Amhara Information Service

Amhara Information Service For whatever it's worth, never fall a victim of the struggle and when it so happens remain a soldier.

በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የማይሰለፍ የትኛውም አደረጃጀት የሕዝብ ጠላት ነው።አሁን ባለው የኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ ጦርነት ትውልድን ሊያሻግር አይችልም።የጦርነት ነጋሪት የመትጎ...
18/02/2026

በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የማይሰለፍ የትኛውም አደረጃጀት የሕዝብ ጠላት ነው።
አሁን ባለው የኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ ጦርነት ትውልድን ሊያሻግር አይችልም።
የጦርነት ነጋሪት የመትጎስሙና የሕዝብ ጠላትነት ውስጥ የተዘፈቃችሁ ሁሉ ከፊታችሁ ያለው ጊዜ የውድቀት ነው።

በሰላማዊ የትግል መስመር የተሰለፋችሁ ደግሞ ለትውልዱ ልዩ የድል ብሥራቶች ናችሁ።

ከጅምሩም የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ ሁኔታ እስከተፈጠረ ድረስ የትጥቅ ትግል አማራጭ የፖለቲካ መንገድ ሊሆን አይችልም ነበር። አቅሙ አለን ብለው የትጥቅ ትግል ከጀመሩ ሁለት ዓ...
10/02/2026

ከጅምሩም የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ ሁኔታ እስከተፈጠረ ድረስ የትጥቅ ትግል አማራጭ የፖለቲካ መንገድ ሊሆን አይችልም ነበር።

አቅሙ አለን ብለው የትጥቅ ትግል ከጀመሩ ሁለት ዓመት ከሰባት ወር ከሞላቸው በኋላ አንድ ወረዳ እንኳን ማስተዳደር ሲያቅታቸው ደግሞ የአማራ ሕዝብ ለሚያነሳቸው ሁሉም ጥያቄዎች ዋነኛ ተጠያቂ የሆነው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጭ ጋር ጥምረት ፈጥረዋል። የአማራ ሕዝብ ጠላት ፥ የኢትዮጵያም ሕዝብ ጠላት ከሆነው የግብጽ መንግሥትና የሱዳን ጦር ሃይል እንዲሁም የኢሳያስ መንግሥት ጋር ኅብረት ፈጥረዋል።

ከመሰረቱ ለችግሮቻችን መፍትሔዎች የተጣመመና ፀረ ሕዝብ መፍትሔ ይዞ የተነሳ ቡድን ከሕዝብ ጠላት ጋር ኅብረት መፍጠሩ የሚደንቅ አይሆንም። ሁኖም ግን በአንድ ጉዳይ እርግጠኛ መሆን ይቻላል። ሕዝባዊ መሰረታቸውን ፈጽሞ አጥተዋል። ምንም አይነት የሕዝብ ድጋፍ የላቸውም። ምክንያቱም ሕዝቡ ጠላቱን ጠንቅቆ ያውቃል።

የሕወሃት ካድሬ ለአማራ ሕዝብ የሚፈታው አንዳች የፖለቲካ ጥያቄ አለ ብሎ ማመን በራሱ ጽኑ የአእምሮ ህመምተኛ መሆንን ይጠቃል።

እመኑኝ አንድ ዞን የሚቆጣጠር ምንም ኃይል የለም ፥ ከጠላት ጋር ተጣምሮም ማሸነፍ የሚችል አይደለም። ይህ ኃይል ኑሮ ያልተሳካለት፣ በወንጀል የተጨማለቀ፣ የከተማ ሌባ፣ በገጠርም በዝርፊያና ስርቆት የሚታወቅ ፣ መደዴ፣ የፖለቲካ ሀ ሁ ን የማይረዳ opportunist ቡድን ነው። Mark this statement በቅርቡ ይከስማል። የሚተርፈው በአማራ ሕዝብ ውስጥ የሚያሳድረው ማኅበራዊ ምስቅልቅል ብቻ ነው።

ህወሃት ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ጠላት ነው፡፡ ህወሃት ሁልጊዜም የሌሎችን አቅም ተጠቅማ ፊጥ የማለት ብቃት ነው ያላት፡፡ በሻእቢያ ታዝላ አዲስ አበባ እ...
31/01/2026

ህወሃት ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ጠላት ነው፡፡ ህወሃት ሁልጊዜም የሌሎችን አቅም ተጠቅማ ፊጥ የማለት ብቃት ነው ያላት፡፡ በሻእቢያ ታዝላ አዲስ አበባ እንደገባች ሁሉ፤ በፈጠረቻቸው ምስለኔ ድርጅቶች ታዝላ ደግሞ ያን ያክል ጊዜ መንግሥት ሁና ኑራለች፡፡ ዛሬም የምትጋልበው ድርጅትና ሃገር እንዳለ አስልታ ጦርነት መክፈቷ ብቸኛ ተሞክሮዋ ይህ ስለሆነ ነው፡፡

ህወሃት ለኢትዮጵያውያን እድገትና ልዕልና የሚሆን ምንም አይነት ትምህርት የላትም፡፡ ብቸኛ አማራጯብቸኛ ተሞክሮዋን እንደያዘች እያጣጣረች ከኢትዮጵያ ሰማይ ስር መክሰም ብቻ ነው፡፡ አዲሱ ትውልድ ከህወሃት የሚማረው ምንም ነው፡፡

ወረራ እየተፈጸመበት ያለው የጠለምት ሕዝብም እየተናገረ ያለው ይህንኑ ነው፡፡
I stand with Peace and the Telemet People.

Well done!
05/12/2025

Well done!

የዘላቂ ሰላም ስምምነት🙏💪
04/12/2025

የዘላቂ ሰላም ስምምነት🙏💪

#አሚኮ #ዜና

"ዛሬ ለክልላችን ሕዝብ የመጀመሪያው ትልቅ የሰላም ኩነት የተካሄደበት ቀን ነው።ከግጭት አሸናፊም ተሸናፊም የለም፥ ከሰላም ሁሉም ያተርፋል፥ ስምምነቱ ለሰላም ወዳድ ሕዝባችን ትልቅ እፎይታን ይ...
04/12/2025

"ዛሬ ለክልላችን ሕዝብ የመጀመሪያው ትልቅ የሰላም ኩነት የተካሄደበት ቀን ነው።

ከግጭት አሸናፊም ተሸናፊም የለም፥ ከሰላም ሁሉም ያተርፋል፥ ስምምነቱ ለሰላም ወዳድ ሕዝባችን ትልቅ እፎይታን ይሰጣል፡፡

የሕዝብና የመንግሥትን ጥሪ ተቀብለው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለመጡ ወንድሞቻችን እንደ መንግሥት አድናቆትና ክብር አለኝ፡፡"

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
በአማራ ክልል መንግሥትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት ላይ ከተናገሩት።

25/11/2025

ተናግረናል አሁንም እንናገራለን። የአማራን ሕዝብ ሊጠቅም የሚችል "የፋኖ ትግል" የሚባል የለም። የጠላትን አጀንዳ የሚያስፈጽም ከመሆን በስተቀር።

አሁንም እጅ የቆረጠው አማራ ፥ እጁን የተቆረጠው አማራ፥ እጅ ሲቆረጥ በለው በለው የሚለው አማራ ፥ የቆራጩ ደጋፊም ራሱ አማራ ፥ ቆራጩን የሚያወድሰውም ፤ ቆራጩን በዓይኑ በብረቱ እያየው መቃወም ሲገባው "ዐቢይ ነው ቆራጭ" የሚለውም ራሱ አማራ ነው። ማን ነው የተጠቀመው? ማን ነው የተጎዳው? ማንም ከአማራ በስተቀር።

ፋኖ የሚባል አማራን የሚጠቅም አደረጃጀት ይኖራል ብሎ መጠበቅ in physical world ግመል በመርፌ ቀዳዳ ያልፋል ብሎ እንደማመን ያለ ነው።

ዛሬ ሀምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ነው።  ይህ ጊዜ በኢትዮጵያ የበጀት አቆጣጠር የአዲሱ በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የሚጀመርበት ዕለት ነው። በዚህ የሥራ መጀመሪያ ዕለት ርዕሰ መስተዳ...
08/07/2025

ዛሬ ሀምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ነው። ይህ ጊዜ በኢትዮጵያ የበጀት አቆጣጠር የአዲሱ በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የሚጀመርበት ዕለት ነው።

በዚህ የሥራ መጀመሪያ ዕለት ርዕሰ መስተዳድራችን ከሁሉም የክልላችን መሪዎች ጋር በመሆን በመላው የክልላችን ሕዝብ ንቁ ተሳትፎ የሚደረግባቸው 3 ዐበይት የንቅናቄ መርሀ ግብሮችን አስጀምረዋል።

☑️ የ2017 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በሁሉም የክልላችን ወረዳዎች በይፋ ተጀምሯል። የጦርነት ቀጠና በነበረው ይልማና ዴንሳ ወረዳ ታሪክ ተቀይሮ አቦላ ተራራ ላይ በየዕለቱ ለሰላምና ለኅብረተሰብ ተጠቃሚነት እንደምንሠራ በማሳየት በክልሉ 1.6 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የመጀመሪያው ፊሽካ ተነፍቷል።

