03/06/2026
የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን 7ኛው ጠቅላለ ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ መሆኑን ገለጸ
++++++++++++++++
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ መሆኑን ገለጸ።
የምርጫ ታዛበ ቡድን ምርጫውን አስመልክቶ ያዘጋጀውን የመጀመሪያ ደረጃ የምርጫ ምልከታ ሪፖርት ይፋ አድርገዋል።
የኢጋድ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ምርጫ በማዘጋጀትና በማስፈጸም ረገድ ያሳየውን ከፍተኛ አስተዳደራዊና ተግባራዊ አቅም አድንቋል።
የኢጋድ የታዛቢዎች ቡድን ሰብሳቢ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዙቤ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የታዘቡት ምርጫ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት ነው።
ሰብሳቢዋ ከኢትዮጵያ መንግሥት እና ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደረሰው ጥሪ መሠረት 26 አጭር ጊዜ ታዛቢዎችን ያቀፈ ቡድን በማሰማራት ሂደቱን ሲከታተሉ መቆየታቸውን ጠቅሰው፣ በምርጫው የታዩ አስተዳደራዊ ማሻሻያዎችን አድንቀዋል።
ቦርዱ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥም ቢሆን በ501ዱ የምርጫ ክልሎች ውስጥ ወደ 52 ሺህ የሚጠጉ የምርጫ ጣቢያዎችን በተሳካ ሁኔታ ሥራ ላይ ማዋል መቻሉን ቡድኑ በሪፖርቱ አመልክቷል።
ኢፕድ