Debre Birhan Agricultural Research Center-ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahir Dar
  • Debre Birhan Agricultural Research Center-ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል

Debre Birhan Agricultural Research Center-ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል Debre Birhan Agricultural Research Center (DBARC) is a governmental research institution located in Debre Birhan, Amhara Region, Ethiopia.

የወተት ምርትን በዘመናዊ የባዮቴክኖሎጂ ዘዴ ለማሳደግ የሚያስችል «ሞዴል የወተት መንደር» ምስረታ ስራ መጀመሩ ይፋ ሆነ!‎በክልል ካፒታል በጀት እና በብሄራዊ እንስሳት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ፕ...
30/05/2026

የወተት ምርትን በዘመናዊ የባዮቴክኖሎጂ ዘዴ ለማሳደግ የሚያስችል «ሞዴል የወተት መንደር» ምስረታ ስራ መጀመሩ ይፋ ሆነ!

በክልል ካፒታል በጀት እና በብሄራዊ እንስሳት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ የወተት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል፣ መንደር መሰረት ያደረገ የዝርያ ማሻሻል ስራ መጀመሩ ይፋ ተደርጓል። በአንጎለላና ጠራ ወረዳ ጨኪ ቀበሌ የተጀመረው ይህ በምርምር ላይ የተመሰረተ የዝርያ ማሻሻል ስራ፤ በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ስር በሚገኘው የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል እና በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ስር በሚገኘው የቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል ጥምረት የሚከናወን ነው።

‎የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል እንስሳት ቴክኖሎጂ አቅርቦት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተርና የማዕከሉ ተወካይ አቶ ልዑልሰገድ አለማየሁ እንደገለጹት፤ ስራው የላሞች ልየታን፣ ስልጠናን እና ቋሚ የወተት መንደር ምስረታን በማካተት ለሌሎች አካባቢዎች ሞዴልና ማስተማሪያ እንዲሆን ታስቦ የተጀመረ መሆኑን ተናግረዋል። የአንጎለላና ጠራ ወረዳ ተወካይ አቶ በሻህ አጉኔ በበኩላቸው፤ አርሶ አደሩ ይህንን ቴክኖሎጂ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ምርታማነቱን ሊያሳድግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎ይህ በእንስሳት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ዘርፍ የተጀመረው ስራ በተመሳሳይ ጊዜ ወደ ድሪ (Estrus Synchronization) እንዲመጡ እና ፆታው በተለየ የኮርማ ዘር (Sexed Semen) የሰው ሰራሽ ማዳቀል ቴክኖሎጂዎችን በማቀናጀት ጥቅም ላይ የሚያውል ነው። ቴክኖሎጂው በተለይ እስከ 90 በመቶ የሚደርሱ ሴት ጥጃዎችን ለማግኘት ማስቻሉ፣ የበሽታ ስርጭትን መቀነሱ እና የመተኪያ ላሞችን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ለመቆጣጠር መርዳቱ ዋነኛ ጥቅሞቹ እንደሆኑ ተገልጿል።

‎የሰው ሰራሽ ማዳቀል (AI) ስራ ቆየት ያለ ቢሆንም፣ ከአጠቃቀም ችግሮች ጋር ተያይዞ የሚጠበቀውን ያህል ውጤት እንዳልተገኘበት በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል ተመራማሪና እንስሳት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ፕሮግራም ብሔራዊ አስተባባሪ ዶ/ር ሰይድ አሊ አስታውሰዋል። በቢሾፍቱ አካባቢ ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ጥሩ ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው መንደርን መሰረት በማድረግ የዚህን አካባቢ አ/አደር ተጠቃሚ እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል። ለውጤታማነቱም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል ።

‎የማዕከሉ የእንስሳት ጤና ተመራማሪው ዶ/ር ቸኮል ደምስ በበኩላቸው፣ ሁሉም እንስሳት በአንዴ ለቴክኖሎጂው ብቁ ላይሆኑ እንደሚችሉ ጠቁመው፤ ለቀጣይ ብቁ እንዲሆኑ በአመጋገብና በጤና አያያዝ እንዲሻሻሉ ተደርገው እንደሚመረጡ ገልጸዋል። በመሆኑም አርሶ አደሮች የመመረጣቸውን ዕድል በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባና ቋሚና ሞዴል የወተት መንደር ለመመስረት የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም ተናግረዋል። የሚወለዱት ጥጆች ሴት መሆናቸው ትልቅ ጥቅም እንዳለውም አብራርተዋል።

