የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ

የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ

24/03/2026

በዞናችን በ2018 ዓ.ም በጀት አመት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም በመንግሥት ጉዳዮች ላይ በተደረገ ድርድርና ክርክር ብር 9,633,630.41 ለመንግስት ገቢ ማድረግ ተችሏል። ይህም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ገቢው በእጥፍ እንደጨመረ ያሳያል ። ለዚህ ለውጥ መመዝገብ ቁልፉ ነጥብ በየደረጃው ያሉ ዐቃብያነ ህጎች እና አመራሩ ተቀናጅተው መንቀሳቀሳቸው በመሆኑ በርቱ ሊባሉ ይገባል !!

18/06/2020
18/06/2020

የሰኔ 15/2011ዓ.ም የአማራ ክልል አመራሮች መስዋዕትነትን የሚዘክር ጉብኝትተካሄደ

በደቡብ ጎንደር ዞን በእብናት ወረዳ የዞን እና ከተለያዩ ወረዳ የመጡ አመራሮች በተገኙበት የሰኔ 15/2011ዓ.ም የአማራ ክልል አመራሮች መስዋዕትነትን የሚዘክር ጉብኝት ዋነኛ ትኩረቱም በወረዳው የ2011 የተተከለ ችግኝ ምን ደረጃ ላይ እንዳለና ለ2012 ለሚደረገው የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት ስራ ተጎብኝቷል ፡፡

የእብናት ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መለሱ እንግደው እንደገለፁት በወረዳችን የሚደረገው የስራ ጉብኝት በዞን የተዘጋጀና በሰኔ አስራ አምስቱ የተሰው ጓዶቻችን ለማሰብ የሚደረግ ነው፡፡

በዛሬው እለት ባለፈው አመት የተተከሉ ችግን ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለ2012 ዓ.ም ለሚደረገው የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት ስራና ወረዳው ያለበትን የተለያዩ የልማት ስራዎች ለማየት በዞን ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ የሚመራው ሉዑክ በወረዳችን ስለተገኘ በማመስገን የዝሃ ችግኝ ጣቢያ እና የመጨናና የአምስትያ ቀበሌዎች ተፋሰሶች ተጎብኝተዋል፡፡

የጉብኝት ልዑኩን የመሩት የደቡብ ጎንደር ዞን የብልፅግና ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እንደገለፁት በእብናት ወረዳ የጎበኘናቸው ያለፈው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ ውጤቶችም ይሁኑ የ2012 የአረንጓዴ ልማት ቅድመ ዝግጅት ከዚህም ባሻገር የተፋሰስ ልማትና የጠረጴዛ እርከን አሰራሩ የ2012ዓ.ም የአረጓዴ አሻራ ማጠናቀቂያ እብናት ወረዳ እንዲሆንና ተሞክሮ እንዲወሰድበት የሚያነሳሳ ነው ሲሉ አውስተው ይሄንም ላደረጉ የመንግስት ዓመራሮች ባለሙያዎችና ህዝቡ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል፡፡
የደቡብ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
11/10/2012 ዓ.ም
ምንጭ ፡- የእብናት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን

18/06/2020

የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሲጨምር መንግስት ለምን መንግስትነቱን አላሳዬም?

18/06/2020
17/06/2020
17/06/2020

የሰኔ 14ቱ የጸሃይ ግርዶሽ!

ሙሉ ወይም ቶታል የጸሃይ ግርዶሽ በየ3 ዓመት ሁለት (2) ጊዜ ሲከሰት ፤ በአንድ ስፍራ ላይ በድጋሚ ለመከሰት እስከ 400 ዓመት ሊፈጅ ይችላል።

ከዚህ በኃላ በሀገራችን ብዙ ሰዎች የሚመለከቱት ከሰኔ 14ቱ ጋር ተመሳሳይ ግርዶሽ የሚከሰተው ከ54 ዓመት በኃላ ሲሆን ሐረር ፣ ጅግጅጋ ፣ ድሬዳዋ ፣ ደብረ ብርሃን እና ደብረ ማርቆስ እሳታማ ቀለበት ለመመልከት እድለኛ ስፍራዎች ይሆናሉ።

ማሳሰቢያ ፦ የጸሃይ ግርዶሽ በዓይን መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል ፤ ሶላር ኢክሊፕስ መነፅር በመጠቀም፣ በጨለማ ክፍል ውስጥ በቀዳዳ የሚገባ የጸሃይ ብርሃን የሚስለውን ቅርፅ በመመልከት ወይም ፒን ሆል ካሜራ በመስራት መመልከት ይቻላል

16/06/2020

ዴክሳሜታሰን መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት እንደሚታደግ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአነስተኛ ዋጋ በስፋት የሚገኘው “ዴክሳሜታሰን” የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታደግ እንደሚረዳ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ።

እንደተመራማሪዎቹ ገለፃ በመድሃኒቱ በአነስተኛ ዶዝ በሚሰጠው የስቴሮይድ ህክምና የኮሮና ቫይረስን በመዋጋት ሂደት ከፍተኛ ውጤት የሚያመጣ ነው።

መድሃኒቱ በተለይም በመተንፈሻ መሳሪያዎች (ቬንትሌተር) እና ኦክሲጅን ድጋፍ የሚተነፍሱትን ታማሚዎች የመሞት እድልን የሚቀንስ መሆኑንም አስታውቀዋል።

