Ethiopia Senator አዲስአበባ

Ethiopia Senator አዲስአበባ ሁለንተናዊ ለውጥ፣ ለሀገራችን ብልፅግና

አስደንጋጭ የሕግ ጥሰት በሻሸመኔ ! 🥹😢 :  ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሻሸመኔ ከተማ በቅንጦት ሰርግ ደምቃ ነበር ።  በዚህ ሰርግ  የቅንጦት መኪናዎች ፣ ታላላቅ ፌስቲቫሎች ታይተውበታል ። ነ...
12/11/2025

አስደንጋጭ የሕግ ጥሰት በሻሸመኔ ! 🥹😢

: ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሻሸመኔ ከተማ በቅንጦት ሰርግ ደምቃ ነበር ። በዚህ ሰርግ የቅንጦት መኪናዎች ፣ ታላላቅ ፌስቲቫሎች ታይተውበታል ። ነገር ግን አንድ የሰርጉ ተሳታፊ የሻሼን ድባብ ረብሾታል ።

የከተማዋ መሀል አደባባይ (Town Square) ላይ በአደባባይ ሽጉጥ መዝዞ በርካታ ጥይቶችን አርከፍክፏል ። በአካባቢው የነበሩ ሰላማዊ ነዋሪዎችን ክፉኛ አስደንግጧል።ይህ አስደንጋጭ እና ትዕቢት የተሞላበት የሕግ ጥሰት ብዙዎችን አስደንግጧል ፣ አስቆጥቷል ።

በጠራራ ፀሐይ እንዲህ አይነቱ የሕግ ጥሰት እና ስርአት አልበኝነት እንዴት ሊፈፀም ቻለ? በማለት ጥያቄ ያነሱም አሉ። የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር እንዲህ ዓይነቱ ልቅ የሕግ ጥሰት ተደጋግሞ እንዳይከሰት ምን ዓይነት አስቸኳይ እርምጃ ይወስዳል?

* ይህ ድርጊት ለሕዝብ ደኅንነት እና ለሕግ የበላይነት ስላለው ክብር ምን ዓይነት መልእክት ያስተላልፋል?
ሕግን ማክበር የሁላችንም ግዴታ ነው! ከሕግ በላይ ማንም የለም! ግንዛቤን እናሳድግ!

ይህ ነገር በእውነቱ ትክክል ነው ብለው ያምናሉ ?ሀሳባችሁን አካፍሉን ?

 #በኢትዮጵያ ዉስጥ በ21ኛዉ ክፍሌ ዘመን የማንንም የብሔርና የሐይማኖት የበላይነት ቀይ ምንጣፍ አንጥፎ ሪቫን ቆርጦ የሚቀበል ህዝብ የለም stop thinking old, yesterday is ...
11/11/2025

#በኢትዮጵያ ዉስጥ በ21ኛዉ ክፍሌ ዘመን የማንንም የብሔርና የሐይማኖት የበላይነት ቀይ ምንጣፍ አንጥፎ ሪቫን ቆርጦ የሚቀበል ህዝብ የለም stop thinking old, yesterday is not today. ከጫካ አስተሳሰብ ወተህ በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ዉስጥ ሆነህ ዝቅ በማለት ከሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ተዋህደህ ተግባብተህና አንድነትን ፈጥረህ በፍቅር ብትኖር ይሻልሀል፡፡...

ጎፈሬ አበጥረህና ሹሩባ ተሰርተህ ጠብመ*ንጃ ታጥቀህ ጫካ ስለገባህ የምታሰፍነዉ ሰላምና ዲሞክራሲ የለም የምታበለፅገዉ ህዝብም አይኖርም... በሞኝነት እራስን በራስ ከማጥፋት ዉጭ እንዲህ ዓይነት አካሄድ ፋሽኑ ካለፈ ትንሽ ሰንበትበት ብሏል ነቃ በል ጎበዝ ፋኖና ሸኔ መሆን ከኢትዮጵያዊነት አይበልጥም አርፈህ ተደመር ለሀገርቱ ጠላቶች መግብያ ቀዳዳና መጋለቢያ ፈረስ አትሁን።

