East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office

East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office ለአደጋ የማይበገር እና የምግብ ዋስትናው የተረጋገጠ ማህበረሰብ ለመፍጠር ተግተን እንሰራለን!

የምስራቅ ጎጃም ዞን  የአደጋ ስጋት  ስራ አመራር  ተጠሪ ጽ/ቤት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ አብይ ኪሜቴ እና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የመስክ መልስ ስራዎችን ገመገመ።  ጳግሜ 2/2018 (አ...
07/09/2026

የምስራቅ ጎጃም ዞን የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ተጠሪ ጽ/ቤት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ አብይ ኪሜቴ እና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የመስክ መልስ ስራዎችን ገመገመ።
ጳግሜ 2/2018 (አስስኮ)
የዞኑ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ የቴክኒክ ቡድን የዝናብ እጥረቱ በታየባቸው ወረዳዎች በመስክ ተገኝቶ ያደረገውን ድጋፍና ያጋጠሙ ችግሮችንና የመፍትሔ ሀሳብ ያሏቸውን በማቅረብ ውይይትና የስራ ግምገማ ተካሄደ

07/09/2026
የምግብ ልኡላዊነትን ለማረጋገጥ ስንዴ በክላስተር እየለማ ነው፡፡በምስራቅ ጎጃም ዞን በባሶ ሊበን ወረዳ የምግብ ልኡላዊነትን ለማረጋገጥ ስንዴ በክላስተር እየለማ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽሕፈ...
07/09/2026

የምግብ ልኡላዊነትን ለማረጋገጥ ስንዴ በክላስተር እየለማ ነው፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን በባሶ ሊበን ወረዳ የምግብ ልኡላዊነትን ለማረጋገጥ ስንዴ በክላስተር እየለማ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል ።

በ14 የስንዴ አብቃይ ቀበሌዎች ለአርሶ አደሮች የግብዓትና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲሁም የሰብል ጥበቃ ምክር እየተሰጠ ነው።

የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ሙሉቀን አለሙ፣ ባለሙያዎች ሰብሉ በአረምና በተባይ እንዳይጠቃ በተከታታይ የሙያ ምክር እየሰጡ መሆኑን ጠቁመዋል።

በልምጭም ቀበሌም አርሶ አደሮች ስንዴን በኩታ ገጠም እያለሙ ሲሆን፣ የማሳ ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ በማድረግ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ ነው።

የባሶ ሊበን ወረዳ ተወካይ አስተዳዳሪና የአስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ድረስ ዋለ፣ የሚጠበቀውን ምርት ለማሳካት በቂ የግብዓት ስርጭት መደረጉን ገልጸዋል።

በያዝነው የምርት ዘመን በወረዳው ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ስንዴ ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ ነው።

የሰብል ጉብኝቱም የጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት የተካሄደ ሲሆን፣ አርሶ አደሮች የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ መድረክ መፍጠሩ ተገልጿል።

መረጃው የወረዳው መንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ነው፡፡

ከምስራቅ ጎጃም ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ተጠሪ ጽቤት

07/09/2026
07/09/2026
ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት" ቀን በጎዛምን ወረዳ በመስክ ምልከታ ተከበረ።   ****በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ ጳጉሜ 2- "የማንሰራራት" ቀንን አስመልክቶ  በፈንድቃ ታዳጊ ከተማ እየተ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት" ቀን በጎዛምን ወረዳ በመስክ ምልከታ ተከበረ።
****
በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ ጳጉሜ 2- "የማንሰራራት" ቀንን አስመልክቶ በፈንድቃ ታዳጊ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጉብኝት ተካሂዷል።

በዕለቱ ደጃት የዱቄት ፋብሪካ፣ MLE የጥራጥሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እና የነዳጅ ማደያ ግንባታዋች ተጎብኝተዋል።

በጉብኝት መርሀ ግብሩ ተገኝተው ለተሳታፊዋች መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቅነህ እንደግ በቀበሌው እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም አድንቀው ይህን መሰል የጉብኝት ፕሮግራም ማህበረሰቡ በአካባቢው እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲያውቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን አስገንዝበዋል።

ኃላፊው አክለውም የኢንቨስትመንት ዘርፉ እንደ ሀገር ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን ሽግግር እውን በማድረግ ሂደት ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ እንዳዘዘ ጎዴ የተጎበኙ ፕሮጀክቶች የአርሶ አደሩን ምርቶች በግብዓትነት ከመጠቀም በተጨማሪ ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልፀዋል።

አቶ እንዳዘዘ አያይዘውም የአካባቢው ማህበረሰብ ፕሮጀክቶችን በባለቤትነት በመጠበቅና በመንከባከብ በኩል የበኩሉን ሚና እንዲወጣ አሳስበዋል።

አልሚ ባለሀብቶች በበኩላቸው ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ለማስገባት የመንግስት አካላት አስፈላጊ የመሠረተ ልማቶችን በሟሟላት ሂደት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በዕለቱ የተጎበኙ ሦስቱም ፕሮጀክቶች በቀጣይ 2019 ዓ.ም ወደ ምርት እና አገልግሎት የሚገቡ መሆኑ ተገልጿል።

በጉብኝቱ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቅነህ እንደግን ጨምሮ ሌሎች የወረዳ አመራሮች እና የአካባቢው ነዋሪዋች ተሳትፈዋል።