‎በዚሁ የቴክኖሎጂ ትግበራ/ሽግግር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የደብረ ብርሃንና የቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከላት ተመራማሪዎች፣ የሰሜን ሸዋ ዞን እንዲሁም የአንጎለላና ጠራ ወረዳ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት መምሪያና ጽህፈት ቤት ባለሙያዎችና የአካባቢው አርሶ አደሮች በጋራ ተገኝተዋል።

አማራጭ የመረጃ ምንጮቻችን ይወዳጁ
Telegram
https://t.me/dbarc_2016
Youtube
https://youtube.com/?si=K-4ZMq86IVQiP_Eo
Facebook
https://www.facebook.com/share/16kWNBZdYE
LinkedIn
https://www.linkedin.com/.../debre-birhan-agricultural.../

‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በደብረ ብርሃን ምርምር ማዕከል የስራ ጉብኝት አደረጉ‼‎‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን በደብ...
28/05/2026

‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በደብረ ብርሃን ምርምር ማዕከል የስራ ጉብኝት አደረጉ‼


‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን በደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል እየተከናወኑ ያሉ የምርምርና የልማት ስራዎችን በአካል ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል።
‎በጉብኝቱ ወቅት በማዕከሉ እየተሰሩ ያሉ በርካታ የምርምርና የቴክኖሎጂ ብዜት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን፣ በተለይም የወተት ልማት፣ የበግና የፍየል ምርምር ስራዎችና የእንስሳት ማቆያ በረቶች ያሉበት ደረጃ ተገምግሟል።

‎ከዚህም ባሻገር የተመረቱ የምርምር ውጤቶችን በጥራት ለመጠበቅ የሚያገለግለው የዘር ማቆያ መጋዘንና ጥሩ ውጤት እየታየበት ያለው የምግብ ገብስ የብዜት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን፤ አጠቃላይ የምርምር ስራውን ለማዘመንና ምቹ ለማድረግ በማዕከሉ ግቢ ውስጥ እየተገነቡ ያሉ የውስጥ መሰረተ ልማቶችና የተለያዩ የምርምር ፋሲሊቲዎችም በከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ ተጎብኝተዋል።

‎በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተገለጸው፣ የምርምር ማዕከላት የተጣለባቸውን አገራዊና ክልላዊ ኃላፊነት በተሟላ ሁኔታ መወጣት እንዲችሉ የምርምር ፋሲሊቲዎችና መሰረተ ልማቶች ሊሟሉላቸውና ሊዘምኑ እንደሚገባ ተመላክቷል።

‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰማኝ አስረዴ (ዶ/ር) በማዕከሉ እየተከናወኑ ያሉ የምርምርና የመሰረተ ልማት ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸው፤ ማዕከሉ የጀመራቸውን የምርምር ፋሲሊቲዎች የማሟላትና የማዘመን ስራዎች በይበልጥ እንዲሳኩ ኢንስቲትዩቱ የሚጠበቅበትንና የድርሻውን ድጋፍ በቁርጠኝነት እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ! ‎‎በአማራ ግብርና ምርምር...
25/05/2026

የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ!

‎በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የምርምር ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። ማዕከሉ ይህንን ያመለከተው በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የስንዴ እሴት ሰንሰለት ልማት (CREW) ፕሮጀክት አማካኝነት በደጋው አካባቢ በመስኖ የተከናወኑ የምርምር ስራዎችን ለመገምገም በተካሄደ የመስክ ምልከታና የጋራ ግምገማ መርሃ ግብር ወቅት ነው።

‎የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደጉ ተመቸ የእንኳን ደህና መጣችሁ አስተላልፈው ከዚህ በፊት በመስኖ ስንዴ በቆላማው አካባቢ ማዕከሉ ዉጤታማ ስራዎች መስራቱን አስታውሰው አሁን ደግሞ በደጋማው አካበባቢ ያሉ አ/ደሮች በቴክኖሎጅ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምርምሮች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የመነሻ ዘር ማቅረብ አንዱ ተልዕኮአችን በመሆኑ የመነሻ ዘር እያባዛን ለአባዥ ተቋማት እያቀረብን እንገኛለንም ብለዋል። ምንም እንኳን ማዕከሉ በቂ የማባዣ መሬት ባይኖረውም የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ከዚህ በተሻለ ለመስራት ጥረት እንደሚደረግም ጨምረው ገልጸዋል።
‎በዕለቱ በተደረገው የመስክ ምልከታ በደጋማው አካባቢ የተከናወኑ የዳቦ ስንዴ ማላመድና የመነሻ ዘር ብዜት የመስኖ ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን፤ እንዲሁም የማህበረሰብ አቀፍ የዘር ብዜት ስራዎችም ተገምግመዋል። የሚመለከታቸው ተመራማሪዎችም ስለ ስራዎቹ ማብራሪያ በመስጠት ተሳታፊዎቹ በቂ ግንዛቤ እንዲኖር አድርገዋል።

‎የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ም/ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሰማኝ አስረዴ በጉብኝቱ የተመለከቷቸው ስራዎች ውጤታማና የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸው፣ ማዕከሉ የዘር ማባዣ መሬት ሳይኖረው በአማራጭ መንገዶችና ከትምህርት ተቋማት ጋር በውል ስምምነት (MOU) በቅንጅት መስራቱን አድንቀዋል። ይህም ቴክኖሎጂን ለማስፋፋትና ተደራሽ እንዲሆን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

‎በመጨረሻም ክልሉ ያለበትን የዘር አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ፤ የሚመረቱ ምርቶች ወደ ዘር ሰንሰለቱ እንዲገቡና ገበያው በሚፈልጋቸው ዝርያዎች ላይ በትኩረት በመስራት ማዕከሉ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

‎በዚህ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የመስክ ምልከታና ጉብኝት ላይ የኢንስቲትዩቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር ሰማኝ አስረዴ (ዶ/ር)፣ የዘር ምርምርና ቴክኖሎጂ ብዜት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አዕምሮ በዛብህ (ዶ/ር)፣ የሶሺኦ-ኢኮኖሚክስና ምርምር ስርፀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ያልፋል ተመስገን (ዶ/ር)፣ የCREW ፕሮጀክት አስተባባሪ ቸርነት አለም (ዶ/ር)፣ የማዕከሉ የማኔጅመንት አባላት፣ ተመራማሪዎችና የደብረ ብርሃን ትምህርት ኮሌጅ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

አማራጭ የመረጃ ምንጮቻችን ይወዳጁ‼️
Telegram
https://t.me/dbarc_2016
Youtube
https://youtube.com/?si=K-4ZMq86IVQiP_Eo
Facebook
https://www.facebook.com/share/16kWNBZdYE
LinkedIn
https://www.linkedin.com/.../debre-birhan-agricultural.../

ምርምር ማዕከላት ማስተማሪያ፣ ሞዴልና የቴክኖሎጂ ምንጭ እንዲሆኑ መዘመን እንደሚገባቸው ተገለጸ!‎‎በደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል በካፒታል በጀት ድጋፍ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያ...
15/05/2026

ምርምር ማዕከላት ማስተማሪያ፣ ሞዴልና የቴክኖሎጂ ምንጭ እንዲሆኑ መዘመን እንደሚገባቸው ተገለጸ!

‎በደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል በካፒታል በጀት ድጋፍ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የምርምርና የመሰረተ ልማት ስራዎች የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል። በመስክ ምልከታው ወቅት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ ምርምርና ልማት፣ የዘር ብዜትና የተለያዩ መሰረተ ልማት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን በሚመለከታቸው ተመራማሪዎችም ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።

‎ማዕከሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ጭምር እውቅና ያገኘበትን "መንደርን መሰረት ያደረገ የዝርያ ማሻሻል ስራ" ይበልጥ በማጠናከር አ/አደሩንና አርቢውን ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም የሌሎች አካላት መማሪያ እንዲሆን እየተሰራ ይገኛል። በተለይም በቀይ ስጋ ምርቱና በፈጣን እድገቱ የሚታወቀውን የዶርፐር በግ ዝርያ ከአካባቢው ዝርያ ጋር በማዳቀል “ኢትዮጵያዊ ዶርፐር” የመፍጠር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል። ይህ የምርምር ውጤት አርሶ አደሩና አርቢው በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ምርቱን ለገበያ እንዲያቀርብና ለኤክስፖርት የሚሆን ጥራት ያለው ስጋ እንዲያመርት የሚያስችል በመሆኑ፣ ማዕከሉን በቴክኖሎጂ ምንጭነት ተጠቃሽ ያደርገዋል።

‎በሌላ በኩል ለተለያዩ አባዥ ተቋማት የሰብልና መኖ የመነሻ ዘር (Early Generation Seed) በማቅረብ ጉልህ አስተዋጽዖ እየተወጣ ሲሆን በቀጣይም በትኩረት እንደሚሰራ ተብራርቷል።

‎የግብርና ምርምር ማዕከላት ለሌሎች አካላት እንደ ማስተማሪያና ሞዴል ማገልገል እንዲችሉ፣ እንዲሁም ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ምንጭ በመሆን ዘርፉን እንዲመሩ የመሰረተ ልማት አቅማቸውን በማሳደግና አዳዲስ አሰራሮችን በመተግበር ረገድ ሊዘመኑ እንደሚገባ ተገልጿል።
‎ከክልል ገንዘብ ቢሮ የመጡት ባለሙያዎች አቶ ሙሉሰው አይቸውና ወ/ሮ አምሳል ደሳለኝ የሰራተኛውን ተነሳሽነት አድንቀው፣ የግብርና ምርምር ስራዎች የክልሉ መንግስት ዋነኛ ትኩረት መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ማዕከሉ ለሌሎች ተቋማትና ለአርሶ አደሩ እንደ ማስተማሪያና ሞዴል ማገልገል እንዳለበት ገልጸዋል፤ ለዚህም የሚቀርቡ የፕሮጀክት ፕሮፖዛሎች ጠቀሜታውን በግልጽ ማቅረብና በካፒታል በጀት የሚከናወኑ መሰረተ ልማቶች ተለይተው ሊቀርቡ እንደሚገባም አሳስበዋል። በተለይም የመነሻ ዘር ብዜትን ለማሳለጥ አስፈላጊ ግብዓቶች ተለይተው በፕሮጀክት መልኩ ማቅረብ እንዲሁም የመፈጸም አቅምን ማሳደግ እንደሚገባም ጨምረው ገልጸዋል።

‎የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደጉ ተመቸ የገንዘብ ቢሮ ባለሙያዎቹ ስራዎቹን በአካል ተገኝተው በማየታቸውና ሙያዊ አስተያየታቸውን በመስጠታቸው ምስጋና አቅርበዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ማዕከሉን ይበልጥ ለማዘመንና ብቁ የቴክኖሎጂ ምንጭ ለማድረግ እንዲቻል የማዕከሉ ሁለገብ ህንጻ፣ የዙሪያ አጥርና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ በክልሉ መንግስት በትኩረት እንዲታዩ ባለሙያዎቹ የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

‎በመስክ ጉብኝቱ ላይ የማዕከሉ ዳይሬክተርን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላት እና ከክልሉ ገንዘብ ቢሮ የመጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በመጨረሻም፣ የተጀመሩ ውጤታማ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ማዕከሉ በቴክኖሎጂና በመሰረተ ልማት ዘምኖ ለሀገሪቱ የግብርና ሽግግር የላቀ አርአያ እንዲሆን በትብብር መስራት እንደሚገባ በማጠቃለያ ተነስቶ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

አማራጭ የመረጃ ምንጮቻችን ይወዳጁ‼️
Telegram
https://t.me/dbarc_2016
Youtube
https://youtube.com/?si=K-4ZMq86IVQiP_Eo
Facebook
https://www.facebook.com/share/16kWNBZdYE
LinkedIn
https://www.linkedin.com/.../debre-birhan-agricultural.../

13/05/2026
08/05/2026
በምርምር የወጡ ቴክኖሎጂዎችን  በሰርቶ ማሳያ ለማስተዋወቅ እና ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ በምርምር የወጡ ቴክኖሎጅዎችን በሰርቶ ማሳያ ለማ...
07/05/2026

በምርምር የወጡ ቴክኖሎጂዎችን በሰርቶ ማሳያ ለማስተዋወቅ እና ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ

በምርምር የወጡ ቴክኖሎጅዎችን በሰርቶ ማሳያ ለማስተዋወቅ እና ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ የፕሮጀክቶች፣ግብርና ቢሮ እና ምርምር ተቋማት በሰርቶ ማሳያ አሰራር ላይ በትብብርና ቅንጅት ለመስራት የውይይት መድረክ ተካሂዷል ።

በግብርና ምርምር-ሥርዓት ውስጥ በምርምርና በአርሶ አደር ማሳ ደረጃ ተሞክረው የወጡ ቴክኖሎጂዎችን ወደ አርሶአደሩ ማሳ እንዲደርሱ ለማድረግ የሰርቶ ማሳያ ቦታዎች ወሳኝ ሚና ቢኖራቸውም በተቋማት መካከል በቂ ቅንጅትና ትብብር ባለመኖሩ ቴክኖሎጂዎች በተፈለገው ደረጃ እየተስፋፉ አለመሆኑን ተጠቁሟል።

የፕሮጀክቶችን፣ ግብርና ኤክስቴንሽን እና የምርምር ተቋማትን የቅንጅት መድረኮችን ማጠናከር የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ እምርታ እንደሚኖረው የተገለፀ ሲሆን በምርምር የተገኘ ቴክኖሎጂ ከምርምር እስከ አርሶአደሩ ማሳ ላይ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ ያለው የመረጃ፣ የግብዓትና የክትትል ሰንሰለትን የምያጠናክር ነው ተብሏል፡፡

አዳዲስ ሆነ ነባር በምርምር የተገኙ የሰብል ዝርያዎችም ሆኑ የተሸሻሉ አሰራር ምክረ ሃሳቦች በአጭር ጊዜ ወደ አርሶአደሩ እጅ እንዲደርሱ የተቋማት የተናበበ ዕቅድ ሊኖራቸው እንደሚገባም በውይይት መድረኩ ተነስቷል፡፡

በክልል ደረጃ የምርምር ተቋማት፣የግብርና ኤክስቴንሽን እና ሌሎችፕሮጀክቶች በሰርቶ ማሳያ አሰራር እና ተሳትፎ የሚያረጋግጥ ቋሚ ፕላትፎርሞችን መመሥረት እንደሚገባም ተጠቁሟል።

ውጤታማና ቀጣይነት ያለው የሰርቶ ማሳያ ሥርዓት እንዲኖር ምርምርተ ቋማት በጋራ በማስተባበር የሰርቶ ማሳያ ማሳዎችን እንዲለዩ፣ቴክኖሎጂዎችን በንጽጽር ማሳየት እንዲችሉ ማድረግ፣ የሰርቶ ማሳያ ውጤቶችን ማስተዋወቅ፣ በሰርቶ ማሳያ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችንበቀጥታ ለማጋራት ዲጂታል መድረክ መቋቋም፣ በጀት፣ ቁሳቁስና የሰው ኃይል አቅምን በማጋራት የሰርቶ ማሳያ አሰራርን ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡

በመድረኩ ከክልል የግብርና ኤክስቴንሽን ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ ከምርምር ኢንስቲትዩቱ የመጡ ተመራማሪዎች፣ የምርጥ ዘር አባዥ ድርጅቶች እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የመጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

Amhara Agricultural Research Institute-ARARI

የቻይና ኤይድ በኢትዮጵያ እና አማን ፋርም የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የምርምር ስራዎችን ጎበኙ።የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ከቻይና ኤይድ (CHINA AID) እና አማን...
19/04/2026

የቻይና ኤይድ በኢትዮጵያ እና አማን ፋርም የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የምርምር ስራዎችን ጎበኙ።

የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ከቻይና ኤይድ (CHINA AID) እና አማን ፋርም ከእንስሳት ሕክምና፣ ከአትክልትና ፍራፍሬ፣ ከቴክኖሎጂ ስርጭት፣ ከመስኖ፣ እንዲሁም ከዘመናዊ መሣሪያዎችን መገጣጠም ተውጣጠው ለመጡ የባለሙያዎች ቡድን በምርምር ማዕከሉ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የምርምር ስራዎችን አስጎብኝቷል።