የሶሪያን አማጺያንን በመምራት ባሻር አል አሳድን ከሥልጣን ያስወገዱት አሕመድ አል ሻራ ወደ መሪነት ከመምጣታቸው በፊት አሜሪካ ስማቸውን በዓለም አቀፍ የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ አስገብው ነበ...
11/11/2025

የሶሪያን አማጺያንን በመምራት ባሻር አል አሳድን ከሥልጣን ያስወገዱት አሕመድ አል ሻራ ወደ መሪነት ከመምጣታቸው በፊት አሜሪካ ስማቸውን በዓለም አቀፍ የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ አስገብው ነበር።
በዚህም አል ሻራን ለመያዝ የሚያስችል መረጃ ለሰጠ የ10 ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ሽልማት አዘጋጅታ የነበረችው አሜሪካ ከወራት በፊት ሁሉን እርግፍ አድርጋ በመተው ከአዲሱ የሶሪያ መሪ ጋር ወዳጅነቷን አጠናክራለች።
የቀድሞ እስላማዊ ታጣቂ ቡድን መሪ አል ሻራ ከምዕራባውያን ጋር ሆድና ጀርባ የነበሩትን ባሻር አል አሳድን ከሥልጣን ካስወገደ ከ11 ወራት በኋላ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋይት ሐውስ ውስጥ ሞቅ ያለ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በአቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ እና አቶ ሽመልስ ቶማስ ላይ ክስ መመስረቱ ተገለጸ።የቀድሞው የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ  አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ4 የተለያዩ መዝገቦችና በ11 ተደራራቢ ክሶች እንዲ...
10/11/2025

በአቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ እና አቶ ሽመልስ ቶማስ ላይ ክስ መመስረቱ ተገለጸ።

የቀድሞው የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ4 የተለያዩ መዝገቦችና በ11 ተደራራቢ ክሶች እንዲሁም የፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ሽመልስ ቶማስ ላይም በ3 መዝገቦችና በ7 ተደራራቢ ክሶች ማለትም ፦
- ስልጣንን አላግባብ በመገልገል፣
- የመንግስት ስራዎችን በማይመች አኳሗን በመምራት፣
- በህገ-ወጥ መሳሪያዎች ዝውውር፣
- በህገ-ወጥ ኮንትሮባንድ ንግድ፣
- በህገ ወጥ የፖሊስ ማዕረግ አሰጣጥ እና በሌሎች ወንጀሎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የክልሉ ፍትሕ ቢሮ አሳውቋል።

በኢፌዴሪ የፍትህ ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ዐቃብያነህግ የሚታዩ ክሶችንም በተመለከተ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንና በግለሰብ እጅ እንዲያዙ የማይፈቀዱ የመገናኛና የጦር መሳሪያዎችን ይዞ የመገኘትና ተያያዥ ጉዳዮችም ጋር ተያይዞ ምርመራ መጠናቀቁን አመልክቷል።

ሀቅ አትቀበርም ‼️ ቀን ግን ትጠብቃለች ‼️ፍትህ ልትሰፍን ነው! እውነት ልትገለፅ ነው! በጋዜጠኛ እና በተንቀሳሳሹ ቤተ-መጽሐፍ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) አሟሟት ዙሪያ አዲስ የተጀመረው ምርመ...
09/11/2025

ሀቅ አትቀበርም ‼️ ቀን ግን ትጠብቃለች ‼️

ፍትህ ልትሰፍን ነው! እውነት ልትገለፅ ነው!

በጋዜጠኛ እና በተንቀሳሳሹ ቤተ-መጽሐፍ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) አሟሟት ዙሪያ አዲስ የተጀመረው ምርመራ ፍሬ አፈራ!

ጉርሻ ፔጅ እና ሌሎች የገነነን ሞት በሚመለከት "ራሱን አላጠፋም!" በሚል ለፌዴራል ፖሊስ እንደገና ምርመራ እንዲደረግ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ፣ ባለፈው ሐሙስ ዕለት ሦስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተረጋግጧል!

