27/05/2026
የአይከል ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ወርቁ ጎሼ የተላለፈ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
ግንቦት 19/09/18 ዓም. አይከል ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት
እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለው በዓሉ የፍቅር፣ የርህራሄ፣ የመተሳሰብ፣ የአብሮነት እና የመረዳዳት እሴቶች በጉልህ የሚገለጡበት ታላቅ በዓል ነው። በዚህ በዓል ሰዎች አንድነትን ያጠናክራሉ፣ የተቸገሩ ወገኖችን ይደግፋሉ፣ የሰላምና የመቻቻል እሴቶችንም ያጎለብታሉ።
በመሆኑም የአካባቢያችን እና የከተማችን ሰላም ነቅተን በመጠበቅና የሰላም አምባሳደሮች በመሆን ሁሉም ህዝበ ሙስሊም በዓሉን በታላቅ ደስታ እና ሰላም እንዲያከብር መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህ የተባረከ የበዓል ቀን ደስታችንን ከሌሎች ጋር በመጋራት፣ የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመደገፍ፣ ሰላማችንንና አንድነታችንን በመጠበቅ በዓሉን እናክብር።
በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ!
መልካም የኢድ አል-አድሃ በዓል!
ኢድ ሙባረክ!
አይከል 19/2018