ባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ Bahir Dar City Administration Police Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahir Dar
  • ባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ Bahir Dar City Administration Police Department

ባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ Bahir Dar City Administration Police Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ Bahir Dar City Administration Police Department, Law enforcement agency, Bahir Dar.

በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።‎የባሕርዳ...
02/06/2026

በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።


የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር‎​ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 1 የምርጫ ክልል እና 164 የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሰላማዊ፣ ስልጡን እና ስኬታማ በሆነ መንገድ ተጠናቋል ብለዋል።

‎ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ የተካሄደው ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ አባላት ምስጋና አቅርበዋል።

ለመላው ሰላም ወዳድ የከተማው ማህበረሰብ፣ከምርጫው መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ማጠቃለያው ድረስ ሕግን በማክበር፣ ሰላምን በማስቀደም እና ከፍተኛ የዜግነት ኃላፊነት ስሜትን በማሳየት ለቆማችሁ፤​ የጸጥታ አካላት ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ የሕዝብን ደህንነት ለመጠበቅና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሌት ከቀን ያለመታከት በቁርጠኝነት ለወጣቹህ ለወረዳቹህ ለደከማችሁ፤ በሂደቱም ላይ ንቁ ተሳትፎ ላደረጋችሁ በሙሉ፤ ​በራሴ እና በፖሊስ መምሪያው ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን እና አክብሮቴን አቀርባለሁ ብለዋል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ምሪያ
የሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://www.facebook.com/BahirDarCityAdministrationPoliceDepartment
🇪🇹" "በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል"🇪🇹

02/06/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በአማራ ክልል በስኬትና በታላቅ ድል መጠናቀቁ ተገለጸ።

በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በከፍተኛ ስኬት ስልጡን እና ህዝባዊ ተሳትፎ በጎላበት መልክ በታላቅ የህዝብ ድል መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ተወዳዳሪ የሌለው ሚና ለተጫወቱት የክልሉ ፖሊስ፣ ለጀግናዉ የመከላከያ፣ የፌደራል ፀጥታና የብሔራዊ ደህንነት አካላት ፣ለክልሉ ሚሊሻና ሰላም አስከባሪ እና ለመላዉ ህዝባችን በሙሉ የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የላቀ ምስጋናና እውቅና አቅርቧል።

ሁሌም ሰላምና ልማትን ቀዳሚ የሚያደርገው የክልሉ ህዝብ የምርጫ ካርድ ከመውሰድ ጀምሮ በምርጫው ዕለት በታላቅ ትዕግስት እና ስነ-ስርዓት ድምፅ እስከመስጠት ድረስ ያሳየው ፍቅርና ሀገር ወዳድነት የታሪክ ማህደር የማይረሳው መሆኑን ገልጿል።

በምርጫው ዕለት ህብረተሰቡ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት በክልሉ በሚገኙ የምርጫ ክልሎች ያከናወነው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ያለምንም መሰላቸት እስከ ምሽት ሰአት መከናወኑን አረጋግጧል።

ህብረተሰቡ ረጅም ሰልፎችን በታጋሽነት በመሰለፍ፣ የመምረጥ መብቱን በአግባቡ መጠቀሙ የሰለጠነ ዴሞክራሲያዊ ባህሉን ያሳየበትና ለምርጫው ስኬታማነት ትልቁን ድርሻ ያበረከተበት መሆኑንም ጠቁሟል።

ምርጫው የክልሉን ህዝብ ብስለት፣ ሰላም ወዳድነት እና ለሀገር ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ዳግም ለዓለም ያስመሰከረበት ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑንም ዋና ጠቅላይ መምሪያው አመላክቷል።

ሀገራዊ ምርጫው በስኬት ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሌት ከቀን የህግ ማስከበር ስራቸውን በብቃት ለተወጡት ለክልሉ ፖሊስ አባላት፣ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለፌዴራል ፖሊስ፣ለብሔራዊ ደህንነት አካላት፣ለክልሉ ሚሊሻና ሰላም አስከባሪ አካላት በሙሉ ታላቅ አክብሮትና እውቅና ሰጥቷል።