እንደ ተመራማሪዎቹ ገለፃ መድሃኒቱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን በብሪታኒያ እንደገባ ጥቅም ላይ መዋል ቢጀምር እስከ 5 ሺህ የሚደርሱ ሰዎችን ህይወት መታደግ ይቻል ነበረ።

“ዴክሳሜታሰን” የተባለው መድሃኒት ዋጋም አነስተኛ በመሆኑ በተለይም ከፍተኛ የኮሮና ቫይረስ ታማሚዎችን ለያዙ በዝትቀኛ የገቢ ደረጃ ላይ ላሉ ሀገራት ጠቃሚ መሆኑንም አስታውቅዋል።

በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 20 ሰዎች ውስጥ 19 በቶሎ የሚያገግሙ መሆኑን ያስታወቁት ተመራማሪዎቹ፥ በፀና ታመው ሆስፒታል ከሚገቡት መካከል ውስጥ ግን የተወሰኑት እንደ ቬንትሌተር እና ኦክሲጅን አጋዥ የመተንፈሻ መሳሪያዎች ያስፈልጋቸዋል ይላሉ።

ታዲያ “ዴክሳሜታሰን” የተባለው መድሃኒትም በአጋዥ የመተንፈሻ መሳሪያዎች ለሚያስፈልጋቸው ታማሚዎች ነው ጥቅም ላይ የሚውለውም ብለዋል።

በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ቡድን በመድሃኒቱ ላይ በተደረገው ጥናትም በሆስፒታል ውስጥ ለሚገኙ 2 ሺህ ሰዎች “ዴክሳሜታሰን” እንዲሰጥ በማድረግ መድሃኒቱን ካልወሰዱት 4 ሺህ ሰዎች ጋር በማነፃፀር ተመልክቷል።

በዚህም በመተንፈሻ መሳሪያዎች (ቬንትሌተር) ድጋፍ ላይ ባሉ ታማሚዎችላይ የሚከሰት ሞትን ከ40 እስከ 28 በመቶ ቀንሷል ያሉ ሲሆን፥ በኦክሲጅን ታግዘው በሚተነፍሱ ታማሚዎች ላይ የሚከሰትን ሞትን ደግሞ ከ25 እስከ 20 በመቶ መቀነሱን አስታውቅዋል።

የጥናት ቡድኑ መሪ ፕሮፌሰር ፒተር ሆርቢ ፥ እስካሁን ከተደረጉ ሙከራዎች በኮሮና ቫይረስ የሚከሰት ሞትን በመቀነስ ረገድ “ዴክሳሜታሰን” መድሃኒት የመጀመሪያው መሆኑን እና በኮቪድ 19 ላይ በሚደረገው ምርምርም ትልቅ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።

በጥናቱ ላይ የተሳተፉት ፐሮፌሰር ማርቲን ላንድረይ በበኩላቸው፥ መድሃኒቱ በዓለም ዙሪያ የሚገኝ መሆኑ እና ዋጋውን አነስተኛ መሆኑ በፅኑ የታመሙ ሰዎችን ህይወት በመታደግ ረገድ ከፍተኛ ጥቅም አለው ብለዋል።

ሆስፒታሎች በኮቪድ 19 በጽኑ ለተመሙ ታካሚዎቻቸው መድሃኒቱን እንዲሰጡ እናበረታታለን ያሉት ፐሮፌሰር ማርቲን ላንድረይ፥ ሆኖም ግን መድሃኒቱ በጽኑ ለታመሙት ብቻ የሚያገለግል በመሆኑ ሰዎች በራሳቸው ፍቃድ ገዝተው ሊጠቀሙት አይገባም ሲሉም አሳስበዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ



የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 109 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,102 የላብራቶሪ ምርመራ 109 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ ...
16/06/2020

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 109 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,102 የላብራቶሪ ምርመራ 109 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3,630 ደርሷል። የ1 ሰዉ ህይወት አልፏል

በኢትዮጵያ በአንድ ቀን 118 ሰዎች አገገሙ!

በትላንትናው ዕለት አንድ መቶ አስራ ስምንት (118) ሰዎች (115 ከአዲስ አበባ ፣ 3 ሰዎች ከትግራይ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት(738) ደርሷል።

ከኮቪድ-19 ያገገሙ 87 ሰዎች ከሚሊኒየም ማገገሚያ ማዕከል ወጡ!'በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ' ስር በሚገኘው የሚሌኒየም ማገገሚያ ማዕከል ውስጥ ከኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-...
16/06/2020

ከኮቪድ-19 ያገገሙ 87 ሰዎች ከሚሊኒየም ማገገሚያ ማዕከል ወጡ!

'በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ' ስር በሚገኘው የሚሌኒየም ማገገሚያ ማዕከል ውስጥ ከኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ያገገሙ 87 ሰዎች ከማዕከሉ መውጣታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የማዕከሉ ክሊኒካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ውለታው ጫኔ እንደገለጹት ፤ በአሁኑ ወቅት በማዕከሉ ውስጥ 656 ኮሮና ቫይረስ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ህክምናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ።

ከነዚህ ውስጥ 157 ሰዎች የመጀመሪያ የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤታቸው ከኮሮናቫይረስ ማገገማቸውን (ኔጋቲቭ) ያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ 87 ሰዎች ዛሬ ከማዕከሉ እንዲወጡ መደረጉን አመልክተዋል።

Address

East Gojjam Zone
Debra Markos

Telephone

+251587711308

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category