Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department

Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department, Government Organization, North Shewa Debre Birhan, Debre Birhan.

እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲሱ አመት አደረሣችሁ አደረሠን!!የሰ/ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀሥቲክሥ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ አዲሱን አመት አስመልክተዉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕ...
11/09/2026

እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲሱ አመት አደረሣችሁ አደረሠን!!
የሰ/ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀሥቲክሥ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ አዲሱን አመት አስመልክተዉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በዓሉ የደሥታ፣የመጠየቅና የአብሮነት ጊዜ እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ የህዝብና የትራፊክ እንቅሥቃሴዎች የሚበዙበት በመሆኑ መላ የዞናችን የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች በበዓል ወቅት የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት የትራፊክ ህጎችን በማክበር እና አልኮል ጠጥቶ ከማሽከርከር በመቆጠብ ፣ ለእግረኞች ቅድሚያ በመስጠትና ፍጥነትን በመቀነስ እንዲያሽከረክሩና ሁላችንም ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል።

የትራንስፖርት ተቆጣጣሪ ትራፊክ ፖሊሶች እና የትራንስፖርት ባለሙያዎች ከወትሮው በላቀ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ደህንነት እንዲጠበቅ እና መጉላላት ሳይኖር ትክክለኛ አገልግሎት እንዲሰጥ ሙያዊና የዜግነት ህዝባዊ አደራ መወጣት ይገባናል።

በመጨረሻም ለመላዉ የዞናችን ህዝብ፣ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች፣ትራፊክ ፓሊሶች፣አሽከርካሪዎች፣አጋርና ባለድርሻ አካላት አዲሱ ዓመት የሰላም ፣የጤና ፣ የፍቅርና ያቀድነው ሁሉ የሚሳካበት አመት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ! መልካም ምኞታቸዉን ተመኝተዋል።

መልካም አዲሥ ዓመት!!
ደጀኔ በቀለ
የሰ/ሸዋ ዞን መንገድ፣ትራንሥፖርትና ሎጀሥቲክሥ መምሪያ ኃላፊ

በበዓል ወቅት ከአሰራር ዉጭ በሚሰሩ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋልበበዓል ወቅት ሊያጋጥም የሚችለውን የትራንስፖርት መጨናነቅና ሕገወጥ እንቅስቃሴ ለመከላከል አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅ...
09/09/2026

በበዓል ወቅት ከአሰራር ዉጭ በሚሰሩ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል
በበዓል ወቅት ሊያጋጥም የሚችለውን የትራንስፖርት መጨናነቅና ሕገወጥ እንቅስቃሴ ለመከላከል አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅት ማደረጉን የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ አስታወቀ።

​የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ እንደገለጹት የበዓላትን አጋጣሚ በመጠቀም ከመናኸሪያ ውጪ መጫን፣ ትርፍ ተሳፋሪ መጫን፣ ከታሪፍ በላይ ማስከፈልና ተጓዦችን ማዋከብ የመሳሰሉ ሕገወጥ ተግባራት ይስተዋላሉ ብለዋል።

​ይህንን ችግር ለማስቀረትም ከሚመለከታቸው የትራንስፖርት ዘርፍ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ መመሪያ ተሰጥቷል።

​በተለይም አሽከርካሪዎች ከመናኸሪያ ከተነሱ በኋላ በመንገድ ላይ ተሳፋሪዎችን በመጫን ተጨማሪ ክፍያ የሚጠይቁበትን አሰራር በመኖሩ በሁሉም የትራፊክ መስመሮች ላይ ቁጥጥር ይደረጋል ነዉ ያሉት።

​ተሳፋሪዎች መብታቸውን ማስከበር እንዳለባቸው የጠቆሙት አቶ ደጀኔ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲያጋጥማቸው ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ ተቋሙን ማገዝ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

​የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተቀላጠፈ እንዲሆንና ከበዓል በኋላ ተሳፋሪዎች እንዳይንገላቱ ለማድረግም ከፌደራል ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመመካከር ተጨማሪ የሕዝብ ትራንስፖርት አዉቶብስ ለማቅረብ እቅድ ተይዟል ነዉ ያሉት።

​በሌላ በኩል የደብረ ብርሃን ዞናል መናኸሪያ አስተዳደር ቡድን አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ አለሙ ማንኛውም ዓይነት ሕገወጥ አሰራር እንዳይከሰት ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

የክፍያ ሂደቱ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት የሚፈጸም በመሆኑ ተሳፋሪዎች ምንም ዓይነት ሥጋት እንደማያጋጥማቸዉ ጠቁመዋል።

ተሳፋሪዎች የሚያጋጥማቸውን ማንኛውንም ችግር በነፃ የስልክ መስመር 9325 ደውለው መጠቆም እንደሚችሉ የሰሜን ሸዋ ዞን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ገልጿል።

07/09/2026
የትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ቀን፣በእንሳሮ ወረዳ በድምቀት ተከበረ።በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ፣"ሕይወትን እናድን፤ሕግን እናክብር!" በሚል መሪ ሐሳብ  የትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ዛሬ በድም...
06/09/2026

የትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ቀን፣በእንሳሮ ወረዳ በድምቀት ተከበረ።
በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ፣
"ሕይወትን እናድን፤ሕግን እናክብር!" በሚል መሪ ሐሳብ የትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ዛሬ በድምቀት ተከብሯል። የወረዳው መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀሥቲክሥ ጽ/ቤት፣ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት እና ፖሊሥ ጽ/ቤት በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መርሃ ግብር፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች፣ ባለንብረቶችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

መርሃ ግብሩ በደማቅ ሰልፍና በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ በሰልፍ ሥነ-ሥርዓቱ የእንሳሮ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ታደሰ አሻግር ዕለቱን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተዘጋጀው የፓናል ውይይት፣የእንሳሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊና የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አቶ ብዙአየሁ ጸጋው፣ እንዲሁም የወረዳው መንገድና ትራንስፖርትና ሎጀሥቲክሥ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሱ ምሳየ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

በመድረኩም፣በትራፊክ ደህንነት፣ በመንገድ ላይ የሚፈጸሙ ጥፋቶችን በመቀነስና የመንገድ ተጠቃሚዎች ሕግን አክብረው እንዲንቀሳቀሱ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ማብራሪያና ውይይት ተካሂዷል። የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ፣ የዞኑ ፖሊስ ወንጀል መከላከል ምክትል መምሪያ አዛዥ ኮማንደር እምሻው አካለና የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ብዙአየሁ ጸጋው መድረኩን የመሩት ሲሆን በመኪና አደጋ ህይወታቸውን ላጡ የወላጅ ልጆች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ፣ ለተማሪ የትራፊክ ክበብ አባላትም የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እና በሥራቸው ውጤታማና ተመስጋኝ ለሆኑ የትራፊክ ፖሊሶችና ሕግን አክብረው ለሚያሽከረክሩ አርአያ አሽከርካሪዎች የእውቅናና የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ፣ ሁሉም የመንገድ ተጠቃሚዎች፣ አሽከርካሪዎች፣ እግረኞችና የሚመለከታቸው ተቋማት በቅንጅት መሥራትና የትራፊክ ሕግን በአግባቡ ማክበር እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ በክልል ደረጃ 2ኛ ወጣ!! የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘገበው የሥራ አፈጻ...
04/09/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ በክልል ደረጃ 2ኛ ወጣ!!
የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘገበው የሥራ አፈጻጸም በመገምገም በአማራ ክልል ዞኖች መካከል 2ኛ ደረጃ በመውጣት የእውቅናና ሽልማት ተቀበለ።

የአማራ ክልል መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩም በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ዕውቅናና ሽልማት ተበርክቷል።