የጸጥታ ኃይሉ ሂደቱን በበላይነት በመምራትና የእያንዳንዱን አካባቢ ህብረተሰብ በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ በማንቀሳቀስ፣ ከህዝብ የተውጣጡ የሰላም ኮሚቴዎችንና አደረጃጀቶችን ከራሱ የጸጥታ መዋቅር ጋር በማስተሳሰር የጋራ የሰላም ግንባር መፍጠር በመቻሉ ሰላሙን ማረጋገጥ መቻሉንም አረጋግጧል።

ይህንን ስራ ስኬታማ ለማድረግ የጸጥታ ኃይሉ አባላት ሌት ከቀን ያሳዩት ከፍተኛ ልፋት፣ ድካም እና ተጋድሎ በአንዳንድ ቦታዎች የምርጫውን ሂደት ለማደፍረስና ሁከት ለመፍጠር አልመው የተንቀሳቀሱ ህገ-ወጥ አካላትን የጥፋት ሴራ ቀድሞ በተዘጋጀ ስልታዊ የመከላከል እቅድ ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉንም አመላክቷል ።

የጸጥታ ኃይሉ የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ የመወጣት ጀግንነት፣ ሙያዊ ብቃት እና የገባውን ቃልኪዳን በታማኝነት በመፈጸም የህዝቡን ደህንነት በልዩ ጥንቃቄ የማስጠበቅ ስራ፤ ከተቋማዊ ኩራት ባሻገር ለክልሉና ለሀገሪቱ ታላቅ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር በመሆኑ ላቅ ያለ ምስጋናና እውቅና ሰጥቷል።

ምርጫውን ለማወክ የሞከሩ ማናቸውንም የፀረ-ሰላም ኃይሎች የጥፋት አጀንዳ ሙሉ በሙሉ ያከሸፈ ታላቅ የህዝብ ድል የተመዘገበው ህዝቡ ያሳየው አስተዋይነት እና የሰላም ባለቤትነት ስሜት በመኖሩ እንደሆነም አክሏል።

ለታሪካዊ ድሉ መገኘት ህዝቡ ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም፣ መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና ለሰላም ጥበቃው ግንባር ቀደም ጠባቂ በመሆን ያሳየው ጠንካራና የተቀናጀ ጥምረት ዋነኛ መሠረት ነበር ተብሏል።

በምርጫው ወቅት የታየውን መልካም የህዝብና የፖሊስ ቅንጅታዊ አሰራርና አደረጃጀት ይበልጥ በማጠናከር የክልሉን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ቀጣይም በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል።

ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ለሲቪክ ማህበራት፣ ለብዙሃን መገናኛ አካላት ፣ ለዉጭና የአገር ዉስጥ ታዛቢዎች እና ለሰላም ወዳዱ ማህበረሰብ በሙሉ በድጋሚ የላቀ ምስጋና በማቅረብ፤ የተጀመረውን የሰላምና የዴሞክራሲ ጉዞ በጋራ ለማስቀጠል የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ጥሪ አስተላልፏል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
ባህር ዳር

01/06/2026
የወንጀል ምርመራ አቅምን ለማሳደግ  ለመርማሪ ፖሊሶች  ሙያዊ ስነ-ምግባርን ተላብሶ ዜጎችን እንዲያገለግሉ  የስብዕና ግንባታ ስልጠና ተሰጠ ።ግንቦት/2018 ዓ/ም ባህርዳር ከተማ አሰተዳደር ...
24/05/2026

የወንጀል ምርመራ አቅምን ለማሳደግ ለመርማሪ ፖሊሶች ሙያዊ ስነ-ምግባርን ተላብሶ ዜጎችን እንዲያገለግሉ የስብዕና ግንባታ ስልጠና ተሰጠ ።

ግንቦት/2018 ዓ/ም ባህርዳር ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ (የኮሙኑኬሽን እና ህዝብ ግንኙነት)
‎፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የሥራ መመሪያ እና የመክፈቻ ንግግር ያስተላለፉት
የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዪ ልዮ ወንጀሎች እና የኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ይብሬ አሊ አንደገለፁት ባህር ዳር የክልሉ ርዕሰ-ከተማ በመሆኗ በርካታና የተለያየ ችግር ያለባቸው ባለጉዳዮች ወደ ፖሊስ ጣቢያዎች እንደሚመጡ በመግለጽ እያንዳንዱ ምርማሪ ባለጉዳዮችን በአግባቡ ተቀብሎ በጥሩ ስነ-ምግባር ማስተናገድ እንዳለበት በጥብቅ አሳስበዋል።

* በመሳቢያ ውስጥ የሚቀመጥ መዝገብ አይኖርም" በአዲሱ ሪፎርም መሰረት በፖሊስ እጅ ያሉ መዝገቦች በየወሩ መጨረሻ ኦዲት ይደረጋሉ። መዝገቦችን በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ባለመላክ የስራ መዘግየት በሚፈጥሩ ምርማሪዎች ላይ ጥብቅ የስነ-ምግባር እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።

* በተለይ የቆዩ መዝገቦችን በፍጥነት ማጠናቀቅ፦ ከ2016 ጀምሮ የዞሩ እንዲሁም በ2018 በጀት ዓመት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የምርመራ መዝገቦች በአስቸኳይ ተጠናቀው ለፍትህ አካላት መላክ እንዳለባቸው መመሪያ ተሰጥቷል።

አያይዘውም የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ በምስክር እና በተከሳሽ እጥረት ምክንያት የተዘጉ መዝገቦችን በድጋሚ በማስከፈትና በማጠናቀቅ የህግና የፍትህ የበላይነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አመራሩ አሳስበዋል።

ይህ የምክክርና የስልጠና መድረክ በፖሊስ መምሪያው ስር በሚገኙ ሁሉም ጣቢያዎች የተሻለ የአገልግሎት አሰጣጥ ለመዘርጋትና የወንጀል ምርመራ ጥራትን ለማሳደግ ያለመ መሆን አለበት በማለት የመክፈቻ ንግግራቸ አመላክተዋል።

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ም/መምሪያ አዛዥ ኮማንደር መኳንት አድማስ አጭር የ9ወር የምርመራ ሪፖርት እንዳመላከቱት በምርመራ ጥራት ዙሪያ ትኩረት ሰጠን መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

የምርመራ ሙያ የዜጎችን እንባ ማበሻ እና የፍትህ የበላይነት መገለጫ በመሆኑ በተለይ ሙያዊ ስነ-ምግባርን ተላብሶ ማህበረሰቡን እንዲያገለግል ተከታታይ የሆኑ የስብዕና ግንባታ ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

ተቋሙ የምርመራ ሥራውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እያከናወናቸው ካሉ ቁልፍ ተግባራት መካከል የምርመራ ሥራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ፣ ሳይንሳዊ ዘዴዎችን የተከተሉ የምርመራ ሂደቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አዛዡ ጠቁመዋል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የሙስና ወንጀል ምርመራ ዋና/ክፍል ኃላፊ
ኮማንደር መልሰው አበበ በስነ-መግባር ዙሪያ ስለልጠና የሰጡ ሲሆን
**ኢ/ር የሽዋስ ገበየሁ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የልዩልዩ ወንጀል ምርመራ ዋና/ክፍል ኃላፊ ባለጉዳይ መስተንግዶ ዙሪያ ስልጠና ተሰጧል።
በመጨረሻም የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የሰው ሃብትልማት መምሪያ የመለዮ ለባሽ
ዋና ክፋል ኃላፊ ኮማንደር ጌትነት አበበ የዲስፕሊን መመሪያ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ Bahir Dar City Administration Police Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share