30/09/2024
ውድ #የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን በመስከረም ወር የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ እንዴት ማስላት እንዳለብዎ ያውቃሉ? ካለወቁ በምሳሌ እናስረዳዎ!!
አንድ ደንበኛ በመኖሪያ ቤቱ 4 ባለ 60 ዋት አምፖሎች በቀን ለ6 ሰዓት በወር ለ30 ቀናት ቢያበራ፣ 3000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም የእንጀራ ምጣድ በቀን ለ2 ሰዓት በወር ለ10 ቀናት ቢጠቀም እና 1000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም ምድጃ በቀን ለ5 ሰዓት በወር ለ30 ቀናት ቢጠቀም ፤
በዚህም መሰረት፡-
1ኛ. 4 አምፑል X 60 ዋት x 6 ሰዓት x 30 ቀናት = 43,200 ዋት.ሰ፣
2ኛ. 3000 ዋት ኤሌክትሪክ የኃይል የሚጠቀም የእንጀራ ምጣድ x 2 ሰዓት x 10 ቀናት=60,000 ዋት.ሰ፣
3ኛ.1000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም ምድጃ x 5 ሰዓት x ለ30 ቀናት = 150,000 ዋት.ሰ፣
ሶስቱም ሲጠቃለሉ 43,200 ዋት.ሰ + 60,000 ዋት.ሰ + 150,000 ዋት.ሰ = 253,200 ዋት.ሰ ይሆናል፡፡
ይህም ወደ ኪሎ ዋት ሰዓት ሲቀየር 1 ኪሎ ዋት ሰዓት = 1000 ዋት ሰዓት በመሆኑ፤ 253,200 ዋት ሰዓት = 253.2 ኪሎ ዋት ሰዓት ይሆናል፡፡
በዚህ ስሌት መሰረት ከላይ በምሳሌው የጠቀስነው ደንበኛ በወር 253.2 ኪ.ዋ.ሰ የኤሌክትሪክ ኃይል ቢጠቀም በተቀመጠው እርከን መሰረት በ2.46 ብር ይባዛል፡፡
በዚህ መሰረት 253.2 ኪ.ዋ.ሰ x 2.46 ብር= 622.872 ብር ይመጣል፡፡ የአገልግሎት ክፍያ ብር 42.95 እና የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ 10 ብር ሲደመርበት በአጠቃላይ የደንበኛው ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ 675 ብር ከ 80 ሳንቲም ይሆናል ማለት ነው፡፡
ይህ የፍጆታ ሂሳብ ስሌት የሚያገለግለው ለድህረ-ክፍያና ለመስከረም ወር ብቻ ነው፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት