Felege Hiwot Comprehensive Specialized Hospital

Felege Hiwot Comprehensive Specialized Hospital Felege Hiwot Comrehensive Specialized Hospital is giant Hospital which is found in Amhara Region.

የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከኢትዩጵያ ጤና ምርምር ኢንስትቲዩት(EPHI) እውቅና ተበረከተለት ።   ሆስፒታሉ በላብራቶሪ ዘርፍ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ የBioseft...
24/03/2026

የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከኢትዩጵያ ጤና ምርምር ኢንስትቲዩት(EPHI) እውቅና ተበረከተለት ።
ሆስፒታሉ በላብራቶሪ ዘርፍ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ የBiosefty እና Slemta ውድድር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ እውቅናና ሽልማት ተበርክቶለታል።
ተቋሙ በቀጣይ የላብራቶሪ አገልግሎቱን በምርመራ አይነት ብዛት ጥራት እና ሌሎች ተከታታይ የማሻሻያ ስራወችን በመስራት የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ዘርፈ ብዙ ስራወችን የሚያከናውን ይሆናል።

ምስጋና ለሆስፒታላችን ሀኪሞችየ30 አመት ታካሚ ከልጅነት ጅምሮ  በቃጠሎ ምክንያት  የመጣ ችግር በዛሬው ዕለት በሆስፒታላችን የተሳካ ቀዶ ህክምና  የተደረገላት ሲሆን አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ...
10/03/2026

ምስጋና ለሆስፒታላችን ሀኪሞች

የ30 አመት ታካሚ ከልጅነት ጅምሮ በቃጠሎ ምክንያት የመጣ ችግር በዛሬው ዕለት በሆስፒታላችን የተሳካ ቀዶ ህክምና የተደረገላት ሲሆን አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ ትገኛለች።
Surgeon:Dr Adera
Cheif Anesthesiologist:Dr Teffera/MR Yonas
Ass. Dr Adugna
Scrub nurse:Sr Meaza
Runner:Sr Kimem.
አንጋፋው ፈለገ ህይወት

10/03/2026
በማህበራዊ ድህረ ገፅ ስለ ህመማቸው ብዙ ሲዘዋወር ያየናችው እናት እጅግ ከባድ በሆነ እጢ ለረጅም አመት ሲሰቃዩ የነበሩ እናት ከነበረባቸው ዕጢ ስኬታማ የሆነ ቀዶ ህክምና በፈለገ ህይወት አጠ...
07/03/2026

በማህበራዊ ድህረ ገፅ ስለ ህመማቸው ብዙ ሲዘዋወር ያየናችው እናት እጅግ ከባድ በሆነ እጢ ለረጅም አመት ሲሰቃዩ የነበሩ እናት ከነበረባቸው ዕጢ ስኬታማ የሆነ ቀዶ ህክምና በፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተከናውኗል።

ቀዶ ጥገናው በ27/06/2018 ዓ.ም ተሰርቶላቸው በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡

ዶ/ር ካሳው ENT Specialist ከነ ረዚደንት ሀኪሞቹ ክብር ይስጥልን
በስረው ላይ የተሳተፋችሁ የፈለገ ህይወት ሆስፒታል OR ቲም በሙሉ እናመሰግናለን፡፡

ትልቅ ስኬት ትልቅ ድል እያስመዘገበ ያለ የህዝብ አገልጋይ ተቋም
07/03/2026

ትልቅ ስኬት ትልቅ ድል እያስመዘገበ ያለ የህዝብ አገልጋይ ተቋም

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የሆስፒታሎች ውድድር 30 ከፍተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን 1-ከ20_30 ለወጡ የነሀስ ማእረግ2-ከ10-20 የወጡ የብር ማእረግ 3_ከ1_1...
07/03/2026