☑️ የዜጎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት ባህላችንን የበለጠ በማስፋት የማኅበረሰባችን በጎ እሴት አንድ እርምጃ ከፍ ብሎ ተቋማዊ እንዲሆን የሚያስችለው የንቅናቄ መድረክ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ርዕሰ መስተዳድራችን ተገኝተው ሁሉም የክልላችን ነዋሪ አንድነቱን፥ መተሳሰብና መዋደዱን እንዲያጸና መልእክት አስተላልፈዋል።

☑️ የክልሉ ኢኮኖሚ በሚያመነጨው ልክ የመሰረተ ልማት ግንባታ እንዲስፋፋና የልማት አቅማችንን መሰረት ለማጽናት በክልሉ የሚገኙ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች የግብር ማስጀመሪያ መርሀ ግብርንም አብሥረዋል።

ጊዜው ይነጉዳል፥ መሪ ከሆንክ ደግሞ ከእያንዳንዷ ዕለት ጋር ትግል ትጀምራለህ። እቅድህን ለማሳካት የምትቀጥረው ቀን የለም። ሁሉም ቀን የሥራ ቀን ነው።

2018 በጀት ዓመት የውጤትና የስኬት ዓመት ይሁን።

የሕዝባችን ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል💪🥇
29/06/2025

የሕዝባችን ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል💪🥇

ጥሩ ጅምር ነው።የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ አሁን ትናንት ከነበረው በተጨማሪ ሌሎች ጥያቄዎችም አሉት። ከትግራይ ሕዝብ ጋር በገዥና በተገዥ ትርክት ሳይሆን በመከባበርና በሰላም መኖር ይፈልጋል። ር...
23/06/2025

ጥሩ ጅምር ነው።
የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ አሁን ትናንት ከነበረው በተጨማሪ ሌሎች ጥያቄዎችም አሉት። ከትግራይ ሕዝብ ጋር በገዥና በተገዥ ትርክት ሳይሆን በመከባበርና በሰላም መኖር ይፈልጋል። ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት የማንነትና የወሰን ጥያቄው "ዘላቂ ሰላም በሚያመጣና ሕጋዊ ቅቡልነት ባለው መንገድ" መፈታት ይገባዋል። ይኽም የሕዝቡ ፍላጎት ነው።

የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ላለፋት 2 ዓመት በላይ (ከሕወሃት ነጻነቱን ካገኘ ወዲህ) ከሚያገኘው ክልላዊ አስተዳደራዊና የተቋማት ትይዩ ድጋፍ በስተቀር ያለ መደበኛ በጀት ሰላም አስፍኖ፥ ድንበር እየጠበቀ፥ ልማት እያለማ፥ የተረጋጋ አካባቢን ፈጥሮ በአርዓያነት እየኖረ ነው።

በዛሬው ዕለት ክቡር ርዕሰ መስተዳድራችን ከአቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች መሪዎቻችን ጋር በሑመራ ከተማ ተገኝተው ውይይት ማድረጋቸው እጅግ የሚበረታታ ጥሩ ጅምር ነው። በርቱልን።

ጦርነት ተፈጥሯዊ ባሕሪው አውዳሚነት መሆኑ የማይካድ ቢሆንም ቢያንስ "የሞትንለት፥ ዋጋ የከፈልንበት" ተብሎ የሚጠራዓላማ ሊኖረው ግን ይገባ ነበር። አማራ ክልል የገጠመን ጉዳይ ትግል ከመፈጠሩ...
18/06/2025

ጦርነት ተፈጥሯዊ ባሕሪው አውዳሚነት መሆኑ የማይካድ ቢሆንም ቢያንስ "የሞትንለት፥ ዋጋ የከፈልንበት" ተብሎ የሚጠራ
ዓላማ ሊኖረው ግን ይገባ ነበር። አማራ ክልል የገጠመን ጉዳይ ትግል ከመፈጠሩ እንኳን አስቀድሞ ሊኖረው የሚገባው ጉዳይ (ዓላማ) የሌለ መሆኑ ነው።

ወገንህን ትጨፈጭፋለህ፥ ትዘርፋለህ፥ ታግታለህ፥ ትደፍራለህ፥ እንዳይማር ታደርጋለህ፥ ከሕዝብ ጠላት ጋር ትሠራለህ፥ ነጻ የምርትና የሸቀጦች ዝውውር እንዳይኖር በማድረግ ወገንህን ታደኸያለህ ፥ አንድነት የሚባል የለህም እርስበርስ ትበላላለህ ... ይህን ሁሉ እያደረክ ፋኖ ትባላለህ።

እውነት ነው መንግሥት ሠራዊት ሳያዘምት በያላችሁበት አንቆ ለመንግሥት የሚያስረክብ ሕዝብ እየተፈጠረ ነው ፥ አብዝቶ ይፈጠራልም። በቅርብ በዓይናችን የምናየው ሐቅ ይኸው ነው።



Address

Giorgis Road
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Information Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Information Service:

Share