በዚህም የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ከክልሉ ዞኖች መካከል 2ኛ ደረጃን በመያዝ ተሸላሚ ሆኗል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ ለተገኘው ውጤት ለመምሪያው ሠራተኞች፣ ለአመራሮች፣ ለአጋርና ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

አቶ ደጀኔ በተለይም በየደረጃው የሚገኙ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አመራሮች፣ የመምሪያው ማኔጅመንትና ሠራተኞች፣ የሕዝብ ትራንስፖርት ማኅበራት፣ አጋር ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

የተገኘው 2ኛ ደረጃ በመምሪያው የተመዘገበውን የሥራ አፈጻጸም የሚያሳይ ውጤት መሆኑን በመግለጽ፣ በቀጣይም የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ በትብብር መሥራት እንደሚገባ አመራሩ አመልክቷል።

ለሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ፣ ለሠራተኞቹ፣ ለአጋርና ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ!

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንሥፖርትና ሎጀሥቲክሥ መምሪያ በ108 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል (የትራፊክ ኮምፕሌክስ) ተ...
24/08/2026

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ ትራንሥፖርትና ሎጀሥቲክሥ መምሪያ በ108 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል (የትራፊክ ኮምፕሌክስ) ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

​የክልሉ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጋሻው አወቀ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ በዘርፉ ይስተዋል የነበረውን አሰራር በማዘመን፣ ፈጣን፣ ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው።

​በ8 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ማዕከል፤ በወቅታዊ የገበያ ዋጋ ሲተመን ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ትልቅ አህጉራዊ ይዘት ያለው ፕሮጀክት ነው።

አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በማቀናጀት የንድፈ-ሐሳብና የተግባር ማሰልጠኛዎችን፣ የቴክኖሎጂ የታገዘ የቴክኒክ ምርመራ (ቦሎ)፣ የተሽከርካሪና የአሽከርካሪ ፋይሎችን በአንድ መስኮት ያቀናጀ አሰራር ይዟል።

በግቢውና ከአካባቢው ጋር በተያያዙ ዘመናዊ ካሜራዎችና የኮምፒውተር ሲስተሞች ታግዞ የቁጥጥርና የንድፍ ስራዎችን የሚያፋጥን በመሆኑ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

አገልግሎቱን በማፋጠን የህዝብን እንግልት የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ለዞኑና ለክልሉ ተጨማሪ ገቢ የሚፈጥር የመልካም አስተዳደር ማሳያ ተቋም ነው።

​ኃላፊው አክለውም ፕሮጀክቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የመሬት ዝግጅትና የቅንጅት ስራዎችን በማከናወን ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉት የሰሜን ሸዋ ዞንና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ለተቋሙ ኃላፊ እና ሰራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።

በክልሉ ከ152 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች የሚገኙ ሲሆን፤ ይህ ማዕከል ለሌሎች አካባቢዎችም ሞዴል ሆኖ የሚያገለግል መሆኑ ተመልክቷል።

​የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተቋማት ተቀዳሚ ተግባር የመንገድ ትራፊክ አደጋዎችን በመቀነስ የሰው ሕይወትን ማዳን መሆን እንዳለበት የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ ገልጸዋል።

​ዋና አስተዳዳሪው የዞኑ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል በተመረቀበት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት፣ ማዕከሉ የዘመነ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የትራፊክ አደጋ ከመከሰቱ በፊት የመከላከል ሥራ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ይኖርበታል።

ባለሙያዎችና አመራሮች አገልግሎቱን ይበልጥ በማዘመን የበቁ አሽከርካሪዎችን የማፍራት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

​በሌላ በኩል በአካባቢው የተጓተቱ የፌደራልና የክልል የመንገድ ፕሮጀክቶች አሁንም ለትራፊክ አደጋና ለማህበራዊ ምቾት ማጣት ምክንያት መሆናቸውን አንስተዋል።

