቃሴ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

አቶ ታደሰ እንደገለፁት ድልድዩ ቀበሌዎችን በማገናኘት ብቻ ሳይሆን ከአጎራባች ወረዳዎች ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ለአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የቀጥታ ጥቅም ያመጣል ብሏል። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ አንድ ዓመት ከስድስት ወር የፈጀ መሆኑን አያይዘው ገልፀዋል።

በምረቃት ስነ-ስርዓቱ የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ችሮታው አስፋው፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ አበበ፣ የ103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮረኔል ሰለሞን ፀጋዬ፣ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አበራ መኮንን፣ ተጋባዥ እንግዶች እና ሌሎች አመራሮች ከማህበረሰቡ ጋር ተገኝተዋል።

ተሳታፊዎች በንግግራቸው ድልድዩ ለረጅም ጊዜ የነበረ የማህበረሰቡ ጥያቄ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዛሬ እውን መሆኑ ለአካባቢው ህዝብ ትልቅ እፎይታ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ለፕሮጀክቱ ስኬታማ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላት የምስጋናና የእውቅና ሽልማት በመስጠት ስነ-ስርዓቱ ተጠናቋል።

በሰ/ሸዋ ዞን በ30ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በክልሉ የበጀት ድጋፍ እየተገነባ ያለውን የአጥዋ ድልድይ ግንባታ ጉብኝት ተካሄደ በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ በ30 ሚሊዮን ብር እየተገነባ...
19/05/2026

በሰ/ሸዋ ዞን በ30ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በክልሉ የበጀት ድጋፍ እየተገነባ ያለውን የአጥዋ ድልድይ ግንባታ ጉብኝት ተካሄደ

በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ በ30 ሚሊዮን ብር እየተገነባ ያለውን የአጥዋ ድልድይ ግንባታ በዞን ደጋፊ አመራር፣በወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ፣በወረዳው ቋሚ ኮሚቴና ጠቅላላ አመራር ተጎብኝቷል።

አጠቃላይ የግንባታ ሥራው በአግባቡ እየተሠራ ሲሆን በቅርብ ቀን አጠቃላይ ሥራው የሚጠናቀቅ ይሆናል።

በመንዝ ማማ ወረዳ አንገዋ ቀበሌ 4.5ኪሎ ሜትር መንገድ ተሰርቶ ተመረቀ። በወረዳው መንግስትና በቀበሌው ማህበረሰብ ተሳትፎ ከአንገዋ ዋና መስመር ጭንጫ ግድብ የተሰራው 4.5ኪሎሜትር መንገድ ...
17/05/2026

በመንዝ ማማ ወረዳ አንገዋ ቀበሌ 4.5ኪሎ ሜትር መንገድ ተሰርቶ ተመረቀ።
በወረዳው መንግስትና በቀበሌው ማህበረሰብ ተሳትፎ ከአንገዋ ዋና መስመር ጭንጫ ግድብ የተሰራው 4.5ኪሎሜትር መንገድ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።መንገዱ ለሁሉም ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በተለይም የመስኖ ተጠቃሚ አርሶ አደሮችን ልማት እንደሚያፋጥን የወረዳው መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሽመልስ ፅጌ አስረድተዋል።በስራው ከፍተኛ አበርክቶ ለነበራቸው አካላት እውቅና ተፈጥሯል።
የቀበሌው አርሶ አደሮች በበኩላቸው መንግስት ለልማቱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ አመስግነዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ሀብት አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሀላፊና የቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አበራ ፈንታሁን፣የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ፣የሰሜን ሸዋ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ተማለደ በላይሁን፣የመንዝ ማማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መርሻ ሀይሉ፣ የሞላሌ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ አብረሃም አድምቄ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ሀላፊ አቶ ደመቀ ማሙሻን ጨምሮ የሚመለከታቸው የወረዳና የከተማ አስተዳደሩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የአዋሽ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃራ ገበያን የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሥራ አስጀመሩ።392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መንገድ ፕሮጀክቱ 2007 ዓ.ም ተጀምሮ እስከ 2012...
17/05/2026

የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የአዋሽ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃራ ገበያን የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሥራ አስጀመሩ።

392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መንገድ ፕሮጀክቱ 2007 ዓ.ም ተጀምሮ እስከ 2012 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። ኾኖም በሰሜኑ ጦርነት በደረሰበት ውድመት እና ዘረፋ ምክንያት ለመገባደድ ተቃርቦ የነበረው ፕሮጀክት ተስተጓጉሎ ቆይቷል።

ይህ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው ፕሮጀክት መጠናቀቅ የንግድ ሥርዓቱን በማሳለጥ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። የባቡር መስመሩ በኤሌክትሪክ ኀይል የሚሠራ ነው።

የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

#ምንጭ//kombolcha city communications

የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ታሪካዊ የመጀመሪያ የሙከራ በረራውን የአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ በተገኙበት በስኬት አስተናገደ።‎************‎የደብረ ማርቆስ ...
16/05/2026

የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ታሪካዊ የመጀመሪያ የሙከራ በረራውን የአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ በተገኙበት በስኬት አስተናገደ።
‎************
‎የደብረ ማርቆስ ከተማና የአካባቢው ማህበረሰብ ለብዙ አመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያውን የሙከራ በረራ በዛሬው ዕለት በስኬት አስተናግዷል።

‎ይህ ታሪካዊ ክስተት ለአካባቢው የኢኮኖሚ፣ የንግድና የቱሪዝም እንቅስቃሴ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ታላቅ ስኬት መሆኑ ተገልጿል።

‎​በአውሮፕላን ማረፊያው የመጀመሪያው የመንገደኞች አውሮፕላን ሲያርፍ የከተማው ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በመገኘትት ደስታቸውን ገልጸዋል።
‎​
‎​የከተማው አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት የአውሮፕላን ማረፊያው ስራ መጀመር የከተማዋን የትራንስፖርት ተደራሽነት ከማሻሻሉም በላይ የኢንቨስትመንት ፍሰቱን በእጅጉ ያፋጥነዋል ብለዋል።

‎​የአውሮፕላን ማረፊያው የደብረ ማርቆስና አካባቢውን ህዝብ የልማት ጥያቄ የመለሰና ደብረ ማርቆስን ከሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች ጋር በቅርብ የሚያስተሳስር የልማት ምሰሶ ነው ሲሉ የአስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ገልጸዋል።

‎​አውሮፕላን ማረፊያው በይፋ ስራ መጀመሩ
‎​ለኢንቨስትመንት መስፋፋት፣ለቱሪዝም መነቃቃት እና ለንግድ ትስስር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
‎​
‎​የከተማዋ ነዋሪዎች በአውሮፕላን ማረፊያው መከፈት የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ የገለጹ ሲሆን፣ ይህ የልማት ውጤት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለወጣቶች አዲስ የስራ እድል እንደሚፈጥርም ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።

‎የመጀመሪያ በረራ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ በቀጣይ መደበኛ በረራዎች የሚቀጥሉ ሲሆን ይህም የከተማዋን ሁለንተናዊ የዲጂታልና የማህበራዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።

በዕለቱም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ፣ የኢፌድሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አቶ መላኩ አለበል፣ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ፣ የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃን ጨምሮ የፌደራል፣ የክልል፣የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደርና የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

Address

North Shewa Debre Birhan
Debre Birhan
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share