በፌዴራል ፖሊስ የተያዙት ተጠርጣሪዎች፦

* ባለቤቱ ወ/ሮ አስቴር አየለ
* አቶ ይታየው (ምትኬ)
* የዋካና ሆቴል ባለቤት

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ትላንት አርብ ፍርድ ቤት ቀርበው ለተጨማሪ ምርመራ የ10 ቀን ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል።

ይህ ትልቅ የፍትህ ሥራ እውን እንዲሆን ላደረጉት ሁሉ ታላቅ ምስጋና ይገባቸዋል!

* ፌዴራል ፖሊስ - ለሠሩት በጎ ተግባር!
* ጋዜጠኛ አርአያ
* ጋዜጠኛ ሰይድ ኪያር
* ተሰፉ ነዳ
* እንዲሁም ሁሌም የሊብሮ ሞት የሚያንገበግባቸው እና ድምፃቸውን ያሰሙ የገነነ መኩሪያ አድናቂዎች በሙሉ!

እናንተ ድምፅ አሰማችሁ! ፍትህም መሥራት ጀመረች!

ወደፊት በፍርድ ሂደቱ ዙሪያ ያሉ መረጃዎችን ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።

ገነነ መኩሪያ ራሱን አላጠፋም! አዎ አላጠፋም!

የእውነት ብርሃን ይግለጥ!

ጉርሻ ፔጅ እንደዘገበው
🙏🙏🙏

አቶ ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ዓላማ ያደረገ በአፋር ክልል በኩል የሚደረገውን እንቅስቃሴ በጥብቅ ኮንነዋል። እንቅስቃሴው በኤርትራ መንግሥት በሻዕቢያ ትዕዛዝ የሚፈጸ...
08/11/2025

አቶ ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ዓላማ ያደረገ በአፋር ክልል በኩል የሚደረገውን እንቅስቃሴ በጥብቅ ኮንነዋል። እንቅስቃሴው በኤርትራ መንግሥት በሻዕቢያ ትዕዛዝ የሚፈጸም "የኋላቀሩ ቡድን" አጀንዳ ነው ሲሉም ከሰዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "ኋላቀሩ ቡድኑ" የፕሪቶሪያን ስምምነት ለመናድ የተለያዩ ማነሳሳቶችን ቢሞክርም የፌደራል መንግሥት ምላሽ ሳይሰጥ በመቆየቱ አሁን ደግሞ የፌደራል መንግስትን ወደ ግጭት ለመሳብ በማሰብ በዓፋር በኩል የጦርነት ቅስቀሳዎችን እያደረገ እንደሆነ አስታውቀዋል። ይህንን "የሻዕቢያ አጀንዳ" ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ዋና ፈጻሚዎች እና ተጠያቂዎች ፍስሃ ማንጁስ እና ዮሃንስ መዲድ መሆናቸውን ጠቁመው እንቅስቃሴውን እንዲያስቆሙም ጥሪ አቅርበዋል።

ኋላቀሩ ቡድን የአፋርን መንገድ በመዝጋት እና የዓፋርን ህዝብ በማነሳሳት ይህንን ሁኔታ እንደ መደራደሪያ ለመጠቀም እያሰበ ነው ቢሆንም "ይህ በፍጹም ሊሆን አይችልም" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ኃይሎች (TDF እና TPF) ትግራይን ከፌደራል መንግሥት ጋር የሚያጋጭ ምንም ዓይነት አጀንዳ እንደሌላቸው በግልጽ አስቀምጠዋል። " የትግራይ ሰራዊት (TDF እና TPF) በምንም ይሁን በምን ትግራይ ከፌደራል ጋር የሚያጋጭ ምንም ዓይነት አጀንዳ የላትም ሊኖራችሁም አይገባም። ስለዚህ የኋላቀሩ ቡድን እና የሻዕቢያ አጀንዳ መጠቀሚያ ላለመሆን ታገሉ" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ አክለው ትርፋማ የሚሆነው አጀንዳ የፕሪቶሪያን ስምምነት መጠበቅ መሆኑን አሳስበዋል። "ትርፋማ አጀንዳ ያለው ሰው በፕሪቶሪያ ሶስተኛ አመት ላይ ጥያቄያችን ወዴት ደረሰ?' ብሎ ይጠይቃል። ለጊዜውም ቢሆን የምያዋጣን መንገድ ስምምነቱ ነው" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው መልእክታቸውን ሲያጠቃልሉ የህወሓት ቡድን በመወንጀል "አሽከርነት ይበቃችኋል!" የሚል አጽንዖት ያለውን መልዕክት አስተላልፈዋል።

