የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ, Government Organization, Butajira city, Butajira.

በየጣቢያው ድምጽ የተሰጠበት መረጃ በምርጫ ክልሎች ላይ እየተደመረ ነው - ቦርዱ  ግንቦት 26፣ 2018  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በየጣቢያው ድምጽ የተሰጠበት መረጃ ወደ ምርጫ ክልሎች...
03/06/2026

በየጣቢያው ድምጽ የተሰጠበት መረጃ በምርጫ ክልሎች ላይ እየተደመረ ነው - ቦርዱ

ግንቦት 26፣ 2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በየጣቢያው ድምጽ የተሰጠበት መረጃ ወደ ምርጫ ክልሎች ሄዶ የማዳመር ስራ እየተሰራ ይገኛል አለ።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት፤ በትናንትናው ዕለት የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ አጠናቅቀው በምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ለጥፈዋል።

በየጣቢያው ድምጽ የተሰጠበት መረጃ ወደ ምርጫ ክልሎች ሄዶ የማዳመር ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ቀደም ብለው ድምጽ አሰጣጥ ሂደት የጨረሱና የድምጽ ቆጠራ አጠናቀው ውጤት የለጠፉ ጣቢያዎች ሰነዶችን ወደ ምርጫ ክልል የላኩት ሰነድ ወደ ማዕከል ጉዞ መጀመሩን ጠቅሰዋል።

ውጤቱን የማዳመር ስራ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸው፤ በቦርዱ በተዘጋጁ ቅጾች በአግባቡ ተሞልተውና ተዘጋጅተው መምጣት አለባቸው ብለዋል።

በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ድምጽ ከተሰጠ በኋላ በውጤት ማመሳከሪያና ማሳወቂያ ቅጽ ውጤቱ ይሞላል፤ እያንዳንዱ ዕጩ ያገኘው ውጤት በቁጥር ይገለጻል ሲሉ አብራርተዋል።

03/06/2026
የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ ስራንና የደረጃ ''ሀ'' እና ''ለ'' ግብር አከፋፈል አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።በበጀት ዓመቱ ቀሪ ጊዜያት የገ...
03/06/2026

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ ስራንና የደረጃ ''ሀ'' እና ''ለ'' ግብር አከፋፈል አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።

በበጀት ዓመቱ ቀሪ ጊዜያት የገቢ አሰባሰቡን በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ ስራንና የደረጃ ''ሀ'' እና ''ለ'' ግብር አከፋፈል አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብድልቃድር ኢማም ሎላሶ በመሩት በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ በበጀት ዓመቱ በቀሪ ጊዜያት የገቢ አሰባሰቡን በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት ያለምንም መዘናጋት ቀን ከሌት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በመደበኛና በማዘጋጃ ቤት ዘርፍ እስካሁን የተከናወኑ የገቢ አፈጻጸሞች የተገመገሙ ሲሆን የከተማውን የወጪ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በቀጣይ በቀሪ ቀናት የደረጃ ''ሀ'' እና የደረጃ ''ለ'' ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንዲከፍሉ በማድረግ፣ የኦዲት ውዝፍ ያለባቸውን በልዩ ሁኔታ በመለየት፣ የደረሰኝ ቁጥጥር ስራን በማጠናከርና ወርሃዊ ሪፖርቶችን በትክክለኛው ጊዜና ጥራት በማደራጀት የተሸላ የገቢ አሰባሰብ ስራን ለመስራት እርብርብ ይደረጋል ብለዋል።

የከተማችን የልማት ፍላጎት እንዲሟላ ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብሩን በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታውን መወጣት እንዳለበት ጠቁመው በዚህም መሰረት የደረጃ "ሀ" ሁለተኛ ዙር (1/4) ግብር ከፋዮችና የደረጃ "ለ" ሶስተኛ ዙር (1/4) ግብር ከፋዮች እስከ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም ድረስ ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በኋላ ለሚመጡ ግብር ከፋዮች ወለድና አስተዳደራዊ ቅጣት የሚሰላ መሆኑን አውቀው ህጋዊ ግዴታቸውን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

03/06/2026

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጋችሁት 7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ልትኮሩ ይገባል።

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ታዛቢዎች ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ

03/06/2026

የሀገርን ዘላቂ ልማት በራስ አቅም ለመደገፍ ደረሰኝ የመስጠትና የመቀበል ባህልን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑ ቢታመንም አሁንም በገበያ የሚታየው ህገወጥ የደረሰኝ አጠቃቀም በታክስ ስርአቱ ላይ ክፍተት ፈጥሯል።

ይሁንና ይህንን በደረሰኝ አጠቃቀም ላይ የሚታየው ክፍተት እንዳለ ሆኖ በታክስ ስርአቱ ላይ የሚደረጉ ማሻሻያና የቁጥጥር ስራዎች ውጤት ማስመዝገባቸው አልቀረም።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት 10 ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8 ቢሊየን ጭማሪ አሳይቷል።

ለዚህም የ45 ሺ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ መግባት እና በህግ ተላላፊዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተገልጿል።

.1_ይጠብቁ

.1 #ገቢ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ Central Ethiopia Region Bureau of Agriculture Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau
👇👇👇👇👇
👉የፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562204634443
👉የቲክቶክ ገፅ
https://www.tiktok.com/.ethiopia4?_t=ZM-8ynTRPSsANR&_r=1
👉የዩቲዩብ ገፅ (https://youtube.com/?si=ELneJRp2Lj7xJ8GK
👉ኢንስታገራም
https://www.instagram.com/centralethiopiarevenue?igsh=cmY4a2g5dnAxcmQ3

