24/10/2025
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህዝቦች መካከል የነበረውን አብሮነት ለማጠናከር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው።
ወ/ሮ ሰብለጸጋ አየለ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መሪ ሀሳብ ወሰን ተሻጋር በጎ ፍቃድ አገልግሎት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተገኝተው አከናወኑ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰብለጸጋ አየለ በሁለቱ ክልሎች መካከል የሚደረገው የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ ስራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትንና እህትማማችነትን የሚያጠናክር ታላቅ የበጎነት ስራ መሆኑን ተገልጿል።
ኃላፊዋ አክለው እንደገለጹት ለተቸገሩ ወገኖቻችን የምንረዳበትና የምናግዝበት ተገባር ከመሆኑ ባሻገር ህብረ ብሄራዊነታችንን የሚያጎለብት፣ የህዝባችንን የስነልቦና አንድነት የሚያጠናክርና የሁለቱን ክልል እህትማማችነት የሚያጠናክር ተግባር ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ በ14 መስኮች በሚከናወነው የክረምት ወራት በጎ ተግባር ላይ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ በማድረግ በቅንጅት ለቀጣይ ትውልድ ለማሸጋገር የሚያግዝ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ከብልጽግና ፓርቲ እሴቶች አንዱ የሆነውን በህዝቦች መካከል መቀራረብን እና መተጋገዝን የማጠናከር መልካም ተግባርን በማስቀጠል እሴቶችና ብዝሃ ሃብቶች አልምተን በመጠቀም ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ መትጋት ይኖርብናል ብለዋል።
በሴቶች ክንፍ መሪነት በክረምት ወራት የተለያዩ በጎ ተግባራት ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል በዚህም በርካታ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ዲሞክራሲና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስዩም ደጉ እንኳን ወደ ኢትዮጵያዊቷ የሰፊ የስንዴ ምርት ባለቤት ወደሆነች የማዕከላዊ ክልል ሀዲያ ዞን በሠላም መጣችሁ በማለት ይህ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ ጉዞ ወንድማማችነትንና እህትማማችነት በማጠናከር አብሮነት እንዲፀና የሚያግዝ ነው ብለዋል።
የከንባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ፀጋነሽ ደመቀ ይህ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሁለቱም ክልሎች መካከል ያለውን አብሮነት ለማጠናከር ያለመ ሲሆን ጎን ለጎን ደግሞ አቅመ ደካሞችን ስንደግፍ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ፓርቲ መሆኑን የሚያሳይ ነው በማለት ገልጸዋል።
በጉዟቸው መረሐ ግብር በክልሉ ከከተማው ለተወጣጡ አቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎንም የሀዲያ ዞን በሴቶች የተከናዘነ የሌማት ትሩፋት ስራ ጉብኝት አድርገዋል።