በጠዋቱ የተሰማ ሰበር ዜና‼️ጀግናው የአየር ሀይላችን በአፋር ክልል መጋሎ አከባቢ ወረራ የፈፀሙ የሻዕቢያና የህወሓት ወራሪ ወደ አፋር ይዘውት የገቡ የጦር መሳሪያ ፣ታንክና ተሳቢ የጦር መኪኖ...
07/11/2025

በጠዋቱ የተሰማ ሰበር ዜና‼️

ጀግናው የአየር ሀይላችን በአፋር ክልል መጋሎ አከባቢ ወረራ የፈፀሙ የሻዕቢያና የህወሓት ወራሪ ወደ አፋር ይዘውት የገቡ የጦር መሳሪያ ፣ታንክና ተሳቢ የጦር መኪኖች በድሮን ወደ አመድነት ቀይረውቷል።

የአየር ሀይላችን በተጠና መንገድ የጦር መካዝኖችን ብቻ ነው ጥቃት የፈፀመብት። ለወረራ የመጡት የታጠቁ ቡድኖች ላይ ጥቃት ከማድረስ ተቆጥብዋል።
ወራሪው ቡድን ሻዕቢያና ተላላኪዎች ፍርጠጣ ላይ ይገኛሉ። ከዚህ በኃላ ድጋሚ ትንኮሳ የሚያደርስ ከሆነ የእጁን ያገኛል። ኢትዮጵያ ለወራሪዎቿና ለጠላቶቿ ፍፁም የማትመች ሀገር ነች።

ይህ የለሊቱ መሳሪያቸዉን የማዉደም እርምጃ ለሁለቱም ጋላቢና ተጋላቢ ሀይላት ጠንከር ያለ መልእክት የሚያስተላልፍ ታላቅና ታሪካዊ ግዳጅ ነዉ።

ኢትዮጵያን የነካ
የለውም በረካ!!!

ሰበር ዜናየአፋር ክልል ሚሊሻዎች ወደ ክልላቸው ሰብረው በገቡ የሕውሓት ታጣቂዎች ላይ የመልሶ ማጥቃት መክፈታቸው ተሰምቷል፡፡ ሚሊሻዎቹ ወደ ግንባር ሲንቀሳቀሱ የሚያስ ተንቀሳቃሽ ምስል በማኅበ...
06/11/2025

ሰበር ዜና

የአፋር ክልል ሚሊሻዎች ወደ ክልላቸው ሰብረው በገቡ የሕውሓት ታጣቂዎች ላይ የመልሶ ማጥቃት መክፈታቸው ተሰምቷል፡፡ ሚሊሻዎቹ ወደ ግንባር ሲንቀሳቀሱ የሚያስ ተንቀሳቃሽ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተራጭቷል፡፡

05/11/2025

ሰበር ዜና🇪🇹
ዛሬ አመሻሽ ላይ አፋር ክልል ጦርነት ተቀስቅሷል ሻቢያ እና ህውሃት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ፀብ እየጫሩ ነው።

ሰበር ዜና‼የህዳር 11 ህዝባዊ  ሰልፍ ከአስተባባሪ ኮሚቴ በኩል የተሰጠ መግለጫ።የግንዛቤው መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል።👇👇👇👇👇👇👇**የመስቃን ማንነት የህልውና አደጋ ልብ በሉትየመስቃን ...
04/11/2025

ሰበር ዜና‼
የህዳር 11 ህዝባዊ ሰልፍ ከአስተባባሪ ኮሚቴ በኩል የተሰጠ መግለጫ።

የግንዛቤው መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል።
👇👇👇👇👇👇👇
**የመስቃን ማንነት የህልውና አደጋ ልብ በሉት
የመስቃን ማህበረሰብ እየደረሰበት ያለው የተባበረና ስልታዊ የማንነት የህልውና አደጋ እጅግ ከባድና ታሪክ ይቅር የማይለው ተግባር ነው።

