ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ - ወሎ Freedom & Equality Party - Wollo

  • Home
  • Ethiopia
  • Bistima
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ - ወሎ Freedom & Equality Party - Wollo

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ - ወሎ   Freedom & Equality Party - Wollo “የወሎ ድምፅ ለነፃነት፣ ለፍትህ እና ለእኩልነት።
Voice of Freedom & Equality in Wollo.”

የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች ሆይ‼️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበውን፣ በምርጫ ክርክሮቹ የላቀ ሀሳብ በማቅረብ ነጥሮ የወጣውን፣ ለቀጣይ አምስት አመት ሀ...
28/05/2026

የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች ሆይ‼️
✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️

የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበውን፣ በምርጫ ክርክሮቹ የላቀ ሀሳብ በማቅረብ ነጥሮ የወጣውን፣ ለቀጣይ አምስት አመት ሀገርን የመምራቱ እድል ቢሰጠው ለማስተዳደር በበቂ ቁመና ላይ የሚገኘውን፣ ተባብሮና ተቀናጅቶ ለመስራት ፈቃደኛ የሆነውን፣ ሚዛናዊና ምክንያታዊ የትግል ስልትን የሚከተለውን፣ ከየትኛውም ዋልታ ረገጥ አስተሳሰብ የራቀውን፣ የአድሱ ትውልድ ፓርቲ 👇
"ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ምርጫችሁ ይሁን‼️

✍️ ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ሚዛናዊነት፣ ምክንያታዊነት፣ አብሮ ማሸነፍ እና አካታችነት መርሆቻችን ናቸው‼️
✍️ ትምህርት መር ብሔራዊ የልማት ስትራቴጅን እንከተላለን‼️
(Education Driven National Development Strategy - ENDS)

ሀገራችንን ቀስፎ የያዛት ጥላቻ መፈናቀል ጦርነት ስዴትና ሞት ደጉን የሀገራችንን ህዝብ ወግና ባህል እንድሁም እምነት የማይወክልና የሚያራክስ በመሆኑ በሀገራዊ እርቅና ብሔራዊ መግባባት እንድፈታና ዜጎች በሀገራቸው ያለስጋት ሰርተው እንድኖሩ በሰላም ወጥተው እንድገቡ ፓርቲያችን ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) አበክሮ ይሰራል።

ሁሉንም የሀገራችንን ህዝቦች መፈናፈኛ ያሳጣው የኑሮ ውድነት የዋጋ ግሽበት ረሀብና ድህነት የመኖሪያ ቤት እጦትና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውስብስብ ችግሮችና ማነቆዎች በተፈጥሮ የተከሰቱ ሳይሆኑ ከብልሹ አሰራርና አስተዳደር ከሙሰኝነት ካለጠራና ካልተገራ ፓሊሲና ስትራቴጅ እና የትግበራ እንዝህላልነት የሚመነጩ ናቸው ብሎ ፓርቲያችን ነእፓ ያምናል።

በመሆኑም እጅግ ባጠረ ጊዜ ውስጥ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ማራገፍ የሚያስችል ፓሊሲና አሰራር ይዘንላችሁ መጥተናል። የችግሮች ሁሉ መፍቻ ቁልፍ የሆነውን ብዕርን ይምረጡ‼️

የጥቂቶች ብልጽግና በብዙሀን ድህነትና ጉስቁልና ላይ መመስረት የለበትም። ፓርቲያችን ነእፓ ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍልና የጋራ ተጠቃሚነት በሀገራችን እንድሰፍን የሚያስችል ፕሮግራም አዘጋጅቷል።

የሴቶችን እኩልነትና ተጠቃሚነት በተግባር የሚያረጋግ ፓሊሲና ስትራቴጅ አበጅተናል። ሴቶች እድሉ ከተመቻቸላቸው የሀገር ዋልታና ማገር ናቸው።

አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ የማህበራዋዊና ኢኮኖሚያዊ ፓሊሲዎችን ቀርጸናል።

የውጭ ድፕሎማሲን የሚያጎለብት ለሀገራችን አምስት የባህር በር የሚያስገኝ ብሔራዊ ጥቅምን የሚያጎናጽፍ በአርቆ አሳቢነት የተነደፈ ድንቅ ፓሊሲ አዘጋጅተናል። እንድሁም በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ዜጎቻችን የጣምራ ዜግነትን የሚፈቅድ አሰራር ጀባ ብለናል።

ወጣቶች በሀገራቸው ንቁ ተሳታፊ ሆነው ሰርተው ራሳቸውን ማበልጸግ ቤተሰቦቻቸውንና ሀገራቸውን መርዳት የሚያስችል እምቅ ኃይልና እውቀት እንዳላቸው እየታወቀ ቆራጥ አመራርና አሳታፊ አደረጃጀት ባለመዘርጋቱ ብዙ ወጣቶች ስራ አጥ ጥገኛና ተመጽዋች መሆናቸው አልፎም በስደት በየበረሀውና በየባህሩ ወድቀው እንድቀሩ መደረጉ እንቅልፍ የሚነሳው ፓርቲያችን ነእፓ ወጣቶችን ማዕከል ያደረገ የሀገር ኢኮኖሚ ዝርጋታን ይከተላል።

ነጻነትና እኩልነት ስንል ምን ማለታችን ነው??
✍️ ነጻነት ስንል፦
➠ የመናገር ነጻነት
➠ የማሰብ ነጻነት
➠ የእምነት ነጻነት
➠ ከድህነትና ረሀብ ነጻነት
➠ መፈናፈኛ ካሳጣን የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት ነጻነት
➠ ከመፈናቀል ከጦርነትና ከስደት ነጻነት
➠ የመደራጀት ነጻነት
➠ ከፍርሀት ነጻነት
➠ ከጭቆናና አፈና ተጻነት

✍️ እኩልነት ስንል፦
➠ በብሄሮች መካከል
➠ በሃይማኖቶች መካከል
➠ በጾታ መካከል
➠ በእድሜ መካከል
➠ በትውልድ መካከል
➠ በክልሎችና አካባቢዎች መካከል
➠ በስራ ቦታና የስራ እድል ከማግኘት አኳያ
➠ የፍትህ እኩልነት
➠ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች

እኩልነትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብሎ ፓርቲያችን ነእፓ በጽኑ ያምናል። ለተግባራዊነታቸውም ዘመናዊ አሰራሮችን አለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን ይከተላል።

የመሬት ፖሊሲያችን ከመንግስት ጭሰኝነት የሚያወጣ የገጠርም የከተማም የመሬት ባለይዞታዎች በመሬታቸው በነጻነት የመጠቀም መብታቸውን የሚያጎናጽፍ ነው። ሰፊ ጥናት ከተደረገ በኋላ በሂደት ወደ ግል ይዞታነት በማሸጋገር መሸጥ መለወጥ የሚያስችል ህግ በሀገራችን ይሰፍናል።

✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️
የፓርቲያችን የመወዳደሪያ የምርጫ ምልክት ብዕር ነው። ብዕር ደግሞ ረቂቅ ሀሳቦች የሚሰፍሩበት ጥልቅ ምርምሮች የሚወጠኑበት ታላቅ መሳሪያ ነው። ብዕር እውቀት መር ፓሊሲያችንን የገለጽንበት ድንቅ መሳሪያ ነው።