አቶ መካሻ በተለይም የጣርማበር - መሐል ሜዳ እንዲሁም የኮኮብ መስክ - አለም ከተማ - ጃማ የመንገድ ፕሮጀክቶች በፍጥነት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

​አስተዳደሩ ለተጀመሩ የመሠረተ ልማት እንቅስቃሴዎችና ለትራንስፖርት ዘርፉ ማሻሻያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

​መምሪያው በበጀት ዓመቱ የመንገድ መሰረተ ልማት፣ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ እና የተቋም ማሻሻያ ስራዎችን በስኬት ማከናወን የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ ገልጸዋል።

​ተቋሙ በመንገድ ዘርፍ ከ357 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከ932 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ጥገና እንዲሁም 72 ኪሎ ሜትር አዲስ መንገድ የመስራት ጥረት አድርጓል።

በትራንስፖርት ዘርፉም ከ48 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ተችሏል።

​በዞኑ ባሉ 15 ወረደዎች የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ማስጀመርን ጨምሮ ህገ-ወጥ አሰራርን ለመቆጣጠር በተደረገ እንቅስቃሴ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ እርምጃ መወሰዱን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ከ108 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የጊቢ ማሻሻያ፣ የቴክኖሎጂ አሰራር (ኦንላይን) ዝርጋታ እና ለሰራተኞች የአገልግሎት አውቶቡስ ማቅረብ መቻሉን ጠቅሰዋል።

​የመንገድ ልማት፡ ከ932 ኪ.ሜ በላይ ጥገና እና 72 ኪ.ሜ አዲስ መንገድ መገንባቱ ፣ ከ48 ሚሊዮን በላይ ተገልጋዮች አገልግሎት ፣ በ15 ወረደዎች በሚገኙ መናኸሪያዎች ዲጂታል ቲኬት መጀመሩ ቁልፍ ስኬት መሆኑን በመምሪያ ኃላፊው አቶ ደጀኔ በቀለ የተገለፀ ሲሆን ለሁሉም ሥራዎች አሥተዋፅኦ ለነበራቸው የክልልና የዞን አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም ለመምሪያው ማኔጅመንትና ጠቅላላ ሠራተኞች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ ምሥጋና አቅርበዋል::

በመርሐ-ግብሩ ላይ የክልል ፣ የሰ/ሸዋ ዞን ና የደብረ ብርሃን ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሚመለከታቸው አጋርና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን የመሰረተ ልማት ክላስተር ተቋማት የሃምሌ ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄዱ።ክላስተሩን የሚያስተባብሩት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እንደተናገሩት ...
17/08/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን የመሰረተ ልማት ክላስተር ተቋማት የሃምሌ ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄዱ።
ክላስተሩን የሚያስተባብሩት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እንደተናገሩት በዞኑ ተግባራት በታቀደላቸው አግባብ እንዲተገበሩና ውጤት እንዲመዘገብ ተቋማትን በክላስተር በማደራጀት መገምገምና መደገፍ ተገቢ ሆኖ መገኘቱን ተናግረዋል።
በዛሬው እለትም የሁሉም ተቋማት መሰረት የሆኑት የመሰረተ ልማት ክላስተር ተቋማት የበጀት አመቱን የአንድ ወር የስራ አፈፃፀም በመገምገም ለቀጣይ ወራት የተሳካ አፈፃፀም አቅጣጫዎችን እናመላክታለን ብለዋል።
የመሰረት ልማት ክላስተር ተቋማት ዘመናዊ ግብርና እና አምራች ኢንዱስትሪ እንዲሳለጡ፣ ከግንባታ ጋር ተያይዞም ከመዋቅራዊ ጥናቱ ጋር የተዛመዱ የመሰረት ልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ እንዲሁም ህብረተሰብን በማሳተፍ ለልማቱ እርብርብ አድርጎ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ ከፍተኛውን ስራ የሚሰሩ መሆኑን አመላክተዋል።