**የመስቃን ቤተ ጉራጌ ህዝብ በታሪክ የዋህ፣ ፈጣሪን የሚፈራ፣ ማንንም የማይነካ፣ እጅግ ታጋሽና ለማንነቱ ሟች እንደሆነ ይነገራል። በዚህም የተነሳ አንዳንድ ጅሎች የተኛውን አንበሳ እንደድመት ቆጥረውት፣ ሊዘባበቱበትና ሚስትህን አበድረኝ በሚመስል ቀልድ ጨዋታ ከጀመሩ ሰንበትበት ብሎዋል።

**የመስቃን ህዝብም በየጊዜው በተለያየ መዋቅር ደረጃ በተለያዩ ፅንፈኛና ሴረኛ የፖለቲካ ሀይሎች የፖለቲካ ስልጣንና የፖለቲካ ቋንቋ ሽፋን አድርገው በእቅድ ሲያደርሱበት የነበረውን በደል በቸልተኝነትና በቅንነት ሲያልፍ መምጣቱ ዛሬ ከባድ የማንነት የህልውና አደጋ ተደቅኖበታል። አቤቱታውና ጩኸቱ አድማጭ አጥቷል።

**በዚህም ለዘላለም አፍኖት አውቆም በይቅርታ ሳያውቅም በቸልተኝነት ያሳለፈውን የመስቃን ማንነት ህልውና አደጋ ስልቶች፣ ዛሬ ገብቶትና ተረድቶ ለትግል ቆርጦ ተነስቷል ቢዘገይም ጥሩ ነው።

**የማንነት ህልውና አደጋ ማለት ምን ማለት ነው?
​​የማንነት ህልውና ማለት አንድ ሰው፣ ቡድን፣ ወይም ህዝብ የሚመሰረትበት መሰረታዊ ማንነት ለዘላለም ፀንቶ እራሱን ጠብቆ የመኖርና የመቀጠል አቅምና አቋም ማለት ሲሆን በፖለቲካዊ አውድም የማንነት ህልውና ማለት አንድ የብሔር ወይም የጎሳ ማንነት በፖለቲካዊ፣ በህጋዊና በማኅበራዊ ስርዓቶች ውስጥ ሙሉ መብቱና ቦታው ተረጋግጦ፣ እንዳይጠፋና እንዳይዋጥ የመኖር ዋስትና ማለት ነው።

እነዚህም የህልውና መሠረቶች የሚከተሉትን ያካትታል።
1. በህይወት ​የመኖር:፦ በአካል የመኖር መብትና ሁኔታ።
2. ​ራስን የማወቅ፦ ማንነታቸውን የሚገልፅ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ እምነት እና እሴቶችን የማወቅ፣የመጠበቅና የማስቀጠል ሁኔታ።
3. ​ቀጣይነት፦ ማንነቱን፣ ቅርሱን፣ ባህሉን፣ ቋንቋውን፣ እሴቶቹንና እምነቶቹን ከትውልድ ወደ ትውልድ የመተላለፍና የመቀጠል ሂደት ሳይቋረጥ የማቆየት ሁኔታ ናቸው።

**​የማንነት የህልውና አደጋ ማለት!!
​ይህ ጽንሰ-ሐሳብ ከላይ እንደተመለከተው፣ የማንነት ህልውናን ሊያጠፋ የሚችል ወይም ሊያጠፋው የሚችል ኃይል ወይም ሂደት ማለት ሲሆን።።

በፖለቲካዊ ዓለም ውስጥ ይህ አደጋ የሚከተሉትን አደገኛ ስልቶች ያካትታል፦

1. የ​ዘር ማጥፋት (Genocide)፦ በአካላዊ ጥቃት ወይም በስልታዊ ግድያ የአንድን ማህበረሰብ/ቡድን ማንነቱን ለማጥፋት መሞከር።

2. የ​ባህል ቋንቋ ጥቃት፦ የህዝቡን ቋንቋ በትምህርትና በአስተዳደር እንዳይለማና ውጤታማ እንዳይሆን ከማድረግ ጀምሮ የባህልና የታሪክ አጻጻፍን በማዛባት፣ በመበረዝ፣ ወይም በማፈራረስ ማንነቱን ከውስጥ ማዳከም።