ብዕር የእውቀት፣ የጥበብ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጅ፣ የስልጣኔ መገለጫ እና የችግሮች ሁሉ መፍቻ ድንቅ መሳሪያ ነው‼️

የእውቀትና ልዕልና መገለጫ የፍትህና ስልጣኔ ማብሰሪያ የሆነውን ብዕርን ይምረጡ‼️

ነጻነትን እኩልነትን ፍትህን ይምረጡ‼️
ብዕርን ይምረጡ‼️

ከነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ለፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎች እና ለመላ ኢትዮጵያያን የተላለፈ መልእክት፣====================የተወደዳችሁ የነጻነትና እኩ...
27/05/2026

ከነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ለፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎች እና ለመላ ኢትዮጵያያን የተላለፈ መልእክት፣
====================
የተወደዳችሁ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች፣ ውድ የሀገራችን ህዝቦች

ሁላችሁም እንደምታስታውሱት ከ2018 መባቻ በተለይም ባለፉት ስድስት ወራት ፓርቲያችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በጠቅላላ ምርጫ ሲሳተፍ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፣ በምርጫው ውጤታማ ለመሆን ባለፉት አምስት አመታት ሰፊ ድርጅታዊ ስራዎች ሲሰራ ቆይቷል።

አጠቃላይ የምርጫ እንቅስቃሴአችን ፓርቲው ባዘጋጀው የምርጫ ስትራቴጂ እየተመራ በተቀናጀ መልኩ ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህም ዋና ዋና የምርጫ ስራዎች በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቁ ሲሆን፣ ካከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፣

1. በቂ የትምህርት ዝግጅት፣ የስራ ልምድ፣ የህዝብ እና የሀገር ፍቅር ያላቸውን፣ በስነ ምግባር የታነጹ እጩዎችን መርጠን በእጩነት አቅርበናል፣
2. በወቅታዊ መረጃ እና ጥናት ላይ የተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ሳይንሳዊ፣ ሊለካ እና ሊተገበር የሚችል የምርጫ ማኒፊስቶ አዘጋጅተን ለህዝባችን ይፋ አድርገናል፣
3. የፓርቲውን አጠቃላይ ዓላማ እንዲሁም ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀነውን ማኒፊስቶ ለህዝብ ለማድረስ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት ተግባራዊ ለማድረግ ያዘጋጀናቸውን የፖሊሲ አማራጮች ለተከበረው ህዝባችን ለማድረስ ሰፊ የምርጫ ቅስቀሳ ስራ ሰርተናል፣
4. ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመከራከር ፓርቲያችን ያዘጋጃቸው ፖሊሲዎች እና ፕሮግራሞች ከሌሎች ፓርቲዎች የሚለዩበትን እና የሚሻሉበትን ለማሳየት ጥረት አድርገናል፣
5. ለፓርቲዎች የተሰጠውን ነጻ የአየር ሰዓት እድል በመጠቀም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች በቴሌቬዥን፣ በራዲዮ እና በጋዜጣ የፓርቲያችንን ማኒፊስቶ ለህዝባችን አስተዋውቀናል፣
6. በተለያዩ ከተሞች ጎዳናዎች በመንቀሳቀስ ሰፊ የምርጫ ቅስቀሳ አካሂደናል። በዚህም ከህዝባችን ጋር ፊት ለፊት በመገናኘት ፓርቲያችንን፣ የምርጫ ዝግጅታችንን እና ድርጅታዊ መለያዎቻችንን ለህዝባችን በቀጥታ አስረድተናል፣
7. የምርጫ ቅስቀሳ ስራችንን ከመደበኛ ሚዲያ ጎን ለጎን የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አውታሮችን በመጠቀም ለዜጎች ተደራሽ ለመሆን ከፍተኛ ስራ ሰርተናል፣
8. በማህበረሰባችን ውስጥ ልዩ ትኩረት የሚሹ ወገኖችን በተለይም ወጣቶችን፣ ሴቶችን እና የአካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ልዩ የምርጫ እንቅስቃሴ አድርገናል፣
እነዚህን እና ሌሎች አያሌ ዝርዝር ስራዎች ስናካሂድ ቆይተን እነሆ የምርጫ ቅስቀሳ ማገባደጃ ቀን ዋዜማ ላይ ደርሰናል።

ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች

የፖለቲካ ስልጣን ምንጭ ምርጫ እና ምርጫ ብቻ ሊሆን ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ያለው ፓርቲያችን ምንም እንኳን ሀገራችን እጅግ አስቸጋሪ እና ተደራራቢ ችግሮች ውስጥ ብትሆንም ምርጫ ሊካሄድ እኛም በምርጫ ልንሳተፍ ይገባል ብለን የጀመርነው የምርጫ ዝግጅት ተገባዶ፣ ኢትዮጵያውን ድምጻቸውን የሚሰጡበት ቀን እውን ሊሆን በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል።

ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣
ምርጫውን አስመልክቶ የተለያዩ ስጋቶች ሊኖራችሁ እንደሚችል እንረዳለን።

• ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ አንድ አውራ ፓርቲ የፌዴራል እና የክልል ምክር ቤቶችን ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የሚያሸንፍበት የምርጫ ታሪክ ባለት ሀገራችን ለምርጫ ያላችሁ እምነት እና ተስፋ እጅጉን ሊሸረሸር ይችላል፣

• ፓርቲ እና መንግስት አንድ በሆኑባት ሀገር፣ የመንግስት መዋቅር፣ የህዝብ ሀብት እና ገንዘብ ለገዢ ፓርቲ የምርጫ ስራ በግልጽ ጥቅም ላይ በሚውልባት ሀገር ምርጫ ነጻ እና ፍትሀዊ አይሆንም ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፣

• በአንዳንድ አካባቢዎች የሚደረጉ የእርስ በእርስ ግጭቶች እና የሰላም እጦት፣ በምርጫ መሳተፍ በራስ ላይ እንደ መፍረድ ሆኖ ሊሰማችሁ ይችላል፣ በሰላም ወጥቶ መግባት ከፍተኛ ስጋት በሆነባት ሀገር ምርጫ ቅንጦት መስሎ ሊታያችሁ ይችላል፣

• አብዛኛው ህዝባችን ጀርባው ሊሸከመው ከሚችለው በላይ በኑሮ ውድነት እና በዋጋ ንረት እየተሰቃየ ባለበት እና ከህዝብ ፍላጎት ጋር ሆድ እና ጀርባ የሆነው የገዢ ፓርቲ የብልጽግና እና የልእልና ትርክት “ላም አለኝ በሰማይ” ሆኖብዎት በመንግስት ላይ ተስፋ ሊያስቆርጣችሁ ይችላል፣

• የተሻለ አቅም ላለው ገዢ ፓርቲ ከፍተኛ እድል የሚሰጠው እና የተፎካካሪ ፓርቲዎችን ወንበር የማግኘት እድል የሚያቀጭጨው ኢ-ፍትሀዊ የምርጫ ስርዓት ከምርጫው የተለየ ውጤት እንዳይጠብቁ ተስፋ ሊያስቆርጦት ይችላል፣

