North Gondar Communication

North Gondar Communication የፌስቡክ ገፃችንን ይውደዱን፣ይጋሩንና አስተያየት ይስጡን?

የክረምቱን መግባት ተከትሎ ከሚከሰት የወባ በሽታ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል። ወቅቱን መገንዘብ እና ተገቢውን ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እጅግ መሠረታዊ ነገር ነው። ሞቃታማው ወራት አልፎ ቅዝቃዜ ከሚ...
04/06/2026

የክረምቱን መግባት ተከትሎ ከሚከሰት የወባ በሽታ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

ወቅቱን መገንዘብ እና ተገቢውን ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እጅግ መሠረታዊ ነገር ነው። ሞቃታማው ወራት አልፎ ቅዝቃዜ ከሚተካበት ወራት ልንደርስ ጫፍ ላይ እንገኛለን። ይህ ወቅት ታዲያ ጥንቃቄ የሚፈልግ ጊዜ ነው።

በተለይም ለሰው ልጅ የጤና ጠንቅ የኾነችው ወባ አምራቹን በስፋት ልታጠቃ የምትችልበት ምቹ አጋጣሚ የሚፈጠርበትም ጊዜ ነው።
ወረዳችን ላይ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች የወባ በሽታ ተጠቂ የሚሆኑበት ወቅት እየደረሰ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል ።

የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን አንከላከል!! ደባርቅ፡- ግንቦት 27/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን) ግብርና ለኢትዮጵያ አኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑ ለማንም የማይ...
04/06/2026

የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን አንከላከል!!

ደባርቅ፡- ግንቦት 27/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

ግብርና ለኢትዮጵያ አኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑ ለማንም የማይታበል ሃቅ ነው። የዞኑን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ና ለኢንዱስትሪ ግበአቶች የሚሆን ምርት ለማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡

በመሆኑም ለ2018/ለ2019 በጀት አመት የተሻለ ምርት ለማግኘት በሰብል ልማት ላይ የበለጠ ርብርብ የምናደረግበት ወቅት ነው፡፡ ምርት ለመጨመር ደግሞ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን በማመረትና የሰብል በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸው ዝርያዎችን መጠቀም ተገቢ ነው፡፡
እንዲሁም መሬትን ደጋግሞ በማለስለስ፣የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ በመጠቀም፣በመስመር በመዝራትና ሰብሎችን አፈራርቆ መዝራት ምርትን በእጥፍ የሚያሳድጉ አይነተኛ ብልሃቶች በመሆናቸው ትኩረት ሰጥተን ተግባራዊ ልናደረጋቸው ይገባል፡፡

በመሆኑም ከላይ የተገለጹትን ምክረ ሃሳቦች ተግበራዊ በማድረግ ምርትን በእጥፍ በማሳደግ
የወቅቱን የኑሮ ውድነት በጋራ እንከላከል የእለቱ መልእክታችን ነው፡፡

- አርሶ አደሩን ከባህላዊ ግብርና ወደ ዘመናዊ ግብርና እናሸጋግር!!
- ምርትን በእጥፍ በማሳደግ የዞኑን ምግብ ዋስትና እናረጋግጥ!!
ለበለጠ መረጃ :-
ዩቲዩብ https://youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/Northgcd
ዌብሳይት https://northgondarcom.gov.et/
ፌስቡክ https://www.facebook.com/
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/
ይጎብኙን

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤ የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ  ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላ...
04/06/2026

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ያካሄደችው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት በስኬት በመጠናቀቁ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ብሏል።

ለዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ ለሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች፣ ለበጎ ፈቃደኞች፣ ለምርጫ አስፈጻሚዎች እና ምርጫው ስኬታማ እንዲኮን ጊዜያቸውን ለሰጡት ሁሉ ያላውን አድናቆት ገልጿል።

የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የታዛቢ ቡድኖች የነበራቸውን አስተዋጽኦ በበጎ እንቀበላለን ነው ያለው።

የአውሮፓ ኅብረትም ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መካሄዱን በደስታ እንቀበላለን ብሏል።

​ ለምርጫ መሳካት አስተዋጽዖ ያበረከቱትን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን እና የሲቪል ማኅበራት ተዋናዮችን ጥረት እናደንቃለን ነው ያለው።

​የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ( ኢጋድ) እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች የተጫወቱትን ወሳኝ ሚና እንገነዘባለን ብሏል። የታዛቢዎችን ሪፖርት በጉጉት እንደሚጠብቅም አስታውቋል።

​በግንቦት 24 ቀን ምርጫ ማካሄድ ያልቻሉ ሁሉም የምርጫ ክልሎች ምርጫውን የማካሄድ ዕድል እንደሚያገኙ ያለውን ተስፋም ገልጿል።

ጃፓን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላሳየው ሥራ ያላትን  አድናቆቷን ገለጸች። ባሕር ዳር፡ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ባወጣው ...
04/06/2026

ጃፓን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላሳየው ሥራ ያላትን አድናቆቷን ገለጸች።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 የተካሄደውን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደራጀት እና ለመምራት ላደረገው ከፍተኛ ጥረት አድናቆቱን ገልጿል።

ጃፓን በምርጫ ሂደቱ ላይ ለተሳተፉት እጩ ተወዳዳሪዎች፣ ድምፃቸውን ለመስጠት ለቻሉ የኢትዮጵያ ዜጎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች።

ጃፓን የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ሂደት ለመደገፍ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የገንዘብ ድጋፍ በማድረጓ የተሰማትን ደስታ ገልጻለች።

#አሚኮ ዲጂታል

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"         ክቡር አረጋ ከበደየአማራ ክልል ርእ...
04/06/2026

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"

ክቡር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር

በህውሃት ጦርነት ጊዜ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ቴሌ ታወሮች ተጠግነው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።ደባርቅ:- ግንቦት 26/2018  ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )በሰሜን ጎንደር ዞን በጠለ...
03/06/2026

በህውሃት ጦርነት ጊዜ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ቴሌ ታወሮች ተጠግነው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።

ደባርቅ:- ግንቦት 26/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )

በሰሜን ጎንደር ዞን በጠለምት ወረዳ በህውሃት ጦርነት ጊዜ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ቴሌ ታወሮች ተጠግነው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።

የጠለምት ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዮሃንስ ደስታ እንደገለፁት በህውሃት ጦርነት ጊዜ ጉዳት ደርሶባቸው ለተከታታይ 4 ዓመታት አገልግሎት ሳይሰጡ የነበሩ የታርናሻ እና የነጋዴ መሻገርያ የጡልሳ ቴሌ ታወሮች ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት ጀምረዋል ብለዋል።
አቶ ዮሃንስ አክለውም ቴሌ ታወሩ አገልግሎት እንዲሰጥ ግፊት ሲያደርጉ ለቆዩ አካላት እና ጥገናውን ላከናወኑት አካላት ምስጋና አቅርበዋል ።
ለበለጠ መረጃ
ዩቲዩብ https://youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/Northgcd
ዌብሳይት https://northgondarcom.gov.et/
ፌስቡክ https://www.facebook.com/
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/
ይጎብኙን

በደባርቅ ወረዳ በአድስጌ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናወነ ።                  በደባርቅ ወረዳ በአድስጌ ቀበሌ የተ...
03/06/2026

በደባርቅ ወረዳ በአድስጌ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናወነ ።

በደባርቅ ወረዳ በአድስጌ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የወረዳና የዞን አመራሮች በተገኙበት የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናውኗል ።

በምርቃት ፕሮግራሙ ተገኝተው በፕሮግራሙ ለተሳተፉት አካላት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበባው አዛናው በአድስጌ ቀበሌ የተገነባው የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ በአለም ባንክ የበጀት ድጋፍ በ3R-4-CACE ፕሮጀክት የተገነባውን የወረዳና የዞን አመራሮች በተገኝንበት አስመርቆ ሪቫን መቁረጥ የግንባታውን ደረጃ በልኩ አውቆ ለቀጣይ የጎደሉ ግብአቶችን አሟልቶ ማህበረሰቡ የተስተካከለ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናው የላቀ መሆኑን አብራርተዋል ።

የተገነባው ደረጃውን የጠበቀ የጤና ኬላ ተቋም የቀበሌው ማህበረሰብ ተረክቦ በአግባቡ ሊንከባከበው እንደሚገባ ያብራሩት አቶ አበባው የተገነባው የጤና ኬላ ተቋምን ጨምሮ ግንባታው ያረፈበት ቦታ ከሶስተኛ ወገን በማፅዳት የባለቤትነት የይዞታ ህጋዊ የማረጋገጫ ደብተር ወጥቶለት የጤና ተቋሙ ደህንነት በመጠበቅ በኩል የቀበሌው ማህበረሰብና ሌላው ባለድርሻ አካላት የየበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አሳሰበዋል ።

የአድስጌ ቀበሌ ህዝብ እስካሁን ድረስ ደባርቅ ጤና ጣቢያና ሆስፒታል ድረስ በመሄድ የጤና ጥበቃ አገልግሎት ያገኝ እንደነበር ያነሱት የወረዳው የጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ሃይሌ ሞገስ የቀበሌው ህዝብ በማእከላቸው ደረጃውን የጠበቀ የጤና ኬላ ተቋም መገንባት በቅርበት የጤና ጥበቃ አገልግሎት በማግኘት ከአላስፈላጊ የጊዜ ብክነትና የኢኮኖሚ ወጭ እንደሚታደጋቸው አብራርተዋል ።

የጤና ጥበቃ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ የጤና ተቋም መገንባት የቀበሌውን ማህበረሰብ ጤንነት በመጠበቅ በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያብራሩት የሰሜንጎንደር ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሰውነት ውባለም ህዝቡ የተሳካ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኝ ጤና ኬላው የሚያስፈልገውን የሰውሃይልና ግብአት በሟሟላት የቀበሌውን ህብረተሰብ ጨምሮ በምርቃት ፕሮግራም የተገኙትን የወረዳና የዞን አመራሮች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ በማእከላቸው መገንባቱ ያስደሰታቸው የቀበሌው ነዎሪዎች የተገነባው የጤና መጠበቂያ ተቋም ለቀበሌው ማህበረሰብ ውጤታማ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲሰጥ በተቋሙ የጎደሉ የህክምና ቁሳቁሶች፤የሰው ሃይልና ሌሎች ግብአቶችን እንዲሟሉ በፕሮግራሙ ለተገኙት የወረዳና የዞን አመራሮች አሳስበዋል ።

የተገነባው የተቀናጀ አገልግሎት የሚሰጥ የጤና ኬላ ከሶስተኛ ወገን ነፃ በማድረግ ህጋዊ የባለቤትነት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በማሰራት በአግባቡና በእንክብካቤ እንደሚይዙት የገለፁት ነዎሪዎቹ የተገነባው የጤና መጠበቂያ ተቋም የማህበረሰቡን ጤና በመጠበቅ ሚናው የላቀና በቅርስነት ለትውልድ የሚሸጋገር በመሆኑ ህዝቡ በእንክብካቤ እንደሚይዘው ሃሳብ አስተያየታቸውን አብራርተዋል ።
ለበለጠ መረጃ
ዩቲዩብ https://youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/Northgcd
ዌብሳይት https://northgondarcom.gov.et/
ፌስቡክ https://www.facebook.com/
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/
ይጎብኙን
#የደባርቅ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን

የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናወነ ።                    ደባርቅ : ግንቦት 26/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር  ኮሙዩኒኬ...
03/06/2026

የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናወነ ።

ደባርቅ : ግንቦት 26/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በአድስጌ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ ግንባታ የወረዳና የዞን አመራሮች በተገኙበት የማስመረቅና ሪቫን የመቁረጥ ስራ ተከናውኗል ።

በምርቃት ፕሮግራሙ ተገኝተው በፕሮግራሙ ለተሳተፉት አካላት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበባው አዛናው በአድስጌ ቀበሌ የተገነባው የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ በአለም ባንክ የበጀት ድጋፍ በ3R-4-CACE ፕሮጀክት የተገነባውን የወረዳና የዞን አመራሮች በተገኝንበት አስመርቆ ሪቫን መቁረጥ የግንባታውን ደረጃ በልኩ አውቆ ለቀጣይ የጎደሉ ግብአቶችን አሟልቶ ማህበረሰቡ የተስተካከለ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናው የላቀ መሆኑን አብራርተዋል ።

የተገነባው ደረጃውን የጠበቀ የጤና ኬላ ተቋም የቀበሌው ማህበረሰብ ተረክቦ በአግባቡ ሊንከባከበው እንደሚገባ ያብራሩት አቶ አበባው የተገነባው የጤና ኬላ ተቋምን ጨምሮ ግንባታው ያረፈበት ቦታ ከሶስተኛ ወገን በማፅዳት የባለቤትነት የይዞታ ህጋዊ የማረጋገጫ ደብተር ወጥቶለት የጤና ተቋሙ ደህንነት በመጠበቅ በኩል የቀበሌው ማህበረሰብና ሌላው ባለድርሻ አካላት የየበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አሳሰበዋል ።

የአድስጌ ቀበሌ ህዝብ እስካሁን ድረስ ደባርቅ ጤና ጣቢያና ሆስፒታል ድረስ በመሄድ የጤና ጥበቃ አገልግሎት ያገኝ እንደነበር ያነሱት የወረዳው የጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ሃይሌ ሞገስ የቀበሌው ህዝብ በማእከላቸው ደረጃውን የጠበቀ የጤና ኬላ ተቋም መገንባት በቅርበት የጤና ጥበቃ አገልግሎት በማግኘት ከአላስፈላጊ የጊዜ ብክነትና የኢኮኖሚ ወጭ እንደሚታደጋቸው አብራርተዋል ።

የጤና ጥበቃ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ የጤና ተቋም መገንባት የቀበሌውን ማህበረሰብ ጤንነት በመጠበቅ በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ያብራሩት የሰሜንጎንደር ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሰውነት ውባለም ህዝቡ የተሳካ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኝ ጤና ኬላው የሚያስፈልገውን የሰውሃይልና ግብአት በሟሟላት የቀበሌውን ህብረተሰብ ጨምሮ በምርቃት ፕሮግራም የተገኙትን የወረዳና የዞን አመራሮች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የተቀናጀ የጤና አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ በማእከላቸው መገንባቱ ያስደሰታቸው የቀበሌው ነዎሪዎች የተገነባው የጤና መጠበቂያ ተቋም ለቀበሌው ማህበረሰብ ውጤታማ የጤና ጥበቃ አገልግሎት እንዲሰጥ በተቋሙ የጎደሉ የህክምና ቁሳቁሶች፤የሰው ሃይልና ሌሎች ግብአቶችን እንዲሟሉ በፕሮግራሙ ለተገኙት የወረዳና የዞን አመራሮች አሳስበዋል ።

የተገነባው የተቀናጀ አገልግሎት የሚሰጥ የጤና ኬላ ከሶስተኛ ወገን ነፃ በማድረግ ህጋዊ የባለቤትነት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በማሰራት በአግባቡና በእንክብካቤ እንደሚይዙት የገለፁት ነዎሪዎቹ የተገነባው የጤና መጠበቂያ ተቋም የማህበረሰቡን ጤና በመጠበቅ ሚናው የላቀና በቅርስነት ለትውልድ የሚሸጋገር በመሆኑ ህዝቡ በእንክብካቤ እንደሚይዘው ሃሳብ አስተያየታቸውን አብራርተዋል ።

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ  ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ...
03/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

#የአሚኮ

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት አስታወቀ።የደ...
03/06/2026

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት አስታወቀ።

የደባርቅ ወረዳ ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ በሪሁን ጥላሁን 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በወረዳ ባሉ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ህዝቡ በንቃት ወጥቶ ድምፁን በመስጠት 7ኛው ሃገራዊ ምርጫው በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን አሳውቀዋል ።

ሃላፊው አያይዘው እንደገለፁት በጫካ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የብድን አባላት በአንዳንድ አጎራባች ወረዳዎችና ቀበሌዎች ትንኮሳ ለመፍጠር አስቦ ቢንቀሳቀስም በሰላም ወዳዱ ህዝብ ቁርጠኝነትና በጥምር የፀጥታ ኃይላችን በተባበረ ክንድ እንዲሁም ተገግባቦት በተሞላበት ቅንጅትና ዝግጅት የህገወጥ ቡድኑ እቅድና አላማ ሙሉ በሙሉ መክሸፉ መቻሉን አስታውቀዋል።

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በወረዳ በሰላምና በስኬት እንዲከናወን አስተዋፅዖ ላደረጉ ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት አባላት ፣ ለጥምር የፀጥታ መዋቅሮችን ፣ በየደረጃው ለሚገኙ የፖለቲካ አመራሮች፣ ለምርጫ አስፈፃሚዎችና ታዛቢዎች፣ ለቀበሌ አመራር እና የፀጥታ መዋቅር አባላት እንዲሁም ለመራጩ ህዝብ በተቋሙ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
#የደባርቅ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

Address

North
Debark'

Telephone

+251584171125

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North Gondar Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to North Gondar Communication:

Share