3. ​ማፈናቀል፦ በተጠናና በስልት በታቀደ የፖለቲካ ሴራ አጀንዳ በመፍጠር ከጎረቤቶች ጋር ግጭት በማስነሳት የህዝቡን የአሰፋፈር መሠረት በማናጋት፣ በኃይል በማፈናቀል እና ከተፈጥሯዊ መገኛ በማራቅ የጎሳ አንድነትንና የጋራ ማንነትና ህብረት ማፍረስ።

4. ​ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማግለል፦ የማንነት ቡድኑን በፖለቲካዊ ውሳኔዎችና በኢኮኖሚያዊ ሀብት ክፍፍል በመግፋትና በማግለል ቀስ በቀስ ትግሉ እንዲዳከም እና ተስፋ ቆርጦ ማንነቱ እንዲጠፋ ማድረግ።

​** ማንነት የማጥፋት ስልቶች
​በፖለቲካ ዓለም ውስጥ አንድ ማንነት ሌላኛውን ማንነት ለማጥፋት ወይም ለማዳከም የሚከተላቸው ስልቶች
እና ተጎጂው ማንነት የሚከተላቸው የመከላከል ስልቶች አሉ።

** የማጥፋት ስልቶች:-
​እነዚህ ስልቶች የተጎጂውን ማንነት በዝግታም ይሁን በፍጥነት ለማዳከም የሚያገለግሉ የፖለቲካ መሳሪያዎች ናቸው፦

1) ​የታሪክ ትርክት ቁጥጥር ማዛባት
ይህ ​ስልት የሌላውን ማንነት ታሪክ ዝቅ በማድረግ፣ ከፍ በማድረግ ወይም በማጥፋት ተጎጂው ማንነት በስነልቦና እንዲሰበር ማስገደድ። ​የዚህ ስልት ፖለቲካዊ ዓላማ ተጎጂውን ማንነት ያለፈውን ክብሩን እንዲጠራጠር፣ እንዳያስታውስና እንዲረሳ፣ እንዲጠላና የወደፊቱ ተስፋውን እንዲደበዝዝና እንዲያጣ ማድረግ ነው።

2) ​የሀብትና የመሬትና የግዛቱን የመቆጣጣር ስልት
ይህ ​ስልት የህዝቡን የኢኮኖሚ መሠረት የሆኑትን ሀብቶች፣መሬቶች እና ግዛቶች በህግ ወይም በኃይል በመቆጣጠር ህዝቡን በኢኮኖሚ ጥገኝነት ውስጥ ማስገባት።

የዚህ ስልት ​የፖለቲካ ዓላማው ህዝቡ ለኑሮ ሲል ማንነቱን እንዲተውና እንዲረሳ በሂደትም ለመዋጥ ዝግጁ እንዲሆን ለገዥው ኃይል እንዲንበረከክ ለማድረግ ነው።

​የአስተዳደርና የህግ የበላይነትን መጠቀም ሽፋን
​ስልታዊ በሆነ መንገድ የህዝቡን ማንነት፣መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረጉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች በሙሉ በሽብር መልክ በመፈረጅና፣ የተሳሳተ ፖለቲካዊ ትርጓሜ በመስጠትና በማሰጠት፣ ቁልፍና ዋናዋና የአመራር ቦታዎች እና የፖሊስ፣ የደህንነትና የፍትህ አካላትና ተቋማት በአንዱ ጎሳ በማስያዝና በመቆጣጠር በአንዱ ተበዳዩ የጎሳ ማንነት ላይ ኢላማ በማድረግ አላግባብ መጠቀም።

የዚህ ስልት ​የፖለቲካ ዓላማ ተቃውሞን በሽብር መልክ ፈርጆ በዚህ ሰበብ ንፁሃን በፀጥታ ሀይል በጭካኔ በመግደል፣ በማስርና በማሳደድ ተቃውሞውን በአፈና ማስቆም እና ህዝቡን በፍርሃት አስገድዶ መግዛት ነው።