• ባለፉት ጥቂት ወራት እንደታየው ዜጎች ያለፍላጎታቸው የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ ማስገደድ፣ ዜጎች የገዢውን ፓርቲ ብቻ እንዲመርጡ የአካል እና የስነልቦና ጫና ማድረግ፣ የካድሬ እና ሚሊሺያ ወከባ፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ፣ በምርጫ ተስፋ እንዲቆርጡ ሊያደርግዎት ይችላል፣

• እጅግ የተበላሸ የመንግስት አሰራር፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ በጥቅም የተሳሰሩ ሹመኞች የሀገርን እና የህዝብን ደም እንደመዥገር በሚመጡባት ሀገር፣ በሀገር ጉዳይ የመሳተፍ ፍላጎትዎ በእጅጉ እንዲቀንስ አድርጎ ሊሆን ይችላል፣

• እነዚህ እና ሌሎችም በርካታ ችግሮች እና ስጋቶ ዜጎች በምርጫ ላይ ያላቸው እምነት እና ተስፋ እንዲመናመን አድርጎ ሊሆን እንደሚችል እንገነዘባለን፣

• ከዚህ ቀደም እንደተካሄዱ ምርጫዎች ሁሉ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እጅግ አስቸጋሪ በሆነ የፖለቲካ፣ የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ አውድ ውስጥ እንደሚካሄድ በሚገባ እንረዳለን።

ውድ ኢትዮጵያውያን
እነዚህ ችግሮች እና ስጋቶች የሀገራች የፖለቲካ ስሪት፣ የፖለቲካ ታሪካችን አካል እንደሆኑ እንገንዘባለን። ይሁን እንጂ እንደ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሀገራችን ካለችበት የቀውስ አዙሪት ተላቃ ነጻነት፣ እኩልነት እና ፍትህ የሰፈነባት ሀገር እውን ለማድረግ ከእነ ችግሩም ቢሆን መንግስት በምርጫ እንዲመሰረት ማድረግ የተሻለ ነው ብለን እናምናለን።

ከዚህ እምነት በመነሳት ከቀናት በኃላ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው በቀጣይ አምስት አመታት ሀገራቸውን እንዲመራ የሚፈልጉትን ፓርቲ ሊመርጡ ይገባል ብለን አናምናለን።

ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተወደዳችሁ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች

ሀገራችን ካለችበት የጦርነት፣ የድህነት፣ የስደት፣ የስራ አጥነት፣ የኑሮ ውድነት ችግሮች ባጠረ ጊዜ ተላቃ ሰላም የሰፈነባት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በምርጫው ከፍተኛ ውጤን ማግኘት ግዴታ ነው ብለን ለምርጫው ከፍተኛ ዝግጅት ስናደርግ ቆይተናል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በምርጫ ከፍተኛ የህዝብ ድምጽ አግጭቶ በቀጣይ አምስት አመታት በሀገራችን የሚመሰረተው መንግስት አካል ይሆን ዘንድ ለፓርቲያችን አባላት፣ ደጋፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት እና ለመላው የሀገራችን ህዝቦች የሚከተሉትን መልእክቶች እናስተላልፋለን።

1ኛ. መላ የፓርቲያችን አባላት፣ ደጋፊዎች እና አድናቂዎች ይህ መልእክት ከደረስዎት ጊዜ ጀምሮ ምርጫው እስከሚጠናቀቅበት የመጨረሻ ሰዓት የቤተሰብ አባልዎ፣ ዘመድ አዝማድ፣ የስራ ወይም የትምህርት ቤት ጓደኞቻችሁ፣ ጎረቤቶቻችሁ እንዲሁም በቅርብም ሆነ በርቀት የሚያውቋቸው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ነእፓን ይመርጡ ዘንድ በስልክ፣ በአጭር የጽሁፍ መልእክት፣ በማህበራዊ ሚዲያ የትስስር አውታሮች መልእክት እንድታስተላልፉ በክብር እንጠይቃለን፣

2ኛ. በየትኛውም ክልል፣ ዞን፣ ወረዳ ከተማ እና የምርጫ ክልል የምትገኙ መራጮች ነእፓ በአካባቢው ያለው ማህበራዊ መሰረት ወይም ድጋፍ ምንም ይሁን ምን ድምጻችሁን ለነጻነትና እኩልነት ፓርቲ እንድትሰጡ አደራ እንላለን። ዜጎች ለፓርቲያችን የሚሰጡት እያንዳንዷ ድምጽ ፓርቲያችን በህዝብ ዘንድ ያለውን ድጋፍ እና ተቀባይነት የምታሳይ ኃይል ናት።

እያንዳንዷ ድምጽ የፓርቲያችን የምርጫ ታሪክ አካል ናት። እያንዳንዷ ድምጽ በሀገራችን ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ሰላም እና እድገት እንዲሰፍን ዜጎች ፍላጎታቸውን የሚገልጹበት መሳሪያ ነች። ድምጽ በሚሰጡበት የምርጫ ክልል ነእፓ አብላጫ ድምጽ ሊያገኝ ወይም ላያገኝ ይችላል። ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ድምጽዎን ለነእፓ ይስጡ። የነጻነት እና የእኩልነት አሻራዎን ያስቀምጡ።

3ኛ. በፓርቲያችን እና ሌሎች ጥቂት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በፋይናንስ፣ በአደረጃጀት፣ በሎጂስቲክስ እና በሌሎች አቅሞች በግልጽ የሚታይ ሰፊ ልዩነት ሊኖር ይችላል። ልዩነቱ የሰማይ እና የመሬት ያክል የተራራቀ ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ እውነት በአካላዊ ግዝፈት እና በኃይል አይለካም። እውነት ብዙ ገንዘብ፣ አጀብ፣ ጉልበት እና ጥይት ባይኖራትም ሁሌም አሸናፊ ነች። በፍትህ ላይ ያልተመሰረተ ኃይል ምን ያክል ገዝፎ ቢታይ ለፍትህ ቦታ መልቀቁ አይቀሬ ነው።

የሀገራችን እና የዓለም ታሪክ ለዚህ ህያው ምስክር ናቸው። የዳውድ እና የጃሉት ወይም የዳዊት እና የጎሊያድ ታሪክ የሀሳብ ጥራት እና የዓላማ ጽናት አካላዊ ግዝፈት እና ጉልበትን አሸንፎ ድል እንደሚጎናጸፍ ህያው ማሳያ ናቸው። በመሆኑም ከምርጫ ግርግር፣ ከተትረፈረፈ ድጋስ እና ገንዘብ ባሻገር ድምጽዎን ከእውነት እና ርትዕ ጎን ቆሟል ለሚሉት ፓርቲ ይስጡ። ከዚህ አንጻር ፓርቲያችን በእጅጉ የተሻለ ነው ብለን እናምናለን። እንዲመርጡን በክብር እንጠይቃለን።