👉በሬዲዮ ፕሮግራም በDebub Fm100.9 ሬዲዮ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ8:40_9:00 ይከታተሉን
👉 ይደውሉ
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

"የተከበሩ ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩት እና 73 አባላት የያዘውን የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ፣ ለዴሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎት እና አስተዋፅኦ የላቀ ምስጋናችንን እና...
03/06/2026

"የተከበሩ ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩት እና 73 አባላት የያዘውን የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ፣ ለዴሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎት እና አስተዋፅኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም በተጠናቀቀበት ማግስት የልማት ፕሮጀክቶችን ማስመረቅ መቻል የኢትዮጵያን የእድገት ጉዞ አመላካች ነው:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ግንቦት 26/2...
03/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም በተጠናቀቀበት ማግስት የልማት ፕሮጀክቶችን ማስመረቅ መቻል የኢትዮጵያን የእድገት ጉዞ አመላካች ነው:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ግንቦት 26/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የ2018 ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም በተጠናቀቀበት ማግስት ፕሮጀክት ማስመረቅ መቻል የኢትዮጵያን የእድገት ጉዞ አመላካች ነው ብለዋል።

ከምርጫ በፊትም ሆነ ከምርጫ በኋላ የልማት ፕሮጀክቶችን በማስመረቅ ለአገልግሎት ማብቃት ለልማት ስራ ያለንን ቁርጠኛ አቋም አመላካች መሆኑን ያሳያል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።

በወራቤ ከተማ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል በአነስተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል።

የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋት በአነስተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚነትን ማሳደግ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በሌላ በኩል በከተማው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመሩ የሀገር ግንባታ አንድ አካል ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የምንገነባው ሲስተም በመሆኑ የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ረገድ የሚኖረው አበርክቶ ከፍተኛ ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶች ለምረቃ እንደሚበቁም ጠቅሰዋል።

በክልሉ አንድ ብቻ የነበረውን የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስከ ሰኔ 11 /2018 ድረስ ይህን አሀዝ ወደ 7 ለማሳደግ እየተሰራ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።

በክልሉ እስከ ሰኔ 30 ባለው ጊዜ ደግሞ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ቁጥር እስከ 17 ለማድረስ ይሰራል ብለዋል።

በልማት፣ በሰላም እንዲሁም በትውልድ ግንባታ ላይ ጠንክረን በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ በጊዜ የለኝም መንፈስ መትጋት ይኖርበታል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

የወራቤ ከተማ በከፍተኛ የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት መንግስት አገልግሎቶችን ለማሻሻል የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እየተገበረ ነው ብለዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተግባራዊ ስለመሆኑም ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።

የንግድ የገቢ እንዲሁም የጤናውን መስክ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት ስለመቻሉም አቶ ዘይኔ አብራርተዋል።

በዞኑ 37 ከሰንበት እስከ ሰንበት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ማዕከላት መኖራቸውን ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል በበኩላቸው በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከል የከተማውን ማህበረሰብ የአገልግሎት አሰጣጥ የተቀላጠፈ እንዲሆን የሚያስችል ነው ብለዋል።

ባለፉት የለውጥ አመታት ከተማዋን የንግድ እና የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑም ከንቲባው አመላክተዋል።

ወራቤን ማለፊያ ብቻ ሳትሆን ማረፊያ ማድረግ በሚል መሪ ሀሳብ የከተማዋን የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የማስፋፋት ስራ ትኩረት እንደተሰጠው ከንቲባው ጠቁመዋል።

የወራቤ ከተማ ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል ለህብረተሰቡ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማቅረብ የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት እንደሚያስችልም አብራርተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ (ግንቦት 26/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣ...
03/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

(ግንቦት 26/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

በማዕከሉ በ6ተቋማት 20 አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተመላክቷል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣
የክልል እና የስልጤ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የክ መ ኮ

በክልላችን ለምትገኙ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች በሙሉ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ መሠረት ማናቸውም የደረጃ 'ለ' እና 'ሀ' ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን 1/4ኛ ወይም 25...
03/06/2026

በክልላችን ለምትገኙ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች በሙሉ

በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ መሠረት ማናቸውም የደረጃ 'ለ' እና 'ሀ' ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን 1/4ኛ ወይም 25% ቅድመ ግብር በየሩብ ዓመቱ መክፈል እንዳለባቸው ይታወቃል።

በዚሁ መሠረት የክፍያ ጊዜው የደረሰ በመሆኑ የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች የ3ኛ ዙር 1/4ኛ (25%) ቅድመ ግብር የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮች የ2ኛ ዙር 1/4ኛ (25%) ቅድመ ግብር ከግንቦት 01 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መክፈል ይጠበቅባቸዋል።

ስለሆነም የተከበራችሁ የከተማችን ግብር ከፋዮች የተሰጣችሁን የጊዜ ገደብ በመጠቀም በወቅቱ የሚጠበቅባችሁን የቅድመ ግብር ክፍያ በመፈጸም ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ያሳስባል።

ያስታውሱ ግብርን በወቅቱ መክፈል የልማት አርበኝነት ነው!!!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ!!

02/06/2026

Address

Butajira City
Butajira

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share