በመጀመሪያው ወር ዋናው ተግባር በቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሃብት ማፈላለግና በጀት የማፅደቅ ስራዎች መሰራት ዋናው ተግባር መሆኑንም አመላክተው ተቋማት ለዚህ ተግባር ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚገባቸውና ለዋናው ተግባር መደላደል መፍጠር እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የዞኑ መንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ ባቀረቡት ወርሃዊ የስራ አፈፃፀም እንደተናገሩት የትራንስፖርት አገልግሎትን ፍትሃዊ እና የተቀናጀ እንዲሆን ብሎም የተሽከርካሪ እና የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ በጥራት በመስጠት የሚከሰትን የትራፊክ አደጋ መከላከል እንዲቻል የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

የመንገድ ትራፊክ ደህንነትን ለማረጋገጥ አደጋዎች እንዲቀንሱ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ በሰፊው በመስራት ህገወጥ አሰራሮችን መቀነስ እና ሌሎች በመምሪያው የተከናወኑ ተግባራትን አቅርበዋል።

በተያዘው በጀት አመት መጀመሪያ በዞኑ የተጀመሩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታን ለማጠናቀቅ በሬማና ቡልጋ እንዲሁም በልበሊትና ወቀሎ የሚገኙ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታዎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የተናገሩት የዞኑ ውሃ መምሪያ ሃላፊው አቶ ችሮታው ሹመት ናቸው።

በጣርማበር ወረዳ አጋምበር እና በሌሎች አካባቢዎች ጭምር የተጀመረው የንፁህ መጠጥ ውሃ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

በኢነርጂ በኩል ጭስ አልባ ምድጃ የሶላር ተጠቃሚዎችን እንዲሁም የባዮጋዝ አጠቃቀምን ለማጎልበት እንዲሁም አነስተኛ የውሃ ተቋማትን ለመገንባት ሃብትና በጀትን ለማፈላለግ እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ሌሎች የተከናወነው ተግባራትን አቅርበዋል።

የዞኑ ኮንስትራክሽን ተጠሪ ፅ/ቤት ሃላፊ ወይዘሪት ነፃነት ንጉሴ ተቆሙ በአዲስ ተዋቅሮ ወደ ተግባር ከገባ 6 ወራት ያስቆጠረ መሆኑን ጠቅሰው እስከታች ድረስ በሰው ሃይል በማደራጀት ፈጥኖ ወደ ተግባር ለመግባት መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም ተጠሪ ፅ/ቤቱ ፕላን ስምምነት የግንባታ ፈቃድ መስጠት የግንባታ ቁጥጥር የመንግስት ፕሮጀክቶችን ቁጥጥርና ክትትል ግጭቶች ወደ ህግ ከመድረሱ በፊት በህብረተሰቡ እንዲፈቱ ማድረግ የአቅም ግንባታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁም የወጪና የግንባታ ብክነትን መቀነስ እና ሌሎች የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበዋል።

በመድረኩ የየተቋማቱ ቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን በቀረቡ እቅድ አፈፃፀም መነሻነት ውይይት ተካሂዶባቸው ለቀጣይ መልካም አፈፃፀም የሚበጁ አቅጣጫዎች ተመላክቶባቸዋል።

ምክትል አስተዳዳሪው አቶ ተክለየስ በማጠቃለያቸው ተቋማቱ ያቀዱትን ተግባራት በጥብቅ ዲሲፕሊን እየገመገሙ መምራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው በክላስ

በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ። በሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረማርያም ወረዳ መንገድ፣ ትራንስፓርትና ሎጀስቲክስ  ጽህፈት ቤት ከወረዳው ፓሊስ ጽህፈት...
14/08/2026

በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

በሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረማርያም ወረዳ መንገድ፣ ትራንስፓርትና ሎጀስቲክስ ጽህፈት ቤት ከወረዳው ፓሊስ ጽህፈት ቤት ጋር በመቀናጀት ከአሽከርካሪዎች ጋር ግምገማዊ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በውይይት መድረኩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይ ግዛው ፣ የወረዳው ፓሊስ ጽህፈት ቤት አዛዥ ኢ/ር ሽፈራ ሀይሉ፣የወረዳው መንገድ፣ ትራንስፓርትና ሎጀስቲክስ ጽቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ሀይሉ፣ የጽህፈት ቤቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡

ለውይይቱ ተሳታፊዎች የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የመንገድ ደህንነትና ትራንስፖርት ክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ዘገዬ ጌታሁን ከሪፖርታቸው ጋር አያይዘው እንደገለፁት 2018 ዓ.ም በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ የተስተዋሉ ጠንካራ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና መስተካከል ያለባቸውን ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ሆኖ ሁሉም አሸከርካሪዎች ህግና ስርዓትን በማክበር የሚያሽከረክሩት ተሽከርካሪ ብቃትና ደህንነት ማረጋገጥ በመናኸሪያ ውስጥ ስታንዳርድ አሟልቶ መገኘት ማንኛውም አሽከርካሪ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል ትርፍ ሰው መጫን የሚሉ ሀሳቦች ቀርበው ተገምግመዋል።

የቀረበውን የግምገማ ሪፖርት መነሻ በማድረግ በውይይቱ ላይ የተገኙት አሽከርካሪዎች በየጊዜው ካለው ዋጋ መጨመር እና የነዳጅ ዋጋ መናር ተያይዞ ታሪፉ ተመጣጣኝ አለመሆን ፣ የመንገድ ብልሽት ተሽከርካሪዎች ላይ አደጋ እየፈጠረብን ነው መንገዶች በወቅቱ ሊጠገኑ ይገባል በተለይም የመንገድ መጣበብ በሰራችን ላይ ጫና ፈጥሯል ብለዋል።

በቀጣይ በኛ በአሽከርካሪዎች በኩልም የሚስተዋለውን የስነ-ምግባር ክፍተቶች ተገልጋዩን በአግባቡ ማገልገል ላይ የሚስተዋለውን ችግር እናስተካክላለን የሚሉና ሌሎችንም ሀሳቦች አንሰተዋል፡፡

ከተሳታፊዎቹ ለተነሱ አስተዳደራዊ ጥያቄዎች የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይ ግዛው መመሪያና ደንቦችን መሠት አድርገው ማበራሪያ በመስጠት በወረዳችን በርካታ ተሽከርካሪዎች ያሉ በመሆኑ ለማህበረሰቡ የምንሰጠው አገልግሎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በየጊዜው በህብረተሰቡ ዘንድ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሚነሳባቸውን የትርፍ እና የታሪፍ ችግር ለመቅረፍ ዘመናዊ የመንገደኞች ትኬት መቁረጫ አገልግሎት አስጀምረናል በዚህም የተገልጋዩን እርካታ አሳድጓልም ብለዋል፡፡

በመሆኑም በቀጣይ ሁሉም አሽከርካሪ ለህዝብ መብት መጠበቅ ሀላፊነት ወስዶ መስራት አለበት በማለት ሰጥተዋል፡፡

የወረዳው ፓሊስ አዛዥ ኢ/ር ሽፈራ ሀይሉ በበኩላቸው በስነምግባር የታነፀ ወንጀልን የሚጠላ የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት በጥንቃቄ የሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎች መሆን እንዳለባቸው አሳስበው በቀጣይ የትራፊክ ደንብና መመሪያን በማክበር ምንም አይነት አደጋ እንዳይኖር፣ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸው ቦታ ላይ እንዲንቀሳቀሱ ፣ሀበትና ንብረታቸውን በአግባቡ እንዲጠብቁ አልሞ መስራት ይጠበቃልም ሲሉም ገልፀዋል፡፡

