19/05/2025
ማን ተዋክቦ እጅ ሰጠ? ማንስ ሚሽኑን ጨርሶ ወደ ቤቱ ተመለሰ ጊዜ መልስ ሰጠን።
ጋሽ አሰግድ መኮነን በገዛ ወንድሞቼ ባላቸዉ ስመ አማራ ከሃዲዎች ሴራ ተዋክቦ ምንም ማድረግ በማይችልበት ሁኔታ ዉስጥ ሆኖ በጠላት እጅ ወደቀ። በሰአቱ እንዴት እጅ ይሰጣል ለምን ራሱን አይሰዋም ተብሎም ተሾፈበት። ጋሽ አሰግድ መኮንን በዛ ዕድሜዉ ለአማራ ህዝብ መፃይ ዕድል መደላድል ለመፍጠር በረሃ ሲወርድ ድፍን አማራን እንጅ ጎጥን አዉቅም ነበር።ከሱ በተቃራኒ የሆኑት ግን አስበሉት። የሆነዉም ሆነ እና በሳቁበት ጥርስ ማልቀስ ይመጣል እና ምንም ቢሆን አማራ ነዉ እና ጋሼ በጠላት እጅ ሲገባ ማዘን መተከዝ ሲገባቸዉ ቁራ አማራዎች በተከፈለዉ ዋጋ አፌዙ፣ተሳለቁም። የእነሱ ተራ ሲሆን ግን አባት ፣አያት ወይም ቅድመ አያቶቻቸዉ ሰምተዉት የማያዉቁትን ትጥቅንም እጅንም አንስቶ መ'ማረክ አመጡ። የብልፅግና እና የቁራ አማሮች ሚዲያዎች ጋሽ አሰግድ በሰአቱ ከድቶ ነዉ የገባዉ እያሉ ቢጮሁ ቢያላዝኑም ጀግናዉ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን ግን በጠላት እጅ ከወደቀ ወዲህ ቤተሰቦችም ሆነ የቅርብ ወዳጆቹ አገዛዙ የት እንዳደረሰዉ በዉል የሚያዉቁት ነገር የለም። ጋሼ ከድቶ እጅ ቢሰጥማ ኖሮ ቃሪያ ሱሪ ተገዝቶለት ፣ፂሙን ተላጭቶ ፣የጣልያን ሰደርያ ለብሶ፣የቱርክ ጫማ ገድግዶ፣ ካድሬ ከቦት በአደባባይ ወክ ያደርግ በአደባባይ ከከተማ ከተማ ይንቀሳቀስ ነበር።" አሰግድ መኮንን ተካደ ወይስ እጅ ሰጠ ? መልሱን ጊዜ የሚፈታዉ ይሁንና..." እንዳለዉ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ይኸዉ ጊዜ መልሱን ሰጠን። ጎጥ የማያዉቀዉ ተራማጁ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን ተከዳ በጎጥ የሚያምኑት ቆሞ ቀረች እጅ ሰጡ ይኸዉ ነዉ። እንደዉ ለነገሩ እንዲህም እንዲያ ይባል አንጅ ይሄ ጊዜ ወሳኝ የትግሉ መታጠፊያ በመሆኑ እንክርዳዱ ከስንዴዉ እየተበጠረ ያለዉ አፋብሃ የሚሉት የጎጠኞች እና የቆሞ ቀሮች ዛራ መድሀኒት ይፋ ከሆነ በኋላ በመሆኑ ትግሉ ይበልጥ ጥንካሬ እና ወጥነት ይዞ እንዲሄድ ያግዘዋል ባይ ነን።
አማራነት እስከ ቀራኒዮ!! for people of amhara