ወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት-Boditi Town Prosperity party office

  • Home
  • Ethiopia
  • Boditi
  • ወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት-Boditi Town Prosperity party office

ወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት-Boditi Town Prosperity party office ትጋት ለላቀ ስኬት ! https://t.me/Boditiprosperity

"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በፌዴራል ተቋማት የማህበራዊ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች መድረክ ተካሂዷል።መድረኩ በሀገር ደረጃ በከፍተኛ ስኬት የተጠናቀቀውን የ7ተኛ...
12/06/2026

"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በፌዴራል ተቋማት የማህበራዊ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩ በሀገር ደረጃ በከፍተኛ ስኬት የተጠናቀቀውን የ7ተኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫና የምርጫ ስራዎች አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።

የ7ተኛዉን ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሂደት ለማደናቀፍ የዉስጥና የዉጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ ቢንቀሳቀሱም «ኢትዮጵያ መርጣለች» የሚል ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ውጤታማ ምርጫ መካሄዱ ተገልጿል።

ምርጫው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መልኩ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ተአማኒና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሆኖ መጠናቀቁም ተጠቅሷል።

የማህበራዊ ክላስተር ፖለቲካ ዘርፍ ሰብሳቢ ሽዊት ሻንካ ብልፅግና በምርጫው ሂደት የተለያዩ ግቦችን ይዞ በመንቀሳቀስ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ምርጫ ማካሄድ እንደተቻለ ገልፀዋል።

የምርጫው ስኬት ጊዜ ተወስዶበት በተሰራ የቅድመ ምርጫ ስራና ብቃት ያለው የአመራር ስርዓት በመዘርጋት የተገኘ፣ ከማኒፌስት ትዉዉቅ ጀምሮ የቃል ኪዳን ሰነድ የታደሰበት ሂደት መሆኑን አስገንዝበዋል።

በፓርቲው የፊት መሪነት፣ በደጋፊው ቁርጠኝነት፣ በአባሉ ተጋድሎና በሕዝቡ ይሁንታ የተገኘ የመደመር ዉጤት ማሳያ ድል መሆኑን የማህበራዊ አድርጃጀት ዝርፍ ስብሳቢ ዶክተር ኤርጎጌ ጠቁመዋል።

መድረኩ በምርጫው ሂደት የታዩ ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በጥልቀት በመፈተሽ አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁ የሚሆንበት ነዉ ተብሏል።

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር አዲስ በተመሰረቱ ቀበሌያት ምክር ቤቶች የ13ኛ ስራ ዘመን 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባዔ ተካሄደ ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 05/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደ...
12/06/2026

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር አዲስ በተመሰረቱ ቀበሌያት ምክር ቤቶች የ13ኛ ስራ ዘመን 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባዔ ተካሄደ

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 05/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር አዲስ በተመሰረቱ ቀበሌያት ምክር ቤቶች የ13ኛ ስራ ዘመን 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባዔ ተካሂዷል ።

በነዚህ አዲስ በተመሰረቱ በሁሉም ቀበሌ ምክርቤቶች በተካሄደ የ13ኛ ስራ ዘመን 1ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችም መጽደቅ ችለዋል።

እንደ ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ለህዝብ የሚሰጡ ሁሉም አገልግሎቶች በእነዚህ አዲስ በተመሰረቱ ቀበሌያት ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ተብሏል።

12/06/2026
"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ መካሄድ ጀምሯል ግንቦት 05/2018 ዓ.ም"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት"...
12/06/2026

"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ መካሄድ ጀምሯል

ግንቦት 05/2018 ዓ.ም

"ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩ በሀገር ደረጃ በከፍተኛ ስኬት የተጠናቀቀውን የ7ተኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫና የምርጫ ስራዎች አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።

የ7ተኛዉን ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሂደት ለማደናቀፍ የዉስጥና የዉጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ ቢንቀሳቀሱም «ኢትዮጵያ ትመርጣለች» የሚል ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ውጤታማ ምርጫ መካሄዱ ተገልጿል።