4ኛ. ላለፉት አመታት በተለያየ ተጽእኖ ምክንያት የአንድ ፓርቲ ደጋፊ ሆናችሁ ወይም በግዳጅ ለአንድ ፓርቲ ድጋፍ አድርጋችሁ ወይም ከአንድ ፓርቲ ጋር ከዚህ የተለየ ግንኙነት መስርታችሁ ሊሆን ይችላል። በመርህ ደረጃ ከአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ጋር የሚኖር ግንኙነት በግለሰቦች መልካም ፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይገባል።

ይሁን እንጂ በእኛ ሀገር ለሚዲያ ፍጆታ እና ህጋዊ ባልሆነ መንገድ የዜጎችን ሀብት እና ገንዘብ ለመዝረፍ ዜጎች የአንድ ፓርቲ አባል ወይም ደጋፊ እንዲሆኑ ይገደዳሉ። ዜጎችን አስገድደው የፓርቲ አባል ወይም ደጋፊ የሚያደርጉ አካላት ይህ ህገ ወጥ ተግባር በምርጫ ወቅት ውጤቱ የተገላቢጦሽ እንደሚሆን ጠንቅቀው ያውቃሉ። በዚህ ምክንያት ምርጫ ሲመጣ አብዝተው ይጨነቃሉ።

በመሆኑም ያለፍላጎታችሁ እና ፍቃዳችሁ በግዳጅ የአንድ ፓርቲ አባል ወይም ደጋፊ እንድትሆኑ የተፈረደባችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን፣ ይህ ምርጫ ነጻነታችሁን ገፈው ያለፍቃዳችሁ የማትፈልጉት ፓርቲ አባል ወይም ደጋፊ ያደረጓችሁን አካላት በካርዳችሁ የምትቀጡበት ይሁን። ወሳኝ በሆነው የምርጫ ቀን ከይስሙላ የፓርቲ አባልነት እና ደጋፊነት አልፋችሁ የሀገራችሁን መጻኢ እድል፣ የእናንተን እና የልጆቻችሁን የነገ ተስፋ አስባችሁ ድምጻችሁን ስጡ።

ከራሳችሁ ጋር ብቻ ሆናችሁ በሚስጥር ድምጽ ስትሰጡ በሀገራችን ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ልማት እውን ሊያደርግ ተዘጋጅቷል የምትሉትን ፓርቲ ምረጡ። የድምጽ መስጫ ወቅት ከእውነት እና ከህሊና ፍርድ ጋር ፊት ለፌት የምትቆሙበት ቅጽበት መሆኑን አስታውሱ። በሀገራችሁ ነጻ እና ከሌላው ወገናችሁ ጋር እኩል ሆናችሁ መኖር የምትችሉበትን እድል አስታውሱ።

5ኛ. ውድ የሀገራችን ህዝቦች ሀገራችን ውስጥ ለረዢም ግዜ በቆዩ አምባገነን ስርዓቶች ምክንያት ሀገራችን ዜጎች ሀሳባቸውን በግልጽ መናገር የማይችሉባት ምድር ሆናለች። ፍርሀት እና ስጋት ህዝባችንን ቀፍድደው ይዘውታል። ይህ ስሜት በዚህ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንደነገሰ እንረዳለን። ይሁን እንጂ አርቆ አስተዋዩ ህዝባችን ሀገሩን ከጥፋት ለመታደግ እና ነጻነቱን ለመጎናጸፍ መቼ ምን ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል ብለን በጽኑ እናምናለን።

ኢትዮጵያውያን ያለፍትህ ያሰራቸውን፣ ከሞቀ ጎጃቸው ያፈናቀላቸውን፣ የላባቸውን ፍሬ የቀማቸውን፣ በግብር ስም ደማቸውን የመጠጣቸውን እና አያሌ በደል የፈጸመባቸውን አካል ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዴት መቅጣት እንዳለባቸው ያውቃል የሚል የጸና እምነት አለን። ኢትዮጵያውያን ካርዳቸውን መቼ እና እንዴት መምዘዝ እንዳለባቸው ጠንቅቆ እንደሚያውቅ እንረዳለን።

ከዚህ የጸና እምነት በመነሳት ከቀናት በኃላ በሚካሄደው ምርጫ መላ የሀገራችን ህዝቦች የጦርት፣ የስደት፣ የርሀብ፣ የመፈናቀል፣ የብልሹ አሰራር ታሪክ ተዘግቶ የነጻነት፣ የእኩልነት፣ የፍትህ እና የልማት አዲስ ምእራፍ እውን ይሆን ዘንድ ቁጭታቸውን በካርዳቸው ለመወጣት የምርጫውን ቀን በተስፋ እና በጉጉት እየጠበቁ ነው ብለን እናምናለን። ብቻዎን አይደሉም!! እንደ እርስዎ በሀገራችን የአስተዳደር ለውጥ እንዲመጣ አጥብቀው የሚሹ እና ይህንኑ ባካርዳቸው እውን ለማድረግ የተዘጋጁ ሚሊዮኖች ታሪክ ለመስራት ተዘጋጅተዋል።

እርሶም የዚህ ታሪክ አካል እንዲሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። አዲስ ራዕይ፣ የተሻለ የትግል ስልት፣ እውነተኛ የሀገር ፍቅር ያለው ፓርቲ የትኛው ነው ብለው ሲያስቡ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ያስታውሱ። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲን በመምረጥ አሻራዎን ያስቀምጡ።

ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ በምርጫ የምትሳተፉ ተቋማት ተወካዮች፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች፣ የተወደዳችሁ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ሀገር በቀል እና የውጭ ሀገር ታዛቢዎች፣ የፓርቲ ተወካዮች፣

• 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ እና ውጤቱ የሀገራችንን መጻኢ እድል የሚወስን ታሪካዊ የፖለቲካ ሁነት ነው። ምርጫው ከቃላት አልፎ በተግባር ነጻ፣ ፍትሀዊ እና ሰላማዊ እንዲሆን ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባችሁ እናስገነዝባኋለን፣

• በምርጫው በሚኖራችሁ ተሳትፎ የህግ እና የታሪክ ተጠያቂነት እንዳለባችሁ ተረድታችሁ ኃላፊነታችሁን በታማኝነት እና በተጠያቂነት እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፣

• የድምጽ አሰጣጥ፣ የድምጽ ቆጠራ እና ሌሎች ከምርጫ ቀን በፊት፣ በምርጫ ቀን እና ከምርጫ ቀን ኃላ የሚሰሩ ስራዎች የምርጫ ህግ እና ስርአትን ጠብቀው፣ የዜጎችን መብት እና ሉአላዊነት ባከበረ መልኩ እንዲፈጸሙ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን፣

• የመንግስት አካላት በተለይም የታችኛው መዋቅር የስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ከምርጫው ስራ ጋር በተያያዘ የሚጠበቅባችሁን ተግባር ስትፈጸሙ ገለልተኝነታችሁን ጠብቃችሁ መንግስታዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ፣ የምርጫውን ነጻነት እና ፍትሀዊነት ከሚያውኩ ተግባራት እንድትታቀቡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በመጨረሻም
መላው የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም መላ የሀገራችን ህዝቦች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከምንም በላይ በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ ጥሪያችንን እያስተላለፍን፣ ነጻነት፣ እኩልነት እና ፍትህ የሰፈነባት ሀገር ማየት እንድንችል መላ የሀገራችን ህዝቦች ነጻነትና እኩልነት ፓርቲን እንድትመርጡ በታላቅ አክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የፓርቲያችን የምርጫ ምልክት ብዕር ነው።
ብዕር የሀሳብ ፖለቲካ፣ ብዕር የምክንያታዊ ፖለቲካ፣ ብዕር የስልጡን ፖለቲካ ምልክት ነው።
በብዕርዎ ብዕርን ይምረጡ!!

