12/06/2026
"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በፌዴራል ተቋማት የማህበራዊ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች መድረክ ተካሂዷል።
መድረኩ በሀገር ደረጃ በከፍተኛ ስኬት የተጠናቀቀውን የ7ተኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫና የምርጫ ስራዎች አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።
የ7ተኛዉን ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሂደት ለማደናቀፍ የዉስጥና የዉጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ ቢንቀሳቀሱም «ኢትዮጵያ መርጣለች» የሚል ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ውጤታማ ምርጫ መካሄዱ ተገልጿል።
ምርጫው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መልኩ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ተአማኒና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሆኖ መጠናቀቁም ተጠቅሷል።
የማህበራዊ ክላስተር ፖለቲካ ዘርፍ ሰብሳቢ ሽዊት ሻንካ ብልፅግና በምርጫው ሂደት የተለያዩ ግቦችን ይዞ በመንቀሳቀስ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ምርጫ ማካሄድ እንደተቻለ ገልፀዋል።
የምርጫው ስኬት ጊዜ ተወስዶበት በተሰራ የቅድመ ምርጫ ስራና ብቃት ያለው የአመራር ስርዓት በመዘርጋት የተገኘ፣ ከማኒፌስት ትዉዉቅ ጀምሮ የቃል ኪዳን ሰነድ የታደሰበት ሂደት መሆኑን አስገንዝበዋል።
በፓርቲው የፊት መሪነት፣ በደጋፊው ቁርጠኝነት፣ በአባሉ ተጋድሎና በሕዝቡ ይሁንታ የተገኘ የመደመር ዉጤት ማሳያ ድል መሆኑን የማህበራዊ አድርጃጀት ዝርፍ ስብሳቢ ዶክተር ኤርጎጌ ጠቁመዋል።
መድረኩ በምርጫው ሂደት የታዩ ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በጥልቀት በመፈተሽ አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁ የሚሆንበት ነዉ ተብሏል።