3) ​የህዝቡ የውስጥ አንድነት የመከፋፈል​ ስልት
በተጎጂው ማንነት ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ንዑስ ቡድኖች (በሃይማኖት፣በፖለቲካ በአመለካከት፣ በኑሮ ደረጃ፣ በጥቅም፣ በቤተሰብ፣ በቆዩ የቂምና በቀል፣በጎሳ፣ በውሸት መረጃ፣ በተሳሳተ ፕሮፓጋንዳ እና በመሣሠሉ የልዩነት ነጥቦች) በመለየትና በማጋጨት ህብረታችን ማፍረስና አንድ ያለን የጋራ ማንነታችን ጠያቂ ትውልድ እንዳይፈጠርና ትግሉ ለማዳከም ታስቦ የሚፈፀም ተግባር ነው። የዚህን ስልት
​የፖለቲካ ዓላማ ህዝቡ ለጋራ ማንነቱና ጥቅሙ የተደራጀ ተቃውሞ እንዳያነሳ ለማድረግ ነው።

** ህዝቡ የውስጥ አንድነት ካገኘና ከተደራጀ ያለፈውንና ያጣውን በሚገባ ስለሚረዳ ከትግል አይመለስም ለነገም ቢሆን መብቱንና ማንነቱን አያስነካም የሚል አደገኛ ስጋት በማሰብ ነው። ለዚህ አላማ ማሳኪያ ይሆኑ ዘንድ የህዝቡ የራሱ አብራክ የሆኑ በማንነታቸው የሚያፍሩ፣ ሆዳምና የስልጣን ጥመኛ አላማቢሶች፣ ፈሪ እኔ ታሪክ አልባ የሆኑ ባንዳውች ይጠቀማሉ።

​** መስቃን የተጋረጠበት የህልውና ስጋት እንዲከላከል ሰፊ ግንዛቤዎች ሊወስድ ይገባል እነሱም፦

1. ​የማንነት መልሶ ግንባታና ንቃተ ህሊና ​በተመለከተ፦ የህዝቡን እውነተኛ ታሪክ፣ ባህልና እሴቶች፣ በስርዓተ-ትምህርት፣ በኪነ-ጥበብ፣ በማህበራዊ አደረጃጀቶች፣ በጎሳ ስብሰባዎች፣ በሽምግልና ስርዓት፣ በህብረት ስራ፣ በወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች እና በግል ውይይቶች ህዝቡ በማንነቱና በመብቱ ያለምንም ፍርሃትና ስጋት በመረጃ ተመስርቶ ሞጋች እንዲሆን በግልፅም በስውርም ማስተዋወቅ፣ ማንቃትና ማስተማር አንዱ ስልት ነው። በዚህም ​የህዝቡን የራስን ክብር ማደስ እና የህዝቡን አንድነት በጋራ ማንነት ለማጠናከር አይነተኛ መፍትሔ ነው።

2. ​የህግና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፦
ዓለም አቀፍና ሀገር ውስጥ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተቋማትን በመጠቀም የማንነት ጥቃቶችን ለዓለም እና አገርአቀፉ ማህበረሰብ የተለያዩ መንገዶች በመጠቀም የፖለቲካ ሴረኞች ድብቅና ስልጣንን ሽፋን በማድረግ የአንድ ማህበረሰብ ማንነት ህልውና አደጋ እንደደቀኑ ይፋ ማድረግ እና ህጋዊ ጥበቃን መጠየቅ ነው። የዚህ ስልት አላማ የጥቃት ፈጻሚውን ኃይል በአገር እና በዓለም አቀፍ ህጎች መሠረት ተጠያቂ ለማድረግ ይረዳል የፖለቲካ ሴረኞች ክፋታቸው ማጋለጥ አለበት።።

3. ​የባህላዊና የማኅበራዊ መረቦች ጥበቃ ማድረግ አለበት፣
​የቤተሰብ፣ የጎሳ እና የባለቤትነት መረቦችን በማጠናከር የኃይል መፈናቀል ሲያጋጥም እንኳን ህዝቡ እንዳይበታተን እና ትስስሩ ሳይቋረጥ ሰላማዊ ትግሉ ማቀጣጠል አለበት። የዚህ ስልት አላማ የአካላዊ ኪሳራ ቢኖርም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሕልውናውን ለማስቀጠል የሚረዳ ነው።