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የሆስፒታሎች ውድድር 30 ከፍተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን
1-ከ20_30 ለወጡ የነሀስ ማእረግ
2-ከ10-20 የወጡ የብር ማእረግ
3_ከ1_10 ለወጡ ከፍተኛ የወርቅ ሜዳሊያ አና 5ሚሊየን ብር ሽልማት የተበረከተ ሲሆን 100% በማምጣት የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ1ኛ ደረጃ በመውጣት የተሸለመ ሲሆን
የአማራ ክልል ጤና ቢሮም ብዙ ሆስፒታሎችን በማሸለም እውቅና ተሰጥቶታል።

በዛሬው እለት ማለትም በ28/06/2018 የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ም/ኋላፊ አቶ አበበ ተምትሜ የፈለገ ህይወት ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ አብይ ፍስሀ የአንጅባራ ሆስፒታልና የፓዊ ሆስፒታል ስራ አስኪያጆች በተገኙበት በፈለገ ህይወት ሆስፒታል ሰራተኞች ሞቅ ያለ አቀባበል የቸደረገ ሲሆን

በሀገር አቀፍ ደረጃ 1ኛ መውጣታቸው በቀጣይ የተሻለ ስራ እንዲሰሩ መነቃቃትን የፈጠረ በመሆኑ ለአብክመ ጤና ቢሮ ምስጋና አቅርበዋል።

እንኳን ደስ አላችሁ  የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የሆስፒታሎች ውድድር በኢትዩጵያ ደረጃ ካሉ ከ415 በላይ   ሆስፒታሎች መካከል    1ኛ ...
06/03/2026

እንኳን ደስ አላችሁ
የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የሆስፒታሎች ውድድር በኢትዩጵያ ደረጃ ካሉ ከ415 በላይ ሆስፒታሎች መካከል
1ኛ ደረጃ በመውጣት የ5ሚሊየን ብር የገንዘብና የወርቅ ዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችሏል።
የሆስፒታሉ ሰራተኞች እና ተገልጋዬቻችን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።

03/03/2026
የባህር ዳር ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመንና ተወዳዳሪ የህክምና ማዕከል ለመሆን እየሰራ ያለውን መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ የርክክብና የምረቃ ...
03/03/2026

የባህር ዳር ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመንና ተወዳዳሪ የህክምና ማዕከል ለመሆን እየሰራ ያለውን መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ የርክክብና የምረቃ መርሃ ግብር አካሄደ።

በዕለቱም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጤና ቢሮ የገንዘብ ድጋፍ የተከናወነው የምዕራፍ አንድ የእድሳትና ማስፋፊያ ስራዎች ተመርቀዋል። በተጨማሪም የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረው የኤም አር አይ (MRI) የህክምና መሣሪያ በይፋ ርክክብ ተደርጎለታል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አብይ ፍስሀ እንደገለጹት፣ ተቋሙን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በተከናወኑ ቆራጥ ስራዎች አሁን ላይ ተወዳዳሪ ደረጃ ላይ መድረስ ተችሏል።

በተለይም አዲሱ የኤም አር አይ ማሽን መገኘቱ ቀደም ሲል ህብረተሰቡ ለምርመራ ይከፍል የነበረውን ከፍተኛ ወጪ የሚቀንስና ለገንዘብ እጦት ይቸገሩ ለነበሩ ወገኖች ትልቅ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል። መሳሪያው ዘመኑ የደረሰበት የመጨረሻ ቴክኖሎጂ በመሆኑም ውስብስብ የጤና ችግሮችን ለይቶ ለማውጣት ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተገልጿል።

የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ፍስሀ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ ተቋሙ ያሉበትን ችግሮች በመለየትና መፍትሄ በማምጣት ረገድ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል።

በቆይታቸውም ለህሙማን ምቹ ሁኔታን በመፍጠር፣ የህክምና መሳሪያዎችን በማሟላትና የመድኃኒት እጥረትን በመቅረፍ ረገድ ለውጦች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ተጀምረው የቆዩ የህንፃ ግንባታዎች በድጋሚ እንዲቀጥሉ መደረጉም ሆስፒታሉ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችለው አመልክተዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፣ ጤና ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገትና ለሰብአዊ ሀብት ልማት መሰረት መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።