የወረዳው መንገድና ትራንስፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ሀይሉ በበኩላቸው የወረዳችን አሽከርካሪዎች በስነ-ምግባር ምስጉን ለህግና ስርአት ተገዥ ለተገልጋዮች ክብር ያላቸው አሽከርካሪዎች መኖራቸውን ገልፀው አመስግነዋል።

በተቃራኒው የስነ- ምግባር ችግር ያለባቸው አሽከርካሪዎች ከችግራቸው ፈጥነው አንዲወጡና እርምት እንዲወስዱ መክረው በቀጣይ የጋራ አቅጣጫ በመስጠት በተሰጠው አቅጣ ጫ መሰረት አሽከርካሪዎች ለሚያገለግሉት ህዝብ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል ፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገመገመ።ደብረ ብርሃን፦ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ...
11/08/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገመገመ።

ደብረ ብርሃን፦ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ተቋማት ጋር በመሆን የሐምሌ ወር አፈጻጸሙን በዙም ሚቲንግ ገምግሟል።

መምሪያው በ90 ቀናት ውስጥ ለማከናወን ያቀዳቸውን መደበኛ ተግባራትና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገምግሟል።

በግምገማው የሐምሌ ወር ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ቀርበው፣ የተገኙ ጥንካሬዎችና የታዩ እጥረቶች በመለየት ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በግምገማው ወቅት በቀጣይ በትራንስፖርት ዘርፍ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ማጠናከር፣ መደበኛ ቁጥጥርን በማጠናከር ሕገወጥነትን መከላከል፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተመላክቷል።

የመናኸሪያ ስምሪትንና አገልግሎት አሰጣጥን እንዲሁም መሠረተ ልማትን ማሻሻልና ማዘመን፣ የድንገተኛ ተሽከርካሪ ምርመራ አገልግሎትን ማጠናከር እና ሁሉአቀፍ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ከመንገድ ዘርፍ አንጻርም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ከወዲሁ መጀመር፣ በሁሉም ዘርፍ ሕዝቡን ባለቤትና ተሳታፊ በማድረግ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠበቅ ያለ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

መድረኩን የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ የመሩ ሲሆን፣ በመድረኩ የዞን ማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳና ከተማ ኃላፊዎችና የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የወረዳና ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

የመንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ።የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ አፈ...
30/07/2026

የመንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ።

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ከመምሪያው የማኔጅመንት አባላትና ጠቅላላ ሠራተኞች ጋር ገምግሟል።

​በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በመንገድና ትራንስፖርት ዘርፎች የተከናወኑ አበይት ተግባራትን አስመልክቶ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቧል።

ተሳታፊዎችም በውጤቶቹ እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

​በግምገማ መድረኩ ላይ እንደተመለከተው የተመዘገቡ ውጤቶች አብዛኞቹ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ አበይት ተግባራት በተሻለ ደረጃ መከናወናቸው ተገልጿል።

በሂደቱ የታዩ ጥንካሬዎች የተገመገሙ ሲሆን፣ የታዩ እጥረቶች ደግሞ በዝርዝር ተለይተዋል።

የታዩ እጥረቶችን በመቅረፍ በቀጣዩ የበጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ ተካተው ሊፈጸሙ የሚገባቸው ዋና ዋና ተግባራት ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

​በመጨረሻም የመድረኩ መሪ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ በበጀት ዓመቱ ለተመዘገቡት በጎ ውጤቶች የሠራተኞቹን አስተዋጽኦ አድንቀዋል።

በቀጣይም የተለዩ እጥረቶችን በማረም የተሻለ የህዝብ አገልግሎት ለመስጠት ሁሉም በቁርጠኝነት እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።(ሰሸመኮ)

Address

North Shewa Debre Birhan
Debre Birhan
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Region North Shoa Zone Road, Transport and Logistics Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share