26/08/2026
እውነተኛ መሪዎችን እንጂ ጉዳይ አስፈጻሚ ምስለኔዎችን የሚቀበል ሕዝብ የለም።
ከሰሞኑ በሃገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የምክክር ሂደት ላይ እውነተኛ የሕዝብ ልጆች መሪዎቻችን ፥ የአክራሪ የፖለቲካ ቡድኖችን ፍላጎት ለመላው ኢትዮጵያዊ ስላጋለጡ ጥርስ እንደተነከሰባቸው የውስጥ መረጃ ደርሶናል።
በምክክር ሂደት የሃሳብ ልዩነት የሚጠበቅ ቢሆንም እኛ ያልነው ካልሆነ ሃገር የሚባል ወይም የጋራ ተጠቃሚነት የሚባል መርህ ገደል ይግባ የሚለው አክራሪ ብሔረተኛና ቆሞ ቀሩ የፖለቲካ ቡድን የዓላማየ እንቅፋት ናቸው ያላቸውን ጀግኖች መሪዎቻችንን ወደ ፌዴራል መንግሥት እንዲመደቡ በማድረግ አዳዲስ ምስለኔዎችን በቦታቸው ለመመደብ ግፊት እያደረገ ነው።
ይህ ቡድን በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተደምሮ ሃገሩን የሚያሻግርበትን የሃገረ መንግሥት ግንባታ እውን በማድረግ ላይ ያለው ብልጽግና ፓርቲና የመንግሥት መዋቅርን እንደ ሽፋን በመጠቀም፤ ስሁት የሆነውን የቡድን ፍላጎቱን ለማሳካት የሚያስችል እድል ለመፍጠር በክልሉ መንግሥት አስተባባሪዎች ላይ ምስለኔዎችን ለመመደብ የሚያደርገው ጥረት ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም።
ክልላችን የአክራሪ ብሔረተኞችን ፍላጎት የሚያስፈጽሙ፥ ተለጣፊና አድርባይ ምስለኔዎችን የሚቀበሉበት ትከሻ የላቸውም።
እየተገነባ ያለውን ጠንካራ ሃገረ መንግሥት በጠንካራ ተቋማትና መሪዎች በማስቀጠል ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ለማውረስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የአማራ ክልል መሪዎች ታምነው የሚቀጥሉ እንጂ ለእኔ ብቻ የሚለውንና system sabotage ውስጥ እየዳከረ የሚገኘውን ንዑስ አንባገነን ቡድን ለማንገሥ የሚሠሩ አይደሉም። ሕዝባችንም ፈጽሞ አይቀበለውም።