መንግስት ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር በጤናው ዘርፍ የማከምና የመከላከል ስራዎችን አቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የህዝብን ክብርና ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሰፍን ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የጤና አገልግሎቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ እንደ ልዩ ትኩረት የተያዘው ፅዱ የጤና ተቋማትን መፍጠርና አጠቃላይ አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማዘመን እንደሆነ ተጠቁሟል። በዕለቱ የምዕራፍ ሁለት የእድሳት ሂደት ምልከታ የተደረገ ሲሆን፣ የምዕራፍ ሶስት የእድሳት ስራ ደግሞ በይፋ ተጀምሯል።

የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር  እና የጡት ካንሰር ልየታ በባህር ዳር ከተማ ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተካሄደ‎‎በአለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ50 "የሴቶች...
28/02/2026

የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር እና የጡት ካንሰር ልየታ በባህር ዳር ከተማ ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተካሄደ

‎በአለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ50 "የሴቶች ድምፅ ለእኩልነት እና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በሆስፒታሉ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ክልላዊ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር እና የጡት ካንሰር የምርመራ ፕሮግራም ከክልሉ ጤና ቢሮ እና የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በጋራ አካሂደዋል።

‎በአማራ ክልል በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ እንደተናገሩት እህቶቻችን ወደ ፊት ለማምጣት ተላላፊም ሆነ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታ እራሳቸውን እንዲጠብቁ ርብርብ ስናደርግ ነው ብለዋል።


‎በመድረኩ መክፈቻ ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጌትነት እንደተናገሩት የቅድመ ካንሰር ምርመራ በማድረግ የማህፀን በር ካንሰር እና የጡት ካንሰር በተገቢው ጊዜ መታከም ከተቻለ በሽታ ደረጃ ላይ ሳይደርስ መከላከል እንደሚቻል አስረድተዋል

‎በክልሉ በ6 ወራት ውስጥ 1መቶ 58 ሺህ በላይ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ልየታ የተደረገ ሲሆን 7 መቶ በላይ የሚሆኑ ሴቶች ደግሞ ካንሰር እንዳለባቸው በምርመራው መታወቅ መቻሉን አቶ መልካሙ ተናግረዋል።

‎የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዝናሽ ጌታቸው በበኩላቸው በሴቶች ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ለውጦች እንዲመጡ በማድረግ እና ችግሮችን በመቅረፍ ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።


‎በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተካሄደው መድረክ የክልሉ ጤና ቢሮ፣ የአብክመ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና የሆስፒታሉ ሴት አመራርና ሰራተኞች ተሳትፈው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር እና የጡት ካንሰር ልየታ አካሂደዋል፡፡

አስደሳች ዜና !!!አንጋፋው ሆስፒታላችን የፈለገ ህይወት ሆስፒታል ለክልላችን ህዝብ አዳዲስ ህክምና  ማስፋፋት  አንዱ አላማው መሆኑ ይታወቃል።በዛሬው ዕለት አንገብጋቢ  ከሆኑ የማህበረሰባችን...
26/02/2026

አስደሳች ዜና !!!
አንጋፋው ሆስፒታላችን የፈለገ ህይወት ሆስፒታል ለክልላችን ህዝብ አዳዲስ ህክምና ማስፋፋት አንዱ አላማው መሆኑ ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት አንገብጋቢ ከሆኑ የማህበረሰባችን ህክምና የላንቃ እና ከንፈር ክፍተት ከSmile train ጋር በመተባበር ከዚህ በፊት በዘመቻ የሚካሄደውን በቋሚነት በነፃ መጀመራችን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው።
ስለሆነም
የከንፈር እና ላንቃ ክፍተት ያለባቸው ህፃናት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መረጃውን በመጋራት እንድንተባበር እናሳስባለን።

Address

Kebelle 13
Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Felege Hiwot Comprehensive Specialized Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share