ምርጫው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መልኩ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ተአማኒና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሆኖ መጠናቀቁም ተጠቅሷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ብልፅግና በምርጫው ሂደት መንቲያ ግቦችን ይዞ በመንቀሳቀስ በሁሉም የክልሉ ምርጫ ክልሎች ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ምርጫ ማካሄድ እንደተቻለ ገልፀዋል።

የምርጫው ስኬት ጊዜ ተወስዶበት በተሰራ የቅድመ ምርጫ ስራና ብቃት ያለው የአመራር ስርዓት በመዘርጋት የተገኘ፣ ከማኒፌስቶ ትዉዉቅ ጀምሮ የቃል ኪዳን ሰነድ የታደሰበት የምርጫ ሂደት እንደነበር አስገንዝበዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሁሉም አከባቢዎች ሕብረተሰቡ የቀኑ ፀሐይ፣ የሌሊቱ ብርድና ዉርጭ እንዲሁም ረጃጅም ሰልፎች ሳይበግሩት በድምፁ ዴሞክራሲን ለማፅናት ላሳየው ተጋድሎ ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

በርካታ አዋኪና አዋጊ ፈተናዎች ሳይበግሩት በክልሉ ምርጫው በሰላም ለመጠናቀቁ የአመራሩ፣ የአባላትና የደጋፊዎች ቅንጅት ዉጤት መሆኑንም አስረድተዋል።

በቅድመ ምርጫው ወቅት የታየዉ ፅናትና ከፍተኛ ርብርብ በድህረ ምርጫ ተግባራት ላይ ሊደገም እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላ በክልሉ የምርጫ ስራዎችን በስኬት ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ መደረጉን ተናግረዋል።

በፓርቲው የፊት መሪነት፣ በደጋፊው ቁርጠኝነት፣ በአባሉ ተጋድሎና በሕዝቡ ይሁንታ የተገኘ የመደመር ዉጤት ማሳያ ድል መሆኑን አቶ ገ/መስቀል ጠቁመዋል።

መድረኩ በምርጫው ሂደት የታዩ ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በጥልቀት በመፈተሽ አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁ የሚሆንበት መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የክልሉ መንግስት አስተባባሪ አካላት፣ የክልል ማዕከል፣ የዞንና ሪጂዮ ፖሊሲ ከተሞች ከፍተኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።

ፖለቲካ የማኅበረሰብ ችግሮችን በመፍታት፣ የጋራ ከፍታን ለማረጋገጥ የሚከወን ነው:: ከጊዜያዊ ግብና ከሥልጣን ቆይታ በላይ ነው። ዘላቂ ግብና ዓላማን ያነገበ፣ አቧራን በማስነሣት ከሚገኝ ጊዜያ...
12/06/2026

ፖለቲካ የማኅበረሰብ ችግሮችን በመፍታት፣ የጋራ ከፍታን ለማረጋገጥ የሚከወን ነው:: ከጊዜያዊ ግብና ከሥልጣን ቆይታ በላይ ነው። ዘላቂ ግብና ዓላማን ያነገበ፣ አቧራን በማስነሣት ከሚገኝ ጊዜያዊ ድጋፍ የሚልቅ ነው። ዐሻራን በማኖር የሚፈጠር ዘላቂ ለውጥን የሚተልም ነው፡፡ ፖለቲከኞችም ከራሳቸው ተሻግረው የብዙኃኑን ፍላጎት ለማርካት የሚሠሩ መሆን አለባቸው።

የመደመር መንግሥት ገፅ 281

‎የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ቦርድ አባላት አዲስ ስራ አስኪያጅ ሾሟል‎‎ቦዲቲ ፤ሰኔ 04/2018 የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ቦርድ አባላት አዲስ ስራ አስኪያጅ ሹመት ሰጥቷል።‎‎ቦርዱ አቶ ...
11/06/2026

‎የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ቦርድ አባላት አዲስ ስራ አስኪያጅ ሾሟል

‎ቦዲቲ ፤ሰኔ 04/2018 የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ቦርድ አባላት አዲስ ስራ አስኪያጅ ሹመት ሰጥቷል።

‎ቦርዱ አቶ ዋሲሁን ወ/ዮሃንስን ከዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ስራ አስኪያጅ ሆነው እንዲሰሩ ሾሟል።

‎ወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ከታዳጊ እግርኳስ ፕሮጄክቶች ጀምሮ እስከ ዋናው የወንዶችና የሴቶች እግርኳስ ቡድን ድረስ ያሉ ስራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ እንዲሁም የቮሊቦል ቡድኑ የያዘበትን አስደናቂ የውጤት ጉዞ ለማስቀጠል በማሰብ ነው።

‎አቶ ዋሲሁን ወ/ዮሃንስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በስፖርት ሳይንስ እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ጨርሰዋል።

‎​አዲሱ ስራ አስኪያጃችን በዘርፉ ለበርካታ ዓመታት ሰፊ የስራ ልምድና እውቀትም ያላቸው ናቸው።

‎ቀደም ሲል በ2017 እና 2018 በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ኮሚቴ እንዲሁም በ2018 ላይ የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕርሚየር ሊግ ኮሚቴ በሆኑበት ቆይታ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ናቸው።

‎​ቦርዱ ለአዲሱ ስራ አስኪያጅ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ በማድረግ የስፖርት ክለቡን ስኬት እንደሚያጠናክረም አስታውቋል።

11/06/2026
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ በዶ/ር ዳንኤል ዳሌ የተመራ የድጋፋዊ ክትትል ቡድን በቦዲቲ ከተማ ተገኝቶ የዘርፉን ተግባር አፈጻጸም ገመገመቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 04/...
11/06/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ በዶ/ር ዳንኤል ዳሌ የተመራ የድጋፋዊ ክትትል ቡድን በቦዲቲ ከተማ ተገኝቶ የዘርፉን ተግባር አፈጻጸም ገመገመ

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 04/2018 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ በዶ/ር ዳንኤል ዳሌ የተመራ የድጋፋዊ ክትትል ቡድን በቦዲቲ ከተማ በመገኘት በበጀት አመቱ የዘርፉን የእስካሁን ተግባር አፈጻጸም አጠቀላይ የዘርፉ ባለሙያዎች በተገኙበት ገምግሟል።

ለከተማው የኢኮኖሚያዊ እድገት መሬት ትልቅ ሀብት እንደሆነ በመድረኩ የተጠቆመ ሲሆን ይህንን ውድ የሆነ ሀብት በአግባቡና ለታለመለት አላማ መጠቀም እንዲችል ዘርፉን በትኩረት መምራት ይገባል ተብሏል።

እንደ ከተማ በመሬት ዘርፍ ለህዝብ ተጠቃሚነት የሚሰሩ ሌሎች ተግባራትም የተገልጋዩን እርካታ ያገናዘቡ ሆነው መፈጸም እንዳለባቸውም ተነግሯል።

መሬትን ለአስፈላጊ ጉዳዮች በምንጠቀምበት ወቅት የመሬት አስተዳደር ህግን ፤ አሰራርና መመሪያን በጠበቀ መልኩ መሆን እንዳለበት የተነገረ ሲሆን ተቋሙም ይህን ተግባር በሚያስፈጽምበት ወቅት በተጠያቂነት መንፈስ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት ተመላክቷል።

የካድስተር መብት ምዝገብም ይሁን የማረጋገጥ ስራ በተቋሙ በተሻለ ደረጃ ላይ መሆኑን በማረጋገጥ ኢዉቅና መስጠቱንም ጭምር የክልሉ ቲም አሳውቀዋል።

ለኢንቨስትመንት ፤ ለመኖሪያ ፤ ለማህበራት እንዲሁም ለተለያዩ አገ/ት የተዘጋጀ መሬት የተሻለ መሆኑን የክልል ድጋፋዊ ክትትል ቲም በማረጋገጥ ለቀጣይ አንድ ወር ቀሪ ተግባራት ላይ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል።

ከዘርፉ ለህብረተሰቡ የሚሰጠው አገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊና ችግር ፈቺ እንዲሆን በክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ አማካኝነት የሚያደርገው ድጋፋዊ ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።

ከስድስት ዓመት በፊት የተከሠተውን ለውጥ ተከትሎ በሀገራችን እስከዛሬ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የዴሞክራሲ ምኅዳር ሰፍቷል። ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሐሳብ የማሸነፍ ዕድል ተፈጥሯል...
11/06/2026

ከስድስት ዓመት በፊት የተከሠተውን ለውጥ ተከትሎ በሀገራችን እስከዛሬ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የዴሞክራሲ ምኅዳር ሰፍቷል። ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሐሳብ የማሸነፍ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

የመደመር መንግሥት ገፅ 282

የቦዲቲ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዩኒቲ በአፍላ እድሜ ክልል ላሉ ወጣቶችና ለክበባት መሪዎች በሕይወት ክህሎትና አቻ ለአቻ ትምህርት ዙርያ ግንዛቤ ስልጠና ሰጡቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 04...
11/06/2026

የቦዲቲ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዩኒቲ በአፍላ እድሜ ክልል ላሉ ወጣቶችና ለክበባት መሪዎች በሕይወት ክህሎትና አቻ ለአቻ ትምህርት ዙርያ ግንዛቤ ስልጠና ሰጡ

ቦዲቲ ፤ ሰኔ ፤ 04/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዩኒቲ በአፍላ እድሜ ክልል ለሚገኙ ወጣቶችና ለክበባት መሪዎች በሕይወት ክህሎትና አቻ ለአቻ ትምህርት ዙርያ ግንዛቤ ስልጠና ሰጥተዋል።

ስልጠናውን በቦዲቲ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዩኒቲ የስልጠና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሪት ስሜነሽ ቴቲሶ ሰጥተዋል።

አቶ አስራት አይዛ የቦዲቲ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዩኒቲ አስተባባሪ ይህንን ስልጠና በንግግር ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት ወጣቶች በስነምግባር የታነፁና በአስተሳሰባቸው የተሻሉ እንዲሆኑ እንዲሁም ለሌሎች አረአያ መሆን እንዲችሉ ስልጠናው ይጠቅማል ብለዋል።

በተለይ ወጣቶች በስነልቦናቸውና በጤናቸው ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ከተለያዩ ሱሶችና ከብልሹ ባህሪ እንዲታቀቡ ዘንድ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ለሱሶችና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች መንስኤ የሚሆነውን አቻ ለአቻ ግፊት ወጣቱ እንዴት መቋቋም አለበት ለሚለውም ስልጠናው በቂ ግንዛቤን ይፈጥራል ስሉም አብራርተዋል።

ሴቶች በአቻ ለአቻ ግፊት ምክንያት ከሚደርስባቸው ከፆታ ጥቃት እራሳቸውን እንዲከላከሉ ዘንድ በስልጠናው በበቂ ሁኔታ ትምህርት ይሰጣል ስሉም ገልጸዋል።

ከተለያዩ ትምህርት ተቋማት የመጡ የክበባት ተጠሪዎች እና መሪዎች የዛሬውን ስልጠናውን በሚገባ በመከታተል በየትምህርት ቤቶች ለሚገኙ በአፍላ እድሜ ክልል ላሉ ወጣቶች በተለያዩ ኩነቶች እውቀት እንዲያስጨብጩ አስገንዝበዋል።

Address

Boditi

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት-Boditi Town Prosperity party office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share