Niguss Teklehaymanot Sub City Addministration Communication

Niguss Teklehaymanot Sub City Addministration Communication ይህ ፔጅ የንጉስ ተክለሃይማኖት ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ድህረ ገፅ ነው ላይክ ሼር ኮሜንት በማድረግ የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ !!!

‎በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለ ሃይማኖት ክፍለ ከተማ“ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሉዓላዊነት”በሚል መሪ ሀሳብ ከ4 ሄክታር በላይ መሬት በማህበረሰብ ንቅናቄ ማሳን በሰ...
04/08/2026

‎በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለ ሃይማኖት ክፍለ ከተማ“ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሉዓላዊነት”በሚል መሪ ሀሳብ ከ4 ሄክታር በላይ መሬት በማህበረሰብ ንቅናቄ ማሳን በሰብል የመሸፈን ስራ ተጀመረ።

‎በንጉስ ተክለሃይማኖት ክፍለ ከተማ ሀምሌ 28/2018ዓ.ም “ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ‎ሀሳብ ከ4 ሄክታር በላይ መሬት በሕዝብ ንቅናቄ ማሳን በሰብል የመሸፈን ስራ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ፣ የክልል ደጋፊ አመራሮችና ባለሙያዎች ፤ አቶ አበባው ግዛቸው የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ የአቅም ግንባታና የፖለቲ ዘርፍ ሃላፊ፣ አቶ መለሠ ሙላት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ሃላፊ፣ የንጉስ ተክለሃይማኖት ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንማው መላክ ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መሃሪው ነገሰ ፣የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣የግብርና ባለሙያዎች፣የአካባቢው አርሶ አደሮች እና በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በተገኙበት በስኬት እየተከናወነ ይገኛል።

‎ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሰረት ያደረገ አዲስ ጅምር የአካባቢውን አጠቃላይ ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የሕዝብን የምግብ ዋስትና በራስ አቅም አስተማማኝ በሆነ መንገድ ለማረጋገጥ እና የጥገኝነት አስተሳሰብንና ተረጅነትን ማስቀረት ቁልፍ ዓላማው ያደረገ መሆኑን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንማው መላክ ገልፀዋል።

‎የፕሮግራሙ ዋና አላማም ፦ከጠባቂነትና ከጥገኝነት በመላቀቅ ሰባዊ ድጋፎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ከሀገራዊ ኢኒሸቲቮች ውስጥ አንዱ በመሆኑ ሰርቶ የሚለወጥና የጥገኝነት አስተሳሰብን የሚፀየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የልማት አርበኛ ለመሆን፣በእራስ አቅም በምግብ እራስን ለመቻል እና ከውጭ እርዳታና ከተረጅነት ስነ-ልቦና ለመላቀቅ መሆኑን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንማው መላክ ገልፀዋል።

‎በስተመጨረሻም አርሶ አደሮች የዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ ተደርጓል።

‎🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

02/08/2026
የሰላም ማስከበር አቅምን ለማጠናከር የሠለጠኑ ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ ።የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ሥራ የበለጠ ለማጠናከር በደ...
02/08/2026

የሰላም ማስከበር አቅምን ለማጠናከር የሠለጠኑ ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ ።

የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ሥራ የበለጠ ለማጠናከር በደብረ ማርቆስ ከተማ በሚገኘው የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ደብረ ማርቆስ መሠረታዊ ፖሊስ ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ከደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ያሠለጠናቸው ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቀዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ የአገርን ሰላም፣ ሉዓላዊነትና ሕዝባዊ ደህንነት ለማደፍረስ የሚደረጉ ማናቸውም ሙከራዎች ሊሳኩ እንደማይችሉ ገልጸው የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ከሕዝብ ጋር በመተባበር የሰላም ጠባቂነት ተልዕኳቸውን በብቃት እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

አቶ ተሾመ አክለውም ተመራቂዎቹ የሕዝብን ሰላምና ደህንነት የማስከበር ከባድ ኃላፊነት እንደተጣለባቸው በማስገንዘብ፣ ከሕግ አስከባሪ ተቋማትና ከማኅበረሰቡ ጋር በተቀናጀ ሁኔታ በመስራት ዜጎች በሰላምና በመረጋጋት እንዲኖሩ የተጠበቀባቸውን ግዴታ በታማኝነትና በሙያዊ ብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል።

አቶ ተሾመ ዋለ በመልዕክታቸው፣ የኢትዮጵያ አርበኞች የሀገራቸውን ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የከፈሉት መስዋዕትነት የዛሬው ትውልድ የሚወስደው ታሪካዊ አደራ መሆኑን ገልጸው ፤ ተመራቂዎቹም ያንን ታሪካዊ ወግ በመጠበቅ ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው ታማኝ በመሆን፣ የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት፣ በሙያዊ ብቃትና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ አሳስበዋል።

ተመራቂዎቹ በበኩላቸው በሥልጠና ቆይታቸው ያገኙት የወታደራዊ ዕውቀት፣ ሙያዊ ክህሎትና የአመለካከት ግንባታ ለሚጠበቅባቸው ተልዕኮ በቂ ዝግጅት እንዳደረገላቸው ገልጸው በቀጣይም የሕዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስከበር በቁርጠኝነትና በሙሉ ኃላፊነት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ኃላፊዎች፣ አሠልጣኞች፣ የፀጥታ ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች የተጋበዙ እንግዶች ተገኝተው ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

የአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስ የስራ ሃላፊዎች ለንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ምረቃ ደብረ ማርቆስ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገ...
11/07/2026

የአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስ የስራ ሃላፊዎች ለንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ምረቃ ደብረ ማርቆስ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
*************
ሐምሌ 4/2018ዓ.ም፡ የአብክመ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስ የስራ ሃላፊዎች ደብረ ማርቆስ ከተማ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልል ቢሮ ሃላፊዎች፣ የከተማ አስተዳደሩ እና የምስራቅ ጎጃም ዞን የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ማርቆስ ወደ ቀደመ ከፍተዋ የደብረ ማርቆስ ከተማ የንጉስ ተክለሀይማኖት ኤርፖርት ምረቃ አሁናዊ የዋዜማ ከፊል ገጽታ በምስል በዋና ዋና መንገዶች
10/07/2026

ማርቆስ ወደ ቀደመ ከፍተዋ

የደብረ ማርቆስ ከተማ የንጉስ ተክለሀይማኖት ኤርፖርት ምረቃ አሁናዊ የዋዜማ ከፊል ገጽታ በምስል በዋና ዋና መንገዶች

10/07/2026

Address

Debre Markos
Debra Markos

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Niguss Teklehaymanot Sub City Addministration Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Niguss Teklehaymanot Sub City Addministration Communication:

Shortcuts

Share