መረጃዎ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ነው።

ከምስራቅ ጎጃም ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ተጠሪ ጽቤት

ጳጉሜ 2/  "የማንሠራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ በብቸና ከተማ አስተዳደር  2018ዓም የበጀት ዘመን የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በከተማ አስተዳደሩ የከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣ነጋዴዎች...
07/09/2026

ጳጉሜ 2/ "የማንሠራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ በብቸና ከተማ አስተዳደር 2018ዓም የበጀት ዘመን የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በከተማ አስተዳደሩ የከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣ነጋዴዎችና የአገር ሽማግሌዎች ተጎብኝቷል።

የከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የሕጻናት ማቆያ ሕንጻ ፣የአስተዳደር ጂ+2ሕንጻ ፣የኮሪደር ልማት ግንባታዎች በጎብኚዎች የተጎበኜ ሲሆን የብቸና ከተማ አስተዳደር መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላክ የአይኔ አበባ ለጎብኚዎች ገለጻ አድርገዋል። ኃላፊው ብር 80ሚሊዮን በላይ ወጭ በማድረግ የቴክኒክ ኮሌጅ የወርክ ሾፕ ሕንጻ፣ የዲች ፣ የመብራት ዝርጋታ ስራዎች፣ የተለያዩ ተቋማት አጥር ፣የሞዴል ሸድ ግንባታ ስራዎች፣ለዝቅተኛ ነዋሪዎች ቤት ግንባታ፣የብቸና ሆስፒታል አጥር ግንባታዎች ፣የወጣቶች መዝናኛ ጥገናዎች እና ሌሎች በርካታ ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይ የስራ ጊዜ እንደ ሀገር የሚደረገውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ የብቸና ከተማ ሕዝብ አካባቢውን ለማልማት ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊተጋገዝ ይገባል ብለዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ብቸና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት በቀለ ከተማችንን ለማልማት በሁሉም ዘርፍ ህብረተሰቡ ሊደግፍ ይገባል ብለዋል ።

በጉብኝቱ የተገኙት ጎብኝዎችም በከተማ አስተዳደሩ አቅም ይሕ የልማት ስራ መሠራቱ አስደናቂ ነው ፣ የብዙ ዘመን ጥያቄ የነበረው የመብራት ተደራሽነት ፍጥነት የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት

በምስራቅ ጎጃም ዞን በእነብሴ ሳርምድር ወረደ ጳጉሜ2-የማንሰራራት ቀንን "የኢትዮጵያ መንሠራራት" በሚል መሪ ሃሳብ  በእንቬቲቭ የተሰሩ ልዩ ልዩ  የልማት ፕሮጀክቶችን ጉብኝት እየተካሄ ነው።
07/09/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን በእነብሴ ሳርምድር ወረደ ጳጉሜ2-የማንሰራራት ቀንን "የኢትዮጵያ መንሠራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በእንቬቲቭ የተሰሩ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ጉብኝት እየተካሄ ነው።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት" የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ጷግሜ 1"የእምርታ ቀንን"  ምክንያት በማድረግ በወረዳው እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎች ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተዘሩ የጤፍና ...
07/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት"



የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ጷግሜ 1"የእምርታ ቀንን" ምክንያት በማድረግ በወረዳው እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎች ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተዘሩ የጤፍና የስንዴ ሰብል ጎብኝት ተካሄደ።
============
ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም(አስስአኮ
በምስራቅ ጎጃም ዞን የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ጷግሜ 1"የእምርታ ቀንን" ምክንያት በማድረግ በወረዳው እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎች ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተዘሩ የጤፍና የስንዴ ሰብል ጎብኝት ተካሄዷል።
በመስክ ምልከታውን የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉ ጌቴን ጨምሮ የወረዳ ጠቅላላ አመራሩ ተገኝቷል::
የመስክ ምልከታው ከተረጅነት ወደ ምርታማነት በወረዳው እየለማ ያለ 14ሄክታር መሬት ሰንዴናየወጣቶች የደሮ እርባታ ይገኙበታል።

 #ጷግሜ2-"የማንሰራራት ቀን"‎‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር ​«የኢትዮጵያ ማንሰራራት» በሚል መሪ ቃል ጳጉሜ -2 የማንሰራራት  ቀን  በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።‎‎ፕሮግራሙን...
07/09/2026

#ጷግሜ2-"የማንሰራራት ቀን"

‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር ​«የኢትዮጵያ ማንሰራራት» በሚል መሪ ቃል ጳጉሜ -2 የማንሰራራት ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

‎ፕሮግራሙን አስመልክቶም በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ወደ ስራ የገቡ የኢንዱስትሪ ፋብሪካዎች እና በከተማው የማህበረሰብ ተሳትፎ የተገነባ የአቅመ ደካማ ቤት ጉብኝት ተካሂዷል።

‎በጉብኝቱ ላይም የከተማ አስተዳደሩ ጠቅላላ አመራሮች ፤የሉመሜ ከተማ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ፤ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተውበታል።

‎ 🕊ሠላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሠላም🕊 ከሉማሜ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ፅ/ቤት የተወሰደ
‎ •~•~•

Address

Debra Markos

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share