ባለሙያዎቹ በማዕከሉ የእንስሳት ጤና፣ ስነ-ተዋልዶ እና ሥነ አመጋገብ ላቦራቶሪዎችን፣ በግቢው ውስጥ ያሉ የምርምር በጎችን፣ ፍየሎችንና የወተት ከብቶችን እንዲሁም በመስኖ እየለሙ ያሉ የመኖ ልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደጉ ተመቸ እና የእንስሳት ቴክኖሎጂ አቅርቦት ዳይሬክቶሬት አቶ ልዑልሰገድ አለማየሁ ከሌሎች ባለሙያዎች ጋር በጋራ ማዕከሉ እያከናወናቸው ያሉ የምርምር ስራዎች ለቡድኑ ገለፃ አድርገዋል።

ጎብኝዎቹ በምርምር ማዕከሉ በተለይም በበግ፣ ፍየልና ወተት ላሞች የምርምር ሥራዎች ላይ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ እና በተገኙ ውጤቶች በከፍተኛ ሁኔታ መደሰታቸውን የገለፁ ሲሆን በተለይም እጅግ ውድ የሆኑትን የዶርፐር በጎች እና የቦር ፍየሎች ዘር አቆይቶ መያዙን አመስግነዋል። ዝርያዎቹ ለክልሉና ለአገሪቱ እጅግ ጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በአጠቃላይ በማዕከሉ ያሉ እንስሳቶች በጥሩ አቋም ላይ መሆናቸውንም መስክረዋል።

የልኡካን ቡድኑ የቻይናን ተሞክሮ በማካፈል ወደፊት በምርምር ማዕከሉ መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮች ገንቢ አስተያየት ሰጥተው በጋራ ለመስራትም ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በቀጣይም በዝርያ ማሻሻል፣ በባዮቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በበሽታ መቆጣጠርና መከላከል በተለይም በእርባታው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ላይ የሚገኘውን የጉበት ትል በሽታ በተመለከተ ማዕከሉ ከታዋቂ የቻይና ምርምር ተቋማት ጋር በጋራ መስራት ስለሚቻልባቸው ሁኔታ ለማመቻቸት ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

በተጨማሪም የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮቸና ለሌሎች ተጠቃሚዎች በሚፈለገው ልክ ተደረሽ ለማድረግ ከግል ባለሀብቶች ጋር ጠንካራ ትስስር በመፍጠር መስራት ውጤታማ እንደሚያደርግ እንዲሁም የጉበት ትልን ለማከም ጥራት ያላቸውን መድኃኒቶች ወደ ሀገር እንዴት ማስገባት እንደሚቻል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የማጠቃለያ ውይይት ተካሂዶ የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደጉ ተመቸ ጎብኝ ቡድኑ ማዕከሉንና ስራዎችን በመጎብኘታቸው፣ ልምዳቸውን በማካፈላቸውና ወደፊትም በጋራ ለመስራት ፍላጎት ማሳደራቸውን አመስግነው የጉበኝትና ውይይት ፕሮግራሙ ተጠናቋል፡፡

አማራጭ የመረጃ ምንጮቻችን ይወዳጁ‼️
Telegram
https://t.me/dbarc_2016
Youtube
https://youtube.com/?si=K-4ZMq86IVQiP_Eo
Facebook
https://www.facebook.com/share/16kWNBZdYE
LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/debre-birhan-agricultural-research-center-dbarc/

‎ለማዕከሉ ሠራተኞችና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ !‎‎በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል  እንኳን ለጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ...
11/04/2026

‎ለማዕከሉ ሠራተኞችና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ !

‎በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል እንኳን ለጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል ።

‎በዓሉ የሰላም፣የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የስኬት እንዲሆንላችሁ ማዕከሉ ከልብ ይመኛል!

‎መልካም በዓል!

‎ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል!

Address

Bahir Dar
112

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan Agricultural Research Center-ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Debre Birhan Agricultural Research Center-ደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል:

Share