** የመስቃን ህዝብ ተወላጅ ሆይ ከዚህ በፊት በችለተኝነት ዝም የተባሉ አካሄዶች ዛሬ ህዝባችን ከባድ አደጋ ውስጥ ከቶታል፣ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የምትገኙ አጠቃላይ ​የመስቃን ተወላጆች፣ ወዳጆችና ዘመዶች በመጪው ህዳር ወር ቀን 11 ላይ ከባድ ህዝባዊ ተቃውሞ ስለሚካሄድ ቀድማችሁ ወደ መስቃን ቡታጅራ እንድትገቡና አጠቃላይ ግንዛቤው እንድትወስዱ ሲል አስተባባሪው ኮሚቴው አሳስቧል።

ክፍል ሁለት ይቀጥላል..
(የህዳር 11 ህዝባዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴዎች)
**መስቃን ቡታጅራ፨

 #የክልላችን ፕሬዝዳንት እንዳሻው ጣሰው ምስራቅ ጉራጌ ሰላም እንዳይሆን የፈለገ የሚያሥመሥሉበት ነጥቦች እና አላማዎች ሚስጥሮች ምንድናቸው? #1- የምስራቅ ጉራጌ ሽማግሌ መናቅ #2- ወጣቶች...
03/11/2025

#የክልላችን ፕሬዝዳንት እንዳሻው ጣሰው ምስራቅ ጉራጌ ሰላም እንዳይሆን የፈለገ የሚያሥመሥሉበት ነጥቦች እና አላማዎች ሚስጥሮች ምንድናቸው?
#1- የምስራቅ ጉራጌ ሽማግሌ መናቅ
#2- ወጣቶችን ያለአግባባብ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በማበር ማሠር
#3- የመስቃን ህዝብ ጥያቄ ማፈን
#4- ከተለያዪ የራሱ ከሆኑ ግለሰቦች ጋር መረጃ መውሰድ
#5- የመስቃንን ማህበረሰብ ለይቶ ማሠር
#6-በመስቃን ቡታጅራ ከተማ ላይ የማይመለከታቸው የራሱ የሆኑ ሰዎችን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ማሣተፍ
#7-አካባቢው ላይ ፈጣን የሰላም አማራጮች እንዳይመጡ ማዘግየት
#8-አጀንዳ ፈብራኪዎችን ከለላ መሥጠት
#9-አንድን ማህበረሰብ ማስፈራራት መናቅ
#-10-ንጉሴ አስረስ ከተባለ አውሬ ጋር አብሮ መስራት
#11-የመስቃን ወጣቶችን እንደ ህወሀት ካድሬ የጦር ወንጀለኛ በማስመሠል ከከተማ ውጪ ማሰር የራሳቸውን የፓሊስ ሀይል በመጠቀም ዳጎስ ያለ አበል በማውጣት እንደ ትልቅ ወንጀለኛ የፌዴራል ከተማ እና የክልል ከተማ በመዘዋወር መፈለግ በምክንያት የህዝብ ብር እንዲባክን ማድረግ
#12-የመስቃን ህዝብ ሊያግዘው አብሮ ሊሠራ ሲያስብ ሲቀርብ ማግለል

ህዳር 11/2018 ከባድ የተቃውሞ ሰልፍ በመስቃን ቡታጅራ ከተማ ታላቅ ጥሪ ተደርጓል።ዝርዝር መረጃው እንደደረሰን የምንገልፅ ይሆናል...ሼር በማድረግ ለመላው ህዝባችን አድርሱ።
25/10/2025

ህዳር 11/2018 ከባድ የተቃውሞ ሰልፍ በመስቃን ቡታጅራ ከተማ ታላቅ ጥሪ ተደርጓል።

ዝርዝር መረጃው እንደደረሰን የምንገልፅ ይሆናል...
ሼር በማድረግ ለመላው ህዝባችን አድርሱ።

Address

Meskan
Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Senator አዲስአበባ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopia Senator አዲስአበባ:

Share