ብዕርን ስለሚመርጡ እናመሰግናለን!!
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት 2018

27/05/2026
ሰብአዊ መብት በኢትዮጵያ የእምነት ነጻነት እና እኩልነት እንደማሳያ*****************************ሰብአዊ መብት ማለት አንድ ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ የሚቀዳጀው፣ ከልደት እስከ ህ...
26/05/2026

ሰብአዊ መብት በኢትዮጵያ
የእምነት ነጻነት እና እኩልነት እንደማሳያ
*****************************
ሰብአዊ መብት ማለት አንድ ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ የሚቀዳጀው፣ ከልደት እስከ ህልፈት የሚጎናጸፈው፣ በጊዜ እና ቦታ የማይገደብ መብቶችን ያካትታል። በህይወት የመኖር፣ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመስራት እና ሀብት የማፍራት፣ የመረጡትን እምነት የመከተል እና የማምለክ፣ በህግ ፊት እኩል የመዳኘት፣ ወዘተ ከሰብአዊ መብቶች ጥቂቶቹ ናቸው። ሰብአዊ መብቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የተቀዳጇቸው መብቶች ሲሆኑ ሁሉም ሰብአዊ ፍጡራን ሊኖራቸው የሚገቡ መብቶች ናቸው።

ዓለምአቀፍ የሰብአዊ መብት ስምምነቶች መንግስታት ሰብአዊ መብቶችን የማክበር ዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋሉ። ሰብአዊ መብቶችን ለመጠበቅ ሀገራት ከሚያወጧቸው ህጎች በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ ልዩ ልዩ ደንቦች የጸደቁ ሲሆን እ.ኤ.አ በ1948 የወጣው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌ አንዱ ነው።

የሰብአዊ መብት ሰፊ አድማስ ያለው ጽንሰ ሀሳብ ሲሆን ልዩ ልዩ የዘርፉ ባለሙያዎች በተለያየ መንገድ በመከፋፈል ይገልጹታል። የግለሰብ እና የቡድን መብት፣ የሲቪልና የፖለቲካ መብት፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ እና የባህል መብቶች ከሰብአዊ መብቶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

የሰብአዊ መብት አያያዝ በኢትዮጵያ
የሀገራችን የሰብአዊ መብት አያያዝ ታሪክ በዓለምአቀፍ ደረጃ ዝቅተኛ ከሚባሉት ሀገሮች ተርታ የሚመደብ ነው። የኢትዮጵያ መንግስታት በዜጎች ላይ እጅግ ዘግናኝ ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶችን ፈጽመዋል። ዜጎች በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ በብሄራቸው፣ በኃይማኖታቻው ወይም በሌላ ማንነታቸው ምክንያት ሰብአዊ መብቶቻቸው ተጥሶ ለከፋ እና አሰቃቂ ግፍ ይዳረጋሉ። በዜጎች ላይ በተፈጸሙ ኢ-ሰብአዊ እርምጃዎች አያሌ ወገኖቻችን ህይወታቸውን አጥተዋል፣ አካላቸው ጎድሏል፣ ሀብት ንብረታቸውን አጥተዋል። ከህግ ውጪ ግድያ፣ እስርና ግርፋት፣ ያለክስ ለተራዘመ ጊዜ ማቆየት በዜጎች ላይ ከሚፈጸሙ ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች መካከል ናቸው።

የሀገራችን የሰብአዊ መብት አያያዝ ያለበትን አስከፊ ደረጃ በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ሌሎች ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች የሚያወጧቸው ሪፖርቶች ያመለክታሉ። የሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አለመከበር ሀገራችንን ብዙ ዋጋ አስከፍሏታል።

የአምልኮ ነጻነት ህጋዊ መሰረቶች
የእምነት ነጻነት ሰፊ ብሄራዊ እና ዓለማቀፋዊ መሰረቶች ያሉት የሰብአዊ መብት አካል ነው። የሀይማኖት ነፃነት መርኅ በኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እዉቅና የተሰጠው ሲሆን የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 27(1) “ማንኛዉም ሰዉ የማሰብ፣ የህሊናና የሀይማኖት ነፃነት እንዳለው ይህም መብት ማንኛዉም ሰዉ የመረጠዉን ሀይማኖት ወይም እምነት የመያዝ ወይም የመቀበል፣ ሀይማኖቱንና እምነቱን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን በይፋ ወይም በግል የማምለክ፣ የመከተል፣ የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብትን እንደሚያካትት ይደነግጋል።

የሃይማኖት ወይም የእምነት ነፃነቶች በተለያዩ ዓለም አቀፍ ህጎች እና ስምምነቶች ሰፊ እውቅና ተሰጥቷቸዋል። እ.ኤ.አ. በ1981 የወጣው የተባበሩት መንግስታት የጠቅላላ ጉባኤ መግለጫ አንቀጽ 1(1) "ማንኛውም ሰው የማሰብ፣ የሕሊና እና የሃይማኖት ነፃነት እንዳለው እና ይህም መብት የፈለገውን እምነት የማግኘት ነፃነትን እንደሚጨምር ያመለክታል።

የዓለም አቀፉ የሲቭል እና የፖለቲካ መብቶች የቃል ኪዳል ሰነድ (ICCPR) በአንቀፅ 2(1) እያንዳንዱ የመንግስት አካል ምንም ዓይነት ልዩነት ሳያደርግ በግዛቱ ውስጥ ያሉ ግለሰቦችን ሀይማኖት ማክበር እንዳለባቸው እንዲሁም በአንቀጽ 18 (1) ሁሉም ሰው ሀይማኖቱን በነጻነት የመተግበር፣ የማሰብ፣ የህሊና ነፃነት እንዳለው ይደነግጋል።

የሀይማኖት ነጻነት በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ 18፣ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን አንቀጽ 18 እንዲሁም በሃይማኖት ወይም እምነት ላይ የተመሰረተ አድልዎን ለማስወገድ በወጣው ዲክላሬሽን ተረጋግጧል። ሀገራችን እነዚህን ስምምነቶች የተቀበለች ሲሆን የኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 13/2 ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸዉ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችም የኢትዮጵያ ህግ አካል ተደርገው ይወሰዳሉ።

በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ መንግስት እነዚህን አለም አቀፍ ስምምነቶች እንዲያከብር፣ እንዲያስከብር እና ለህጎቹ መከበር ምቹ ሁኔታን እንዲፈጥር ያስገድዳሉ። ከላይ የተገለጹት የኢፌድሪ ህገ መንግስት እና ሌሎች አለም አቀፍ ህጎች የሀይማኖት እና የአምልኮ ነጻነቶች ጠንካራ ህጋዊ መሰረት ያላቸው የማይሸራረፉ የዜጎች ስብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አካል መሆናቸውን በማያሻማ መልኩ ያሳያሉ።

ሰብአዊ መብት በኢትዮጵያ፡ የእምነት ነጻነት እንደማሳያ
የእምነት ነጻነት በብሄራዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ህጎች የተከበረ ቢሆንም፣ ይህ የሰብአዊ መብት አካል የሆነው መሰረታዊ መብት በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያየ ጊዜ እና ሁኔታ ሲጣስ ማየት የተለመደ ነው። በሀገራችን ዜጎች እምነታቸውን በነጻነት እና እኩልነት እንዳይተገብሩ በተለያይ መንገድ ስልታዊ ጫና ይደረግባቸዋል። ዜጎች በእምነታቸውን ቀኖና እና አስተምህሮ መሰረት የግል እና የቡድን መብቶቻቸውን እንዳይጠቀሙ በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ ጫና እና ግልጽ ክልከላ ማድረግ በሀገራችን የተለመደ ነው።

ዜጎች በሚያምነት እምነት ቆኖና መሰረት አምልኮ መፈጸም እና የሚለብሱትን ልብስ መምረጥ ከሰብዓዊ መብቶች መካከል እጅግ በጣም ዝቅተኛው የስብአዊ መብት መገለጫ ነው። ይሁን እንጂ ይህ መብት ዛሬም በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ሲጣስ ይስተዋላል።

ዜጎች የእምነታቸው ህግ በሚፈቅደው መሰረት ለብሰው እንዳይማሩ ጫና ይደረግባቸው። ዜጎች በትምህርት ቤቶች እና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአለባበሳቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ይባረራሉ። ይህ ችግር የአንድ ጊዜ ወይም የአንድ ትውልድ ሳይሆን የበርካታ ትውልዶች ችግር ሆኖ ዛሬም ድረስ ቀጥሏል።

በተለያየ ወቅት ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ መንግስታት ሃይማኖትን አስመልክቶ ባወጧቸው ህጎች እና በወሰዷቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች የዜጎችን የእምነት ነጻነት በስፋት ሲገፉ ኖረዋል። የመንግስት አካላት የዜጎችን የእምነት እና የአምልኮ ነጻነት የሚቃረኑ፣ አለባበስን ጨምሮ በዜጎች የኑሮ ዘይቤ ጣልቃ የሚገቡ ህጎችን በህዝብ ላይ ጭነዋል። የዜጎችን የአኗኗር እና አለባበስ መብት በመጋፋት የተጠመዱ አንዳንድ አካላት፣ በእምነታቸው ምክንያት ዜጎች የሚጠቀሙትን አለባበስ “የብሄራዊ ደህንነት ስጋት ነው” ብለው እስከ መፈረጅ ደርሰዋል።

እንዲህ ያሉ ኃላፊነት የጎደላቸው ፍረጃዎች፣ ክልከላዎች እና እሳቤዎች የሀገራችንን ህዝቦች ብዝሀነት ያልተረዱ፣ የሀገራችንን ህገ መንግስት የሚጻረሩ፣ የኢትዮጵያውያንን የረዢም ጊዜ የአብሮነት፣ የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት ታሪክ ያላገናዘቡ ስሁት እና የተንሸዋረሩ ፖሊሲዎች ናቸው። በመሆኑም የዜጎችን የእምነት ነጻነት የሚሸራርፉ ህግች እና አሰራሮች በአፋጣኝ ሊቆሙ እና ህገ መንግስታዊ ዋስትና ያለው ዘላቂ መፍትሄ ሊዘጋጅላቸው ይገባል።

የኃይማኖት ነጻነት እና እኩልነት በነጻነትና እኩልነት ፓርቲ እይታ
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በኢፌድሪ ህገ መንግስት የተረጋገጠው የሃይማኖት ነጻነት እና እኩልነት ሳይሸራረፍ ሊከበር ይገባል ብሎ በጽኑ ያምናል። ነእፓ የዜጎች ህገ መንግስታዊ የሃይማኖት እና የአምልኮ ነጻነት ያለ አንዳች ጣልቃ ገብነት ሊከበር ይገባል ብሎ የሚያምን ሲሆን፣ ለዜጎች የተሟላ ስብዕና እና ጤናማ ስነ-ልቦና ሃይማኖቶች የማይተካ ሚና እንዳላቸው ይገነዘባል። ነእፓ ሀይማኖትን እና አምልኮን በተመለከተ የሚወጡ ህጎች፣ ደንቦች እና አሰራሮች የሀገራችንን እና የህዝቦችን ወግ፣ ባህል እና ታሪክ ታሳቢ ያደረጉ ሊሆኑ ይገባል ብሎ ያምናል።

ነእፓ አልፎ አልፎ “ሴኩላሪዝምን” እንደ መነሻ በመውሰድ በዜጎች ላይ የሚወሰዱ የእምነት እና የአምልኮ ክልከላዎች ህገ መንግስታዊ መሰረት የሌላቸው፣ የሀገራችንን ማህበራዊ ስሪት እና መስተጋብር ያላገናዘቡ ህገ ወጥ እርምጃዎች ናቸው ብሎ ያምናል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሁሉም ሃይማኖቶች መሰረታዊ መልዕክት ሰላም፣ ፍቅር፣ ሰብዓዊነትና ወንድማማችነት ነው ብሎ ያምናል። ነእፓ ሃይማኖቶችን በስጋት የሚመለከቱ መጤ አስተሳሰቦች እንዲሁም በሃይማኖቶች እና አማኙ ማህበረሰብ ላይ እብዘፈቀደ የሚጣሉ ክልከላዎች እና ገደቦች የዜጎችን ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብት ይሸረሽራሉ ብሎ ይገነዘባል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ኢትዮጵያውያን ለሃይማኖት እና ሃይማኖተኛነት ከፍተኛ ዋጋ እና ክብር እንዳላቸው እና ሀይማኖት የአብዛኛው የሀገራችን ህዝቦች አንዱ እና ዋነኛው የማንነት መገለጫ እንደሆነ ይገነዘባል። ኢትዮጵያ በአለም “የሀይማኖተኛነት መለኪያ Religiosity Index” ከአለም ቀዳሚ ስፍራ መያዟ ለዚህ አንድ ትልቅ ማሳያ እንደሆነ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ይረዳል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከላይ የተጠቀሱ ሀገራዊ እና ዓለማቀፋዊ የሰብአዊ መብት ህጎችን፣ አለም አቀፍ የእምነት ነጻነት አተገባበር ተሞክሮን፣ እንዲሁም የሀገራችንን ታሪካዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ሀቆች ከግንዛቤ በማስገባት፣

