23/06/2026
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ውጤት የሆነው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የአርሶ አደሮችን ህይወት እየቀየረ ነው።
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም (ደብረ ኤልያስ ኮሙኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ኤልያስ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ውጤት የሆነው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የላቀ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አርሶ አደሮች ተናገሩ።
በወረዳው፥ በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።
ባለፋት አመታት በሀገራችን ብሎም በወረዳችን ለአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሰጠው ልዩ ትኩረት አርሶ አደሩ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ በመሰማራት የላቀ ተጠቃሚ እየሆነ መጥቷል።
በወረዳው በአበሸብ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር መኮንን ቀሬ፣ በየዓመቱ የዝናብ ወቅትን ጠብቀው ማሳቸውን በተለያዩ ሰብሎች ከመሸፈን ይልቅ ፊታቸውን ወደ አረንጓዴ አሻራ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት በማዞር አቅደው መስራት ከጀመሩ ሰነባብተዋል።
የጉድጓድ ውሃን በመጠቀም እንደ አቮካዶ ያሉ ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ተክሎችን ማልማት ከጀመሩ ወዲህ የእርሳቸውም ሆነ የቤተሰባቸው ኑሮ እየተሻሻለ መምጣቱን አብራርተዋል።
ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጠቃሚና አዋጭ መሆኑን የተረዱት አርሶ አደር መኮንን፣ በቀጣይም በዘርፉ በስፋት ለመስራት ከመንግስት የቴክኖሎጂ አቅርቦት ድጋፍ ቢደረግላቸው የኢኮኖሚ አቅማቸው ይበልጥ እንደሚያድግ ያስረዳሉ።
በዘርፉ የተሰማሩት ሌላኛው አርሶ አደር ሻምበል ታደለ ቀሬ በበኩላቸው፣ መንግስት ያመጣውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጥቅም በመረዳት ወደ ፍራፍሬ ልማት መግባታቸውን ይናገራሉ። በግብርና ባለሙያዎች ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል በመታገዝም ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት በቀበሌው በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ33 ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ልማት መሸፈኑን ያስታወሱት የአበሸብ ቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት አስተባባሪ አቶ ስሜነህ ላቀ፣ አርሶ አደሩ በቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ ተክሎች ላይ ትኩረቱን እንዲያደርግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ውጤታማ የሆኑ አርሶ አደሮችን ተሞክሮ ሌሎችም እንዲከተሉ በማድረግ ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ለህብረተሰቡ የተመጣጠነ ምግብ ከማስገኘታቸውም በላይ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበት ዘርፍ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት ሰዋለም ናቸው።
በወረዳው ባለፉት አመታት በተሰራው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር 495 ሄክታር መሬት በአትክልትና ፍራፍሬ ተክል የተሸፈነ መሆኑን ገልፀው፣ በዘንድሮው ዓመትም የተሻለ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ከ120 ሺህ በላይ የአቮካዶና የቡና ችግኞችን በ117 ሄክታር መሬት ላይ ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ እሱባለው በበኩላቸው፤ በወረዳው እየተከናወነ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ እና ለምግብነት የሚያገለግሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። ለዚህም የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ለማልማት በስፋት ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
በዘርፉ አርሶ አደሩን በማደራጀት ተጠቃሚ እንዲሆን የባለሙያ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው፣ ወረዳው