1. በሀገራችን ሁሉም አይነት የሰብአዊ መብቶች በተለይም የእምነት እና የአምልኮ ነጻነቶች ሳይሸራረፉ እንዲከበሩ ይሰራል።

2. ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ዜጎች እምነታቸውን መሰረት ያደረገ የኑሮ ዘይቤ በተለይም የአለባበስ ባህል እዲከበር ይሰራል። በዚህም በአለባበሳቸው ምክንያት በዜጎች ላይ የሚደረግ ማንኛውም ክልከላ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲወገድ ነእፓ ይሰራል። ነእፓ በተለይም ሴት ተማሪዎች በእምነታቸው ህግ መሰረት ለብሰው የመማር እና የመስራት መብታቸው እንዲከበር አስፈላጊውን የህግ ጥበቃ እና ዋስትና ይሰጣል፣

3. ከተማሪዎች የአምልኮ ነጻነት፣ ከተማሪዎች ባህላዊ እና ሀይማኖታዊ አለባበስ ጋር ተያይዞ ከሀገራችን የትምህርት ዘርፍ ደንቦች እና መመሪያዎች ጋር በሚቃረን መልኩ አንዳንድ የትምህር ቤት እና የከፍተኛ የትምህርት ተቋም አመራሮች በግል ፍላጎት እና ጥላቻ የሚወስዱትን ህገ ወጥ ተግባር ስርአት ለማስያዝ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አስፈላጊውን የህግ ማሻሻያ ተግባራዊ ያደርጋል፣

4. የአምልኮ ቦታዎችን መገንባት የሀይማኖት ነጻነት አንዱ አካል ነው። አለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን 2005/40 በአንቀፅ 9 (ሰ) ሁሉም ሰዎች ከሀይማኖት ወይም እምነት ጋር በተገናኘ የማምለክ ወይም የመሰብሰብ መብት እንዳላቸው እና ለሀይማኖታዊ/ለአምልኮ ስነስርአቶች ቦታዎችን የማቋቋም እና የመንከባከብ መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን ይደነግጋል።

በተመሳሳይ የኢፊድሪ ህገ መንግስት ዜጎችን የመረጡትን እምነት በግልም ሆነ በቡድን ለመከወን የአምልኮ ቦታዎችን የመገንባት እና የማስፋፋት መብት እንዳላቸው ይደነግጋል። ይህንን መሰረት መሰረት ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ዜጎች በየትኛውም የሀገራችን አካባቢዎች የአምልኮ ቦታዎችን የመገንባት መብታቸው እንዲከበር ይሰራል፣

5. ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሃይማኖትን አስመልክቶ የሚወጡ ህጎች እና ደንቦች በአንድ በኩል በሀገራችን የሚገኙ የሁሉንም እምነቶች የወል ባህሪያት በሌላ በኩል የእያንዳንዱን እምነት ልዩ ባህሪያት እና ድንጋጌዎች ከግምት ውስጥ ያስገቡ እንዲሆኑ ያደርጋል፣

6. የተለያዩ ሀይማኖቶች በጊዜ የተገደቡ የአምልኮ ስርአቶች እንዳሏቸው ይታወቃል። ይህንን መብት መገደብ የእምነት ነጻነትን ከመገደብ ተለይቶ አይታይም። በመሆኑም ዜጎችን እንደየ እምነታቸው መብታቸው እንዲከበር ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሳያለሰልስ ይሰራል።

7. ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሃይማኖትን በተመለከተ የሚወጡ ህጎች፣ ደንቦች፤ መመሪያዎች እና አሰራሮች በኢትዮጵያዊያን ህይወት ውስጥ ሃይማኖቶች ያላቸውን ከፍተኛ ቦታ እና ክብር ያከበረ እንዲሆን ያደርጋል።

8. ኢትዮጵያ ከዓለም ታላላቅ እምነቶች ጋር ተንካራ ቁርኝት እና ታሪክ ያላት ሀገር እንደሆነች ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ይገነዘባል። አብዛኛው የሀገራችን ህዝብ የእስልምና፣ የክርስትና እና የሌሎች እምነቶች ተከታይ እንደሆነ እና ለእምነቱ ዋጋ የሚሰጥ ማህበረሰብ እንደሆነ ነእፓ ይረዳል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ማተብም፣ ሂጃብም፣ ኒቃብም ኢትዮጵያው ናቸው ብሎ ያምናል። በዚህም መሰረት ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ መላ የሀገራችን ህዝቦች እምነታቸውን በነጻነት እና በእኩልነት እንዲተገብሩ፣ እንደ እምነታቸው ወግ እና ባህል እንዲለብሱ፣ በእምነታቸው እንዲዋቡ እና እንዲከብሩ ተገቢውን የህግ እና የአስተዳደር ማዕቀፍ ያዘጋጃል።

የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፤
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሀገራችን ሁሉም አይነት የሰብአዊ መብቶች በተለይም የእምነት እና የአምልኮ ነጻነቶች እንዲከበሩ ይሰራል። ነእፓ ዜጎች የእምነታቸው ቆኖና እና ባህላዊ እሴቶቻቸው በሚፈቅዱት መሰረት የእለት ተለት ህይወታቸውን እንዲኖሩ፣ የአለባበስ ወጋቸውን ጠብቀው እንዲማሩ እና እንዲሰሩ ያደርጋል። ነእፓ ይህንን መሰረታዊ የሰብአዊ መብት የሚቃረኑ እና ዘመኑ የደረሰበትን የሰብአዊ መብት እሳቤዎችን የሚቃረቡ ኃላ ቀር ህጎች፣ አሰራሮች እና ደንቦች እንዲሻሩ ያደርጋል።

ነእፓ ይህን ራዕዩን እውን ማድረግ ይችል ዘንድ በመጪው ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ በሰብአዊ መብት አያያዝ መስክ የተሻለ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ያለውን ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ እንድትመርጡ በከፍተኛ አክብሮት እንጠይቃለን።

ምልክታችን ብዕር ነው!!
ብዕር የእውቀት፣ የጥበብ፣ የምርምር፣ የስልጣኔ መገለጫ ነው።
ብዕርን ስለሚመርጡ እናመሰግናለን!!
ብዕርን ይምረጡ። ብዕር ሁሌም ያሸንፋል።
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት ፣ 2018
አዲስ አበባ።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)Freedom and Equality Party (FEP)ፓርቲያችን ነእፓ ተመራጭና ቀዳሚ ነው ስንል በምክንያት ነው‼️        ‼️‼️ነጻነትና እኩልነት ፓርቲን...
25/05/2026

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)
Freedom and Equality Party (FEP)

ፓርቲያችን ነእፓ ተመራጭና ቀዳሚ ነው ስንል በምክንያት ነው‼️








‼️‼️

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲን ይምረጡ‼️
ብዕርን ይምረጡ‼️

25/05/2026
በውጪ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንየምስጋና እና የአብረን እንስራ ጥሪ!!➖➖➖➖➖➖➖ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባዘጋጀት ማኒፌስቶ በኢ...
20/05/2026

በውጪ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን
የምስጋና እና የአብረን እንስራ ጥሪ!!
➖➖➖➖➖➖➖
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባዘጋጀት ማኒፌስቶ በኢትዮጵያ የጣምራ ዜግነት ፖሊሲን ተግባራዊ እንደሚያደርግ መግለጹ ይታወቃል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ያደረገው የጣምራ ዜግነት የፖሊሲ ሀሳብ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ በተሻለ ሁኔታ እንዲሳተፉ እና ለአገራቸው እድገት የተሻለ አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችሉ መልካም እድል እንደሚፈጥር ይታመናል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ይፋ ያደረገውን የጣምራ ዜግነት የፖሊሲ አማራጭ ዜና የሰሙ በተለያዩ የዓለም ክፍል የሚኖሩ የነእፓ አባላት፣ ደጋፊዎች እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለፖሊሲው ያላቸውን ከፍተኛ ድጋፍ በተለያየ መንገድ እየገለጹ ይገኛሉ።

እነዚሁ ወገኖች የጣምራ ዜግነት ጉዳይ ላለፉት በርካታ አስርት ዓመታት ሀገር ላስተዳደሩ የኢትዮጵያ መንግስታት ያለመታከት ሲያቀርቡት የነበረ መሰረታዊ ጥያቄ መሆኑን ጠቅሰው ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አጀንዳውን ደግፎ በመምጣቱ ለፓርቲው ያላቸውን ከፍተኛ ድጋፍ እና አድናቆት እየገለጹ ይገኛሉ።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ጣምራ ዜግነትን በተመለከተ ቀደም ሲል ባካሄደው ጥናት የጣምራ ዜግነት ህግ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መሆኑ ለሀገራችን በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ጂኦ-ፖለቲካዊ ፋይዳዎች የሚያስገኝ መሆኑን እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ አይነተኛ ሚና ሊጫወት እንደሚችል ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህንኑ ጥናት መነሻ በማድረግ የጣምራ ዜግነት ፖሊሲን በፓርቲው የ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ማኒፊስቶ ውስጥ አካቷል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ያሉባቸውን ችግሮች በልዩ ሁኔታ እያጠና የተሻሉ የፖሊሲ አማራጮችን ያዘጋጃል። የጣምራ ዜግነት ፖሊሲ ተግባራዊ መሆን ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑ ቢታወቅም፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከፖሊሲው ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ይታወቃል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በውጭ ሀገር የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ፓርቲው ይፋ ላደረገው የጣምራ ዜግነት ፖሊሲ ላሳያችሁት ጣንካራ ድጋፍ ልባዊ ምስጋናውን እየገለጸ፣
📍ፖሊሲው በሀገራችን ተግባራዊ ሆኖ ዜጎች እና ሀገራችን ከፖሊሲው ተጠቃሚ መሆን ይችሉ ዘንድ በውጭ ሀገር የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወዳጅ፣ ጋደኛ. . . በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ነእፓን ይመርጡ ዘንድ በመወትወት እና በማሳመን የበኩላችሁን እንድትወጡ፣

📍በውጪ ሀገር የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በምትኖሩበት ሀገር የፓርቲውን አባላት/ደጋፊዎች ቁጥር ለማሳደግ እና አደረጃጀቱን ለማጠናከር የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አባል ወይም ደጋፊ በመሆን ፓርቲው በቀጣይ በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ቀጥተኛ ተሳታፊ እንድትሆኑ እና በሀገራችሁ ጉዳይ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ፣

📍የነጻነትና እኩልነት ፓርቲን አቅም ለመገንባት እና የፓርቲውን አፈጻጸም እና ተጽእኖ ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ፣ በገንዘብ እና በሌሎች መንገዶች ድጋፍ እንድታደርግ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በድጋሜ ነእፓ የጣምራ ዜግነት ፖሊሲን በኢትዮጵያ ተግባራዊ ለማድረግ ያቀረበውን ፖሊሲ በመደገፍ ላሳያችሁት ድጋፍ በመላ የፓርቲው አባላት እና አመራሮች ስም ልባዊ ምስጋናችንን እየገለጽን፣ በሀገራችን ነጻነት እና እኩልነትን እውን ለማድረግ በምናደረግው ጥረት ከነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ጎን እንድትቆሙ የአብረን እንስራ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በምርጫው በሚያገኘው ድምጽ ድህረ ምርጫ በሚቋቋመው የሀገራችን መንግስት ውስጥ የጣምራ ዜግነት ፖሊሲ ተግባራዊ ይሆን ዘንድ አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ ለማድረግ ለህዝብ የገባውን ቃል እንደሚፈጸም በድጋሜ ያረጋግጣል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት 11፣ 2018
አዲስ አበባ።

ነእፓ በሶስት ቃል፡ ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ!!
19/05/2026

ነእፓ በሶስት ቃል፡ ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ!!

ሀገራችን አሁን ካለችበት ውስብስብ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ወጥታ፣ ወደ ተሻለ የዴሞክራሲና የእድገት ጎዳና እንድትሸጋገር የሁላችንም ንቁ ተሳትፎና ትክክለኛ ውሳኔ የሚያስፈል...
18/05/2026

ሀገራችን አሁን ካለችበት ውስብስብ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ወጥታ፣ ወደ ተሻለ የዴሞክራሲና የእድገት ጎዳና እንድትሸጋገር የሁላችንም ንቁ ተሳትፎና ትክክለኛ ውሳኔ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ኢትዮጵያዊነትን መሠረት ያደረገ፣ የዜጎችን መብት የሚያስከብርና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ አማራጭ ይዞላችሁ ቀርቧል።

‎ለምን ነፃነትና እኩልነት ፓርቲን እንመርጣለን?
‎✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅

‎❶. እውነተኛ ነፃነትን ለማረጋገጥ
‎እያንዳንዱ ዜጋ ያለ ስጋት ሃሳቡን የሚገልጽባት፣ በፈለገው አካባቢ የመኖርና የመስራት መብቱ የተከበረባት ሀገር ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል። ነፃነት ለጥቂቶች የተሰጠ ስጦታ ሳይሆን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት የሚሰጥ የተፈጥሮ መብት ነው ብለን እናምናለን።

‎➋. ፍፁም እኩልነትን ለማስፈን
‎በብሄር፣ በሃይማኖት፣ በፆታ ወይም በማንኛውም ልዩነት ሳይገደብ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በህግ ፊት እኩል የሚታይበት ስርአት እንገነባለን። የሀገራችን ፀጋዎችና እድሎች ለሁሉም ዜጋ በፍትሐዊነት እንዲዳረሱ እንሰራለን።

‎➌. የሰላምና የህግ የበላይነት
‎ሰላም የሁሉ ነገር መሠረት ነው። እኛ የምንከተለው ፖለቲካ በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ውይይት፣ መቻቻልና በህግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ነው። ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱና ዜጎች በቤታቸውና በስራቸው ዋስትና እንዲኖራቸው እናደርጋለን።

‎❹. ጠንካራ ኢኮኖሚና የስራ እድል
‎የኑሮ ውድነትን ለማቃለል፣ ግብርናን ለማዘመንና ኢንደስትሪውን ለማቀጣጠል ግልፅ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አለን። በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ፕሮጀክቶችን ቀርፀን ተግባራዊ እናደርጋለን።

Address

Bistima

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ - ወሎ Freedom